ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ

በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ አገልግሎትና የስራ አፈጻጸም ላይ ለመምከርና ለመወሰን ኃላፊነት ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት መደበኛና ዓመታዊ ጉባኤውን የጀመረ መሆኑን ለሕዝበ ክርስቲያኑ እናበስራለን፡፡
እግዚአብሔር ጉባኤያችንን ይባርክ!

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በ፵፫ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ ያስተላለፉት መልዕክት፤

ጥቅምት ፬ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት የሕግ አገልግሎት መምሪያ ሥር የተቋቋመው የሕግ ባለ ሙያዎች ዐቢይ ኮሚቴ ጠቅላላ ጉባኤ አካሔደ።

ጥቅምት 3 ቀን 2017 ዓ.ም.

ኹለተኛው የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃና መምሪያ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የ12ኛ ክፍልን ያጠናቀቁ ተማሪዎች የምርቃት መርሐ ግብር በጠቅላይ ቤተክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ ተከናወነ።

ጥቅምት 2 ቀን 2017ዓ.ም.

ለሦስት ወራት በ6 አህጉረ ስብከት ሲካሄድ የነበረው ሐዋርያዊ ጉዞ ለቤተክርስቲያን ዘርፈ ብዙ ትርፎችን በማትረፍ ተጠናቀቀ

ጥቅምት 1 ቀን 2017 ዓ.ም.

በህገ ወጥ መንገድ ተሠብሮ ከአገልግሎት ውጪ የነበረው  የምዕራብ ወለጋ መንበረ ጵጵስና   ጥገና ተደገርጎለት  በሰባቱ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ሩፋኤል ተባርኮ  ዳግም አገልግሎት  መስጠት ጀመረ።

መስከረም 29 ቀን 2016ዓ.ም.

ኮሚቴው የማጣራት ሥራው የደረሰበትን ደረጃ በተመለከተ ለጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር ጉባኤ ሪፖርት አቀረበ።

መስከረም ፳፰ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም

ብፁዕ አቡነ ገሪማ የጌዴኦ ኮሬና ቡርጅ ሀገረ ስብከት ጳጳስ በልዩ ልዩ የሙያ ዘርፍ ተሰማርተው በአዲስ አበባ ከሚገኙ ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ጋር በሀገረ ስብከቱ በሚከናወኑ ዕቅዶች ዙሪያ ውይይት አደረጉ።

መስከረም 27 ቀን 2017ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የማኅበራት ምዝገባ፣ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ ፈቃድ ከተሰጣቸው ማኅበራት ጋር የምክክርና የውይይት መርሐ ግብር እየተካሔደ ነው።

መስከረም 27 ቀን 2017ዓ.ም.

በቤተክርስቲያን ለውጥና እድገት እንዲመጣ በመሻት ምእመናን የሚሰጡትን በቅንነት ተቀብሎ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ተገለጸ።

መስከረም 26 ቀን 2017 ዓ.ም

በፌስቡክ ያግኙን

የኅትመትና ሚዲያ ዋና ክፍል

ብፁዕ አቡነ አብርሃም

የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ

በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ

ለውስጥ አገልግሎት

የኢሜይል አገልግሎት

ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን

ርእይ

ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት

ተልእኮ

  • የእግዚአብሔርን ቃል ለሰው ልጆች ሁሉ ማስተማርና ማዳረስ

  • ሰውን በሁለንተናዊ ሰብእናው ማገልገልና ማዳን

  • ሰውን ሁሉ በነገረ መለኮትና በነገረ ጥበብ ትምህርት በማልማት በመንፈሳዊም ሆነ በሥጋዊ ሕይወቱ የተሻለ ኑሮ እንዲኖረው ማድረግ

  • ጥራትና ብቃት፣ ፍትሐዊነትና እኩል ተደራሽነት ያለው መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ለሰው ሁሉ ማበርከት

  • የተለያዩ የልማት መርሀ ግብሮችን በመንደፍ ቤተ ክርስቲያንን በኢኮኖሚ ማበልጸግ

  • በቴክኖሎጂ ስልት የሚመራና አዋጭነቱ አስተማማኝ የሆነ የጠቅላላ ሀብት አስተዳደርና አጠቃቀም እንዲረጋገጥ ማድረግ

  • የሰው ልጆች ሁሉ እኩልነት፣ ሰላምና ፍትሕ፣ ፍቅርና ስምምነት እንዲጠበቅ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ

  • የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አሰራር ግልጽ፣ ለሁሉም ተደራሽና ችግር ፈቺ እንዲሆን ማድረግ

ዕሴቶች

  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅሊናን የሚረታ፣ አእምሮን የሚመሥጥ፣ ከጥንተ ፍጥረት ተነሥቶ በዘመነ አበው በሕገ ልቡና፣ በዘመነ ብሉይ በሕግ ኦሪት፣ ተራምዶ መዳረሻውን ሕገ ወንጌል ያደረገ ጥንታዊ ክርስቶሳዊና ሐዋርያዊ ትምህርተ ሃይማኖት፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን፣ በያሬዳዊ ጣዕመ ዜማ የታጀበ ሥርዐተ አምልኮ፣ በጽሑፍና በትውልድ ቅብብሎሽ የተወረሰ የረጅም ጊዜ ትውፊት ባህልና ታሪክ

  • በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የበለጸገ፣ እግዚአብሔርን የሚወድና የሚፈራ ለእግዚአብሔር የሚታዘዝና ምክረ ካህን የሚቀበል ከስልሳ ሚልዮን በላይ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ

  • ለምጣኔ ሃብት ዕድገት እጅግ የምትጠቅም በውብ ሥነ ተፈጥሮና በሥነ ጽሑፍ፣ በሥነ ጥበብና በኪነ ጥበብ፣ በታሪክና በቅርስ ሃብት የበለጸገች እንዲሁም በሃይማኖት፣ በነጻነትና በአንድነት የደመቀች ሃገር

  • የእግዚአብሔርን ቃል ከሃገር ውስጥ ባሻገር ለመላው ዓለም ማዳረስ የሚችሉ ከግማሽ ሚልዮን ያላነሱ ሊቃውንት፣ ቀሳውስት፣ ዲያቆናት፣ ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ከሁለት ሺሕ ያላነሱ ገዳማት

  • መላውን ዓለም እያዳረሰና እየሰፋ የሚገኝ ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ የተዋቀረ ጠንካራ መዋቅር ያላት መሆኗ

ያግኙን

+251 111 55 0098 P.O.Box 1283 A.A. 5 KILLO, ADDIS ABABA, ETHIOPIA በፌስቡክ ያግኙን የዩትዩብ ቻነል