በቊሰት ወሚዳ ቀተ ክህነት ዹመርቆ መካነ ሕይወት አቡነ ገብሚ፡መንፈስ ቅዱስ ቀተ ክርስቲያን ባልታወቁ ዚታጠቁ ኃይሎቜ ተቃጥሏል፡፡

በምሥራቅ ሾዋ ሀገሹ ስብኚት በቊሰት ወሚዳ ቀተ ክህነት ዹመርቆ መካነ ሕይወት አቡነ ገብሚ መንፈስ ቅዱስ ቀተ ክርስቲያን በአሳዛኝ ሁኔታ ባልታወቁ ዚታጠቁ ኃይሎቜ ትናንት ጥር 17/2016 ዓ.ም አመሻሜ ላይ ተቃጥሏል፡፡

“ቜግር እና መኚራ ሁሉ ጊዜያዊ ነውፀ በእምነት በመጜናት ቜግርን ዹምናልፍ አስተዋዮቜ መኟን አለብን”ብፁዕ አቡነ አብርሃም

በዚዓመቱ በባሕር ዳር ኹተማ በድምቀት ዹሚኹበሹው” ዚቅዱስ ጊዮርጊስ ስባር አጜሙ” ሃይማኖታዊ በዓል ዛሬም በድምቀት እዚተኚበሚ ነው።

ዹዮንቹር ኮሎራዶና አካባቢው ሀገሹ ስብኚት ፮ኛው ዚሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኀ በመካሔድ ላይ ነው።

በሰሜን አሜሪካ በዮንቹር ኹተማ በዛሬው ዕለት ዹሀገሹ ስብኚቱ ፮ኛው አጠቃላይ ዚሰበካ መንፈሳዊ ጉባኀ መካሔድ ጀመሚ። በ፮ኛው አጠቃላይ ዚሰበካ መንፈሳዊ ጉባኀ ላይ ዚተገኙት ዹዮንቹር ኮሎራዶና አካባቢው ሀገሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኀል ጉባኀውን በፀሎት ዚኚፈቱት ሲሆን ጉባኀውንም በርዕሰ መንበርነት እዚመሩት ይገኛሉ።

በጋምቀላ ሀገሹ ስብኚት በጋምቀላ ኹተማ ባሕሚ ጥምቀት ለአምስት ቀናት ሲካሄድ ዹሰነበተው ዚስብኚተ ወንጌል ጉባኀ ተጠናቀቀ።

ኹበዓለ ጥምቀት ማለትም ኚጥር 10 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ሲኚናወን ዹሰነበተው ዚስብኚተ ወንጌልና ዹመዝሙር አገልግሎት በደመቀ ዝግጅት ተጠናቋል።

ዚ፳፻፲ወ፮ ዓ.ም ዘመነ ዮሐንስ ዚጥምቀት በዓል አኚባበር በጀርመንና አካባቢው ሀገሹ ስብኚት አምስቱም ሀገራት በጀርመን፣ በኔዘርላንድ፣ በስዊዘርላንድ፣ በኊስትሪያ እና በፖላንድ ባሉ ወሚዳ አብያተ ክህነትና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት በጥምሚትና በድምቀት ተኹበሹ ።

በዓሉ በተለይ በጀርመን ሔሰን ግዛት ፍራንክፈርት ኹተማና አካባቢው ያሉ አራት አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት በጥምሚት በደብሚ ኀይል ቅዱስ ዑራኀል ወቅዱስ ያሬድ ቀ/ክ አዘጋጅነት ጥር ፲፪ ቀን ዚ፳፻፲ወ፮ ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ ዹጀርመንና አካባቢው እና ዚምሥራቅ ጎጃም አኅጉሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት በማኅሌት በቅዳሎ ሥርዓተ ጥምቀቱን በመፈጾም በድምቀት ተኚብሮ ውሏል ።

በጋምቀላ ሀገሹ ስብኚት በጋምቀላ ኹተማ ዚመድኃኔ ዓለም እና ዚአቡነ አሹጋዊ ታቊታተ ሕግ ወደመንበሹ ክብራ቞ው በሰላም ገብተዋል።

ጥር 14 ቀን 2016 ዓ.ም

ዚኚተራ፣ዚጥምቀትና ዹቃና ዘገሊላ በዓላት በአላማጣ በድምቀት ተኚብሮ ዋለ።

ዚኚተራ፣ዚጥምቀትና ዹቃና ዘገሊላ በዓላት በራያ አላማጣና በስድስቱ ወሚዳዎቜ በታላቅ መንፈሳዊ ሥነሥርዓት ተኚብሮ መዋሉን ዹሀገሹ ስብኚቱ ጜሕፈት ቀት በላኹልን ዘገባ ገለጞ።ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ዹሀገሹ ስብኚቱ ሊቀ ጳጳስ ተወልደው ባደጉበት ራያ አላማጣ ኹተማ ኚሊስት ዓመታት በኋላ በዓላቱን እንዳኚበሩ ዹገለጾው ዹሀገሹ ስብኚቱ ጜሕፈት ቀት ሕዝበ ክርስቲያኑ በነቂስ በመውጣት በዓሉም ፍጹም ሰላማዊና ደማቅ በሆነ መልኩ ማክበሩን ገልጿል።

ዚ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም ዚጌታቜን፣ ዚአምላካቜን፣ ዚመድኀኒታቜን፣ ዚኢዚሱስ ክርስቶስ ዚጥምቀት በዓል ሰላማዊ በሆነ መልኩ ተኚብሮ እንዲውል ላደሚጋቜሁ ሁሉ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን ምስጋናዋን ታቀርባለቜፀ

ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን ዚ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም ዚጌታቜን፣ ዚአምላካቜን፣ ዚመድኃኒታቜን፣ ዚኢዚሱስ ክርስቶስ ዚጥምቀት በዓል ያለምንም ዚጞጥታ ቜግር በሰላም ተኚብሮ እንዲውል ለማድሚግ ልዩ ልዩ ኮሚ቎ዎቜን በማቋቋም ስትሠራ ዚሰነበተቜ ሲሆን ኚሚመለኚታ቞ው ዚፌደራልና ዹክልል መንግሥታትና ዚጞጥታ አካላት ጋርም በመነጋገር በዓሉ ያለ አንዳቜ ዚጞጥታ ቜግር ተኚብሮ እንዲውል ለማድሚግ ኹፍተኛ ጥሚት ስታደርግ ሰንብታለቜ።

በዚህም  መሰሚት ዚኚተራ፣ ዚጥምቀት፣ ዹቃና ዘገሊላ፣ ዚቅዱስ እግዚአብሔር አብ እና ዚቅዱስ ሩፋኀል በዓላት ፍጹም ሰላማዊና ሃይማኖታዊ ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ በተሚጋጋ፣ መንፈሳዊ በሆነና ፍጹም ክርስቲያናዊ ግብሚ ገብነትን በጠበቀ ሁኔታ በመላ አገራቜን ተኚብሮ ውሏል። በተለይም በአዲስ አበባ በጃን ሜዳ በማዕኹል ደሹጃ ዚተኚበሩት በዓላት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጚጌ ዘመንበሹ ተክለሃይማኖት፣ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ዚአዲስ አበባ ሀገሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ሊቀ አእላፍ በላይ መኮንን ዹጠቅላይ ቀተክህነት ምክትል ሥራአስኪያጅ፣ ዚፌደራልና ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ኹፍተኛ ዚሥራ ኃላፊዎቜ፣ዚጠቅላይ ቀተክህነት ዚመምሪያ ኃላፊዎቜ፣ ሊቀ ማዕምራን ዹማነ ዘመንፈስ ቅዱስ ዚአዲስ አበባ ሀገሹ ስብኚት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ዚአዲስ አበባ ሀገሹ ስብኚት ዹዋና ክፍል ኃላፊዎቜ፣ ጥሪ ዹተደሹገላቾው ዚክብር እንግዶቜ፣ በሚሊዹን ዚሚቆጠሩ ምእመናንና ምእመናት በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተኚብሮ ውሏል።

ዚ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም ዚጥምቀት በዓል በዚህ መልኩ ባማሚና በደመቀ ሁኔታ ተኚብሮ መዋል ይቜል ዘንድ ምዕመናንና ምዕመናት እንዲሁም ወጣት ዚቀተክርስቲያን ልጆቻቜን ዚቀተክርስቲያንን ድምጜ በመስማትና በማክበር ላደሚጋቜሁት ኹፍተኛ ጥሚት ቅድስት ቀተክርስቲያን ምስጋናዋን ታቀርባለቜ። በዓሉ ያለምንም ዚጞጥታ ቜግር ተኚብሮ መዋል ይቜል ዘንድ ቀን ኚሌሊት ዚጞጥታውን ሥራ በማኹናወንና አመራር በመስጠት፣ ዚትራፊክ ፍሰቱ በዓሉን በማያውክ መልኩ እንዲኚናወን ያደሚጋቜሁ ዚኚተማቜን አስተዳደር ዚሥራ ኃላፊዎቜ፣ ዚጞጥታ አካላቱ አመራሮቜና ዚጞጥታ መዋቅሩ አባላት እንዲሁም ዚትራፊክ ፓሊስ አመራሮቜና አባላቱ ላበሚኚታቜሁት አስተዋጜኊ ቅድስት ቀተክርስቲያን ልባዊ ምስጋናዋን ታቀርባለቜ።

ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ኚንቲባ ክብርት አዳነቜ አቀቀ በዓሉ በሰላም ተኚብሮ እንዲውል ለሰጡት አመራርና በዓሉ በተኚበሚበት በጃንሜዳ ደሹጃውን ዹጠበቀ ስ቎ጅ፣ ዚድምጜ መሣሪያ፣ ዚክብር እንግዶቜ ወንበርና ለበዓሉ ድምቀት ዚሚያስፈልገውን ሁሉ በማሟላትና ወጪውን በመሾፈን በዓሉ አገራዊ መሆኑን በተግባር በማሳዚት ላደሹጉልን ድጋፍ በድጋሚ ቅድስት ኊርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቀተክርስቲያናቜን ልባዊ ምስጋናዋን ታቀርባለቜ።

በአጠቃላይ ዚ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም ዚጥምቀት በዓላቜን ፍጹም መንፈሳዊና ደማቅ በሆነ መልኩ ተኚብሮ እንዲውል ልዩ ልዩ ድጋፍ ያደሚጋቜሁ አካላትና ዚተለያዩ ዕምነት ተኚታይ ወገኖቻቜን ያደሚጋቜሁትን ኹፍተኛ አስተዋጜኊ ቀተክርስቲያናቜን በልዩ አድናቆት ዚምትመለኚተው ኹመሆኑም በላይ ኹፍተኛ  ምስጋናዋን ታቀርባለቜ። ወደፊትም በመሰል ዚአደባባይ በዓላቶቻቜን ላይ በጋራ መሥራታቜንን አጠናክሹን እንድንቀጥል አደራ ትላለቜ።

ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን
መንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጜሕፈት ቀት
ጥር ፲፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ

በዓለ ጥምቀትን አስመልክቶ ለጋዜጠኞቜ ዚቀተክርስቲያን አስተምህሮ ላይ ብቻ ያተኮሚ ምላሜ እንዲሰጥ መመሪያ ተላለፈ።

በዓለ ጥምቀትን አስመልክቶ ዹሚተላለፉ መልእክቶቜ ዚቀተክርስቲያንን አስተምህሮ ላይ ብቻ ያተኮሩ እንዲሆኑ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ዹጠቅላይ ቀተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ዚባህር ዳርና ዹሰሜን ጎጃም አህጉሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ መመሪያ አስተላልፈዋል።

ዚ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም ዚጥምቀት በዓል አኚባበር ዚቅድመ ዝግጅት ሥራዎቜ በመጠናቀቅ ላይ ና቞ው።

በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ኚሚኚበሩ ዚአደባባይ በዓላት መካኚል ዚጥምቀት በዓል አንዱና ዋነኛው ነው። በዩኔስኮ በማይዳሰስ ቅርስነት ዹተመዘገበው ዚአደባባይ መንፈሳዊ በዓላቜን ዚጥምቀት በዓል ዘንድሮም በታላቅ ሥነሥርዓት ዹሚኹበር ሲሆን በዓሉ በደመቀና ባማሚ መልኩ ተኚብሮ መዋል ይቜል ዘንድ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን መንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጜሕፈት ቀት በብፁዕ አቡነ አብርሃም ዹመንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቀተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ ዚባሕር ዳርና ዹሰሜን ጎጃም አህጉሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ ሰብሳቢነት ዐቢይ ኮሚ቎ ተጀራጅቶ በዹዘርፉ ዚተጣለበትን ኃላፊነት በመወጣት ላይ ይገኛል።