የቦታው ስም ቀራንዮ ነው

የ2018 ዓ.ም. መስቀል በዓል ልዩ እትም

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በሊቃውንት ጉባኤ ታይቶና ተመርምሮ፤ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተዘጋጀ

ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች

የ፳፻ ፲ወ፰ ዓ/ም የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የጸሎት መርሐ ግብር በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተከናወነ

ሚያዚያ ፳፯ ቀን ፳፻፲ወ፰ ዓ/ም አዲስአበባ -ኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የ፳፻ ፲ወ፰ ዓ/ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የመክፈቻ ጸሎት መርሐ ግብር በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተከናወነ። በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በተከናወነው የጸሎት ሥነ-ሥርዓት ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ […]

የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም 76ኛ ዓመት ቅዳሴ ቤት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በድምቀት ተከበሮ ዋለ

ሚያዝያ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በየዓመቱ ሚያዚያ 27 ቀን በዓመት እንድ ግዜ ብቻ ታቦተ ሕጉ ወጥቶ በአውደ ምሕረት ምዕመናን የሚባርክበት ዕለት እና የኢትዮጵያ የነጻነት በዓል በምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም በድምቀት ተከብሮ ውሏል ። በበዓሉ ላይም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የመንበረ ፓትርያርክ ዋና ስራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ […]

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ለምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም የ76ኛ ዓመት ቅዳሴ ቤት እና በጀግኖች አባቶቻችን ለተገኘው 85ኛው የኢትዮጵያ የድል በዓል ያስተላለፉት መልዕክት

ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን — በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን አሰሮ ለሰይጣን — አግአዞ ለአዳም ሰላም — እምይእዜሰ ኮነ — ፍሥሐ ወሰላም ​”ኢትዮጵያ ታበጽሕ እደዊሃ ኀበ እግዚአብሔር” “ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች ” መዝ. 68፡31 • ​ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ • ​የጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመመሪያ ኃላፊዎች፤ • ​የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የመመሪያ ኃላፊዎች፤ • […]

በምሁር ኢየሱስ ገዳም የአዲሱን ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ቡራኬን ተከትሎ ሲከበር የነበረው በዓል ተጠናቀቀ

ሚያዚያ ፳፭ ቀን ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም በታላቁ አባት በአቡነ ዜና ማርቆስ የተገደመው የምሁር ኢየሱስ ገዳም ሚያዚያ ፳፬ ቀን በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፀሎተ ቡራኬ ታቦታቱ ከነበሩበት መቃኞ ቤተ ክርስቲያን ወጥተው ወደ አዲሱ ሕንጻ ቤተ ክርስታያን መግባታቸው ይታወሳል።በዓሉ በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ የዋለ ሲሆን በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ታቦታቱ ታጅበው ወጥተው በልዩ ድምቀት እየተከበረ ይገኛል። በዕለቱ የሕንጻ ሥራውን […]

ታሪካዊው የምሁር ኢየሱስ ገዳም አዲሱ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤት ተከበረ

ሚያዚያ ፳፬ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም የምሁር ኢየሱስ ገዳም በጉራጌ ዞን፣ በምሁር አክሊል ወረዳ የሚገኝ ከአዲስ አበባ በ207 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ሲሆን ጥንታዊና ታሪካዊ ገዳም ነው። ገዳሙ የተመሰረተው በ14ኛው ክፍለ ዘመን በታላቁ አባት በአቡነ ዜና ማርቆስ እንደሆነ የገዳሙ ታሪክ ይነግረናል። ገዳሙ የከፍተኛ መንፈሳዊ ትምህርት ማዕከል በመሆን፣ጥንታዊና ብርቅዬ የብራና መጻሕፍትና ንዋያተ ቅድሳትን ጠብቆ በማቆየት፣እንዲሁም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ […]

በሸገር ሀገረ ስብከት የኮዬ ገላን ክፍለ ከተማ ደንጎራ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ሕንጻ የቤተክርስቲያን በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ቅዳሴ ቤቱ ከበረ

ሚያዚያ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓም በተካሄደው የሕንጻ ቤተክርስቲያን ምርቃት ሥነ ሥርዐት ላይ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንደተናገሩት “እንኳን ደስ አላችሁ፣ ስትደክሙበት ለነበረው ሥራችሁ ለፍጻሜ በቅቷል።” ብለዋል። ብፁዕነታቸው አክለውም “የድካማችሁን ፍሬና የሥራችንን ውጤት ለማየት ያበቃን አምላካችን እግዚአብሔር ክብር […]

በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት በሰበታ ገላን ጉዳና ፉሪ የዓለም ገና ደብረ ቀርሜሎስ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ተባረከ

ሚያዝያ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት በሰበታ ገላን ጉዳና ፉሪ ክፍላተ ከተማ ቤተክህነት የዓለም ገና ደብረ ቀርሜሎስ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ሕንጻ ቤተክርስቲያን ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም የበላይ ኃላፊ ፣ ብፁዕ […]

“የአበው ሥርዓት ለቤተ ክርስቲያን አንድነት” በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የቆየውን የገዳማት አበምኔቶችና እመምኔቶች አገር አቀፍ ጉባኤ ተጠናቀቀ

ሚያዚያ ፳፫ ቀን ፳፻፲ወ፰ዓ.ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የገዳማት አስተዳደር መምሪያ ባዘጋጀው መርሐ ግብር፤ ከመላው ኢትዮጵያ የአንድነት ገዳማት ለተውጣጡ አበምኔቶች እና እመምኔቶች “የአበው ሥርዓት ለቤተ ክርስቲያን አንድነት” በሚል ርዕስ ሲሰጥ የነበረው የሥልጠና እና የምክክር ጉባኤ ፍጻሜውን አግኝቷል። ከሚያዝያ ፳፪ እስከ ሚያዚያ ፳፫ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም ድረስ ለሁለት ተከታታይ ቀናት […]

በፌስቡክ ያግኙን

የኅትመትና ሚዲያ ዋና ክፍል

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ

የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ

የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ልማት በቤተ ክርስቲያን

ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።

ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን

ርእይ

ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት

ተልእኮ

  • የእግዚአብሔርን ቃል ለሰው ልጆች ሁሉ ማስተማርና ማዳረስ

  • ሰውን በሁለንተናዊ ሰብእናው ማገልገልና ማዳን

  • ሰውን ሁሉ በነገረ መለኮትና በነገረ ጥበብ ትምህርት በማልማት በመንፈሳዊም ሆነ በሥጋዊ ሕይወቱ የተሻለ ኑሮ እንዲኖረው ማድረግ

  • ጥራትና ብቃት፣ ፍትሐዊነትና እኩል ተደራሽነት ያለው መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ለሰው ሁሉ ማበርከት

  • የተለያዩ የልማት መርሀ ግብሮችን በመንደፍ ቤተ ክርስቲያንን በኢኮኖሚ ማበልጸግ

  • በቴክኖሎጂ ስልት የሚመራና አዋጭነቱ አስተማማኝ የሆነ የጠቅላላ ሀብት አስተዳደርና አጠቃቀም እንዲረጋገጥ ማድረግ

  • የሰው ልጆች ሁሉ እኩልነት፣ ሰላምና ፍትሕ፣ ፍቅርና ስምምነት እንዲጠበቅ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ

  • የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አሰራር ግልጽ፣ ለሁሉም ተደራሽና ችግር ፈቺ እንዲሆን ማድረግ

ዕሴቶች

  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅሊናን የሚረታ፣ አእምሮን የሚመሥጥ፣ ከጥንተ ፍጥረት ተነሥቶ በዘመነ አበው በሕገ ልቡና፣ በዘመነ ብሉይ በሕግ ኦሪት፣ ተራምዶ መዳረሻውን ሕገ ወንጌል ያደረገ ጥንታዊ ክርስቶሳዊና ሐዋርያዊ ትምህርተ ሃይማኖት፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን፣ በያሬዳዊ ጣዕመ ዜማ የታጀበ ሥርዐተ አምልኮ፣ በጽሑፍና በትውልድ ቅብብሎሽ የተወረሰ የረጅም ጊዜ ትውፊት ባህልና ታሪክ

  • በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የበለጸገ፣ እግዚአብሔርን የሚወድና የሚፈራ ለእግዚአብሔር የሚታዘዝና ምክረ ካህን የሚቀበል ከስልሳ ሚልዮን በላይ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ

  • ለምጣኔ ሃብት ዕድገት እጅግ የምትጠቅም በውብ ሥነ ተፈጥሮና በሥነ ጽሑፍ፣ በሥነ ጥበብና በኪነ ጥበብ፣ በታሪክና በቅርስ ሃብት የበለጸገች እንዲሁም በሃይማኖት፣ በነጻነትና በአንድነት የደመቀች ሃገር

  • የእግዚአብሔርን ቃል ከሃገር ውስጥ ባሻገር ለመላው ዓለም ማዳረስ የሚችሉ ከግማሽ ሚልዮን ያላነሱ ሊቃውንት፣ ቀሳውስት፣ ዲያቆናት፣ ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ከሁለት ሺሕ ያላነሱ ገዳማት

  • መላውን ዓለም እያዳረሰና እየሰፋ የሚገኝ ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ የተዋቀረ ጠንካራ መዋቅር ያላት መሆኗ

ያግኙን

+251 111 55 0098 P.O.Box 1283 A.A. 5 KILLO, ADDIS ABABA, ETHIOPIA በፌስቡክ ያግኙን የዩትዩብ ቻነል የቴሌግራም ቻነል