የቦታው ስም ቀራንዮ ነው
የ2018 ዓ.ም. መስቀል በዓል ልዩ እትም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በሊቃውንት ጉባኤ ታይቶና ተመርምሮ፤ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተዘጋጀ
የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ቤት ተከበረ
ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ቅዳሴ ቤቱ ሲከበር ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፤ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ […]
ደንበኛ ተኮር ስርዓት የወለደው የነዋሪዎች አንድነት ከድርጅቱ አልፎ ከጠቅላይ ጽ/ቤቱ ጋርም እያስተሳሰረ መሆኑ ተገለጸ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት የተጀመረው ደንበኛ ተኮር ስርዓት ደንበኞችን ከድርጅቱ ጋር ከማቆራኘት አልፎ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጋር መናበብን የፈጠረ ሲሆን ይህንኑ በሚገልጽና ተባባሪነትን በሚያሳይ መልኩ በዛሬው እለት የጽዳት ዘመቻ አካሂዷል። የጽዳት ዘመቻው ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት […]
በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ቡራኬ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ተከናወነ
ግንቦት ፲፭ ቀን ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም በቡራኬ ቤተክርስቲያን መርሐ ግብሩ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙኀን ድርጅት የበላይ ሓላፊ የሰሜንና ምሥራቅ አፍሪካ […]
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ለሰዋሰው ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለአገልግሎት የሚሆን ፕራዶ መኪና ገዝቶ በስጦታ አበረከተ
ግንቦት ፲፫ ቀን ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የመኪናውን ቁልፍ ለብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል የሸካ ቤንች ማጂ እና የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሊቀ ጳጳስ የበላይ ኃላፊ አበርክተዋል፡፡ ቅዱስነታቸው በርክክቡ ወቅት እንደተናገሩት “ሥራ የሚሠራ ሰው ዋጋ ይገባዋል፡፡ ለአገልግሎት የሚሆን መኪና አስፈላጊ […]
ክፍል ሁለት …..” ከግንቦት እስከ ግንቦት ” እንደሚከተለው ይቀርባል
ባለፈው “ከግንቦት እስከ ግንቦት” ዝግጅታችን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ እና በብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ዘመነ ሢመት የተከናወኑ ዋናዋና ሥራዎችን በመጠኑ የዳሰስንበትን ዘገባ ለንባብ ማቅረባችን ይታወሳል።ቀጣዩን ክፍል እንደሚከተለው እናቀርባለን፦ 7.ኛ ቤተክርስቲያን በመጪው ዘመን መንፈሳዊ አገልግሎቷን ለማሳለጥ፣ ቀደምት አባቶቻችን ጥለውልን በሄዱት ይዞታዎች ላይ ለመጪው ትውልድ የሚተላለፍ ቅርስ ሠርታ ለማስተላለፍ እንዲሁም በከተማችን የሚስተዋለውን የመኖሪያ ቤት እጥረትን ለመቅረፍና በከተማችን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ […]
የለገጣፎ ደብረ ብፁዓን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣ አቡነ ሀብተ ማርያም እና አቡነ ሐራ ድንግል ዘመናዊ የፀበል ቤት በብፁዕ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ተባርኮ ተመረቀ
ግንቦት 10 ቀን 2018 ዓ.ም በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት፣ በለገጣፎ ለገዳዲ እና ኩራ ጂዳ ክፍለ ከተማ ሥር የሚገኘው የደብረ ብፁዓን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣ አቡነ ሀብተ ማርያም ወአቡነ ሐራ ድንግል በዘመናዊ መልክ ያስገነባው የፀበል ቤት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ […]
በአዶላ ወዩ በሚገኙ አድባራት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ክፍል ለሚማሩ ደቀመዛሙርት አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ተሰጠ
ግንቦት 10ቀን 2018ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በኩል ተዘጋጅቶ በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት፣ በብፁዕ አቡነ ዜናማርቆስ የጉጂ ቦረና ሊበን እና የምዕራብ አርሲ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መመሪያ መሠረት በሁለቱም አኅጉረ ስብከቶች ተግባራዊ እየሆነ መሆኑ ተገልጿል። በግንቦት 09 ቀን 2018 ዓ.ም በአዶላ ወዩ ለሚገኙ አድባራት […]
የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ከማኅበረ ቅዱሳን ወሊሶ ማዕከል ጋር በመተባበር በአፋን ኦሮሞ የሚያገለግሉ 15 ተተኪ መምህራንን አስመረቀ
ግንቦት 09 2018 ዓ/ም ዛሬ የተመረቁት ተተኪ መምህራን ለ፫ ወራት ግብረ ዲቁና ፣ኪዳን ፣ ሊጦን ፣ መስተበቁዕ ፣ መልክዓ ሥዕል ፣ መልክዓ ቁርባን ፣ መልክዓ ውዳሴ ፣ መልክዓ ማርያም ፣ መልከዓ ኢየሱስ በአፋን ኦሮሞ እንዲሁም ነገረ ሃይማኖታዊ ፣ የቤተክርስቲያን ታሪክ ፣ የስብከት ዘዴ ፣ ሐዋሪያዊ ተልዕኮ ፣ ነገረ ቅዱሳን ክርስቲያናዊ ሥነ-ምግባር እና ሥርዓተ ቤተክርስቲያን ኮርሶችን […]
በሸገር ሀገረ ስብከት የዓለምገና ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የስብከተ ወንጌል አዳራሽ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ተመረቀ
ግንቦት 09 2018 ዓ/ም በመርሐ ግብሩ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ […]
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቅጣጫ ሰጪነት እየታደሰ የሚገኘውን ዕድሜ ጠገቡን የወንጪ ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም ጎበኙ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ካሏት፣ ጥንታዊና ታሪካዊ ገዳም አንዱ በምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት የሚገኘው ወንጪ ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም ነው። ገዳሙ በ14ኛው ክፍለ ዘመን የተመሠረተ በወንጪ ሐይቅ ደሴት ላይ የሚገኝ ጥንታዊና ታሪካዊ ገዳም ነው። ገዳሙ ከ800 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረ ሲሆን፥ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አቅጣጫ ሰጪነት እየታደሰ የሚገኝ በመሆኑ ገዳሙ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ጎብኚዎችን […]