የቦታው ስም ቀራንዮ ነው
የ2018 ዓ.ም. መስቀል በዓል ልዩ እትም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በሊቃውንት ጉባኤ ታይቶና ተመርምሮ፤ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተዘጋጀ
የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
ለዘመናት የቤተክርስቲያንን ተልእኮ በማሳለጥ የሚታወቀው የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ በበጀት ዓመቱ ለሦስተኛ ጊዜ ዐቢይ ጉባኤ አካሄደ
ሚያዚያ ፲፱ ቀን ፳፻፲ወ፰ዓ.ም. ኢኦተቤክ ሕዝብግንኙነት አዲስአበባ ኢትዮጵያ 👉 እስከ ምድር ዳርቻ ምስክሮች ሊሆኑ ለተጠሩት ለቅዱሳን ሐዋርያት በመጀመሪያ የታወጀው አዋጅ የማይሻር፣ ለዘለዓለም ጸንቶ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተላለፈ ያለና ሲተላለፍ የሚኖር ሕያው ቃል በመሆኑ ብርሃናተ ዓለም ሐዋርያት፣ ሰባ ሁለቱ አርድዕት የስብከታቸውን ማዕከል ክርስቶስንና የአዳኝነቱን ሥራ በማድረግ አስዋከ ረሲዓንን እየነቀሉ፣ የወንጌልን ምርጥ ዘር በምዕመናን የልቡና ማሳ ላይ […]
በበርካቶች ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ድረ-ገጽ አገልግሎት ጀመረ
ሚያዚያ ፲፭ ቀን ፳፻፲ወ፰ዓ.ም. ኢኦተቤክ ቤሕአልድ አዲስአበባ ኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለዘመናት በመኳንንት፣ በወይዛይርትና በግለሰቦች አማካኝነት በውርስ፣ በኑዛዜና በስጦታ መልክ የተሰጧትንና በይዞታ አስከብራ ያቆየቻቸውን ቤቶች፣ ሕንፃዎችና ይዞታዎች ረጅም ዘመናት በድርጅቱ ባሳለፉ ቅን የድርጅቱ ሠራተኞች አእምሮ ከመያዝ ባሻገር የሚመለከታቸው ሁሉ እንዲያውቁት በሚስችል መልኩ ተሰንዶ አለመቀመጡ ድርጅቱ በሥሩ የሚገኙ ደንበኞችን በአግባቡ ለማስተዳደር የሚቸገር ከመሆኑም በላይ የሚባክኑ […]
ኋላ ቀር የገንዘብ አስተዳደርን በማዘመን የደንበኞችን ውጣ ውረድ የማስቀረት ዓላማን ያነገበው የሞባይል ባንኪንግ አገልግልግሎት በይፋ ተመርቆ ተግባራዊ ተደረገ
ሚያዚያ ፲፭ ቀን ፳፻፲ወ፰ዓ.ም. ኢኦተቤክ ቤሕአልድ አዲስአበባ ኢትዮጵያ የቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ይዞት የተነሳውን የደንበኛ ተኮር አስተዳደር ስርዓት አካል የሆነው የዘመናዊ ገንዘብ አስተዳደር ቴክኖሎጂ ማበልጸግ ተግባራዊ ለማድረግ ከበርካታ ባንኮች ፣ ድርጅቶችና ኤጀንትቶች አማራጭ መንገዶችን ለማየት ተደጋጋሚ ውይይቶችን ማድረጉን መዘጋባችን የሚታወስ ነው። የቀረቡት አማራጮች ሙሉ በሚባል ደረጃ የሚያጓጉ ቢሆኑም ድርጅቱ ጥበብ በተሞላው ምርጫ በመምረጥ ከዐባይ […]
ቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ይዞት የተነሳውን ደንበኛ ተኮር ስርዓት ተፈጻሚ ለማድርግ የመጀመሪያውን ምዕራፍ አጠናቆ በዛሬው እለት በይፋ አስመረቀ
ሚያዚያ ፲፭ ቀን ፳፻፲ወ፰ዓ.ም. ኢኦተቤክ ቤሕአልድ አዲስአበባ ኢትዮጵያ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የሸገር ከተማና የደቡብ ምዕራብ ሸዋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም የበላይ ኀላፊ በሚመሩበት በሳልና አባታዊ የአመራር ጥበብ ካደረጉት ሥራና ሠራተኛን የማገናኘት ሥራ አካል የሆነው የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት በሚፈለገው ልክ ራሱ እየለወጠ […]
የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዕድሳት የደረሰበትን አሁናዊ ሁኔታ በተመለከተ ለቅዱስ ፓትርያርኩ እና ለብፁዓን አባቶች መግለጫ ቀረበ
ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዕድሳት አስመልክቶ በተሰጠው መግለጫ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘኣክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮሰ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አሀጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱሰ ሲኖዶስ ዋና […]
ለፉት አራት ቀናት በኬንያ ንይሮቢ በሐዋርያዊ አገልግሎት ላይ የሰነበቱት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስና ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል
ሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስአበባ -ኢትዮጵያ በኬንያ ናይሮቢ ሐዋርያዊ አገልግሎት ሲያከናውኑ የሰነበቱ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዛሬ አመሻሹ ላይ አዲስ አበባ ገብተዋል። ሁለቱ ብፁዓን አባቶች ሚያዚያ 9ቀን […]
ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ እና ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ በኬንያ ናይሮቢ የኢትዮጵያ ኤምባሲን ጎበኙ
ሚያዚያ 11ቀን2018ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም በናይሮቢ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጉብኝት አደረጉ። በጉብኝቱ ወቅት የሚሲዮኑ ዲፕሎማቶች እና ሠራተኞች […]
ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው ለሐዋርያዊ አገልግሎት ወደ ኬንያ ናይሮቢ ተጓዙ
ሚያዚያ 9ቀን 2018 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለአራት ቀናት ሐዋርያዊ አገልግሎት ወደ ኬንያ ናይሮቢ ተጉዘዋል። ሁለቱ ብፁዓን አባቶቻችን ናይሮቢ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የናይሮቢ ደብረ መድኀኒት መድሃኔዓለም ቤተክርስቲያን ካህናት፣ምዕመናንና ወጣት […]
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የብዝኃ ሕይወት ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል ጥረቷን ለማጠናከር ከአጋር ድርጅቶች ጋር እየመከረች ነው
ሚያዝያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የልማትና ክርስቲያዊ ተራድኦ ኮሚሽን ( EOTCVDICAC) ቤተክርስቲያኗ ለዘመናት ጠብቃ ያቆየችውን የብዝኃ ሕይወት ሀብት በዘላቂነት ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍና የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የምታደርገውን አስተዋጽኦ ይበልጥ ለማሳደግ ዛሬ ከአጋር ድርጅቶች ጋር የምክክር መድረክ አካሄዳለች ። በውይይቱ ላይ ኮሚሽነር ይልቃል ሽፈራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የልማትና ክርስቲያዊ ተራድኦ ኮሚሽን […]
የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ እንኳን አደረሰዎ መርሐግብር በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሐፈት ቤት በደማቅ መንፈሳዊ ስነስርዓት ተካሄደ
ሚያዚያ ፭ ቀን ፪፻ ፲ወ፰ዓ.ም. ኢኦተቤክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አዲስአበባ , ኢትዮጵያ በየዓመቱ በትንሣኤ ማግስት ፣ በአዲስ ዓመት ማግስትና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ማግስት ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት ጀምሮ እስከ አዲስአበባ ሀገረ ስብከት አድባራትና ገዳማት አገልጋዮች በመሰባሰብ ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የእንኳን አደረሰዎ መርሐግብር ይካሄዳል። በዚሁ መሠረት የዘንድሮ የ2018ዓ.ም የትንሣኤ በዓል ምክንያት በማድረግ […]