የቦታው ስም ቀራንዮ ነው

የ2018 ዓ.ም. መስቀል በዓል ልዩ እትም

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በሊቃውንት ጉባኤ ታይቶና ተመርምሮ፤ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተዘጋጀ

ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በ2018 ዓ.ም የትንሣኤ በዓል የእንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር ላይ ያስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል

“ወይእዜሰ በክርስቶስ ተሐድሰ ኵሉ ወኃለፈ ዘትካት ወናሁ ኮነ ሐዲስ ኵሉ … ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፏል እነሆ ሁሉም አዲስ ሆኗል” (2.ቆሮ 5÷17) ❖ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤ ❖ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት […]

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንና ዳሽን ባንክ አከሰስዮን ማኅበር ሦስት መቶ ለሚሆኑ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ምዕመናን የበዓል መዋያ ድጋፍ አደረጉ

ሚያዚያ፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፰ ዓ.ም አዲስአበባ -ኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ገቅላይ ጽሕፈት ቤት ከዳሽን ባንክ አክስዮን ማኅበር ጋር በመተባበር ሦስት መቶ ለሚሆኑ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ምዕመናን የ፳፻ ፲ወ፰ ዓ.ም የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለእያንዳንዳቸው አምስት ሌትር ዘይትና አሥር ኪሎ ዱቄት በዛሬው ዕለት በጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት ቅጽር ጊቢ በተከናወነ የልገሳ […]

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣የጌታችን የአምላካችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሣኤን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ

የቅዱስነታቸው አባታዊ መልዕክት እንደሚከተለው ይነበባል። ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ ኣቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዓሠርቱ ወሰምንቱ ዓመተ ምሕረት፤ በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሐዱ ኣምላክ ኣሜን፡- በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር […]

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ከጠቅላይ ቤተክህነት ዙሪያ በልማት ምክንያት ለተነሱ ምዕመናን የበዓል መዋያ ድጋፍ አደረጉ

ሚያዚያ፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፰ ዓ.ም አዲስአበባ -ኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ገቅላይ ጽሕፈት ቤት ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አካባቢ በልማት ምክንያት ተነስተው በልደታና በፒያሳ አካባቢ ወደ ተሰራላቸው ቤት ለገቡ ምዕመናን የ፳፻ ፲ወ፰ ዓ.ም የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለእያንዳንዳቸው አምስት ሌትር ዘይትና አሥር ኪሎ ዱቄት በመስጠት እንኳን አደረሳችሁ በማለት ድጋፍ አድርገዋል። በዚሁ ጊዜ […]

ብፁዓን አባቶች በጥቁር አንበሳ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በመገኘት ሕሙማንን ጎበኙ

መጋቢት 30/7/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የትንሳኤ በዓልን በማስመልከት በጥቁር አንበሳ እስፔሻላይዝድ ኦስፒታል በመገኘት በእመም ላይ ያሉ ሕሙማንን ጎብኝተው ማዕድ አጋሩ፣የቁሳቁስና የገንዘብ ድጋፋ አደረጉ። ጉብኝቱ የተካሄደው የትንሳኤ […]

የጌታችን የአምላካችን የመድኃኔዓለም ጥንተ ስቅለት በዓል በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት በከታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል በታላቅ ድምቀት ተከበረ፡

መጋቢት 27 ቀን 2018 ዓ.ም በየዓመቱ መጋቢት 27 ቀን የሚከበረውን የመድኃኔዓለም ጥንተ ስቅለት በዓል በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት በከታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል በታላቅ ድምቀት የተከበረ ሲሆን በበዓሉ ላይ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ መጋቤ ሐዲስ ለማ በየነ የኦሮምኛ […]

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት የቢሮ ዕድሳት ሥራ ያለበትን ደረጃ ተመለከቱ

መጋቢት 20ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ -ኢትዮጵያ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት የሚያከናውነውን የቢሮ ዕድሳት ሥራ አፈጻጸምን ከጠቅላይ ቤተክህነት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን ዛሬ ረፋዱ ላይ ተዘዋውረው ተመለከቱ። ብፅዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ድርጁቱ የሚያከናውነው […]

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሳዊሮስ ሥልጠና በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ከትናት በተሻለ መልኩ ለመሥራት በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑን ገለጹ

መጋቢት ፲፯ / ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሳዊሮስ ሥልጠና በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ከትናት በተሻለ መልኩ ለመሥራት በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑን ገለጹ። ብፁዕነታቸው ይህንን የይህንን ያሉት በዛሬው ዕለት የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የስብከተ ወንጌል ክፍልና የሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ ክፍል በጋራ ባዘጋጁት የአንድ ቀን ሥልጠና ላይ ነው። በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ […]

ትዕግስት፣ብልሀት፣የመንፈሳዊና አስተዳደራዊ የአመራር ብቃት፣ባለፉት ስምንት ወራት በጠቅላይ ቤተክህነት።

……ካለፈው የቀጠለ፦

በፌስቡክ ያግኙን

የኅትመትና ሚዲያ ዋና ክፍል

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ

የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ

የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ልማት በቤተ ክርስቲያን

ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።

ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን

ርእይ

ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት

ተልእኮ

  • የእግዚአብሔርን ቃል ለሰው ልጆች ሁሉ ማስተማርና ማዳረስ

  • ሰውን በሁለንተናዊ ሰብእናው ማገልገልና ማዳን

  • ሰውን ሁሉ በነገረ መለኮትና በነገረ ጥበብ ትምህርት በማልማት በመንፈሳዊም ሆነ በሥጋዊ ሕይወቱ የተሻለ ኑሮ እንዲኖረው ማድረግ

  • ጥራትና ብቃት፣ ፍትሐዊነትና እኩል ተደራሽነት ያለው መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ለሰው ሁሉ ማበርከት

  • የተለያዩ የልማት መርሀ ግብሮችን በመንደፍ ቤተ ክርስቲያንን በኢኮኖሚ ማበልጸግ

  • በቴክኖሎጂ ስልት የሚመራና አዋጭነቱ አስተማማኝ የሆነ የጠቅላላ ሀብት አስተዳደርና አጠቃቀም እንዲረጋገጥ ማድረግ

  • የሰው ልጆች ሁሉ እኩልነት፣ ሰላምና ፍትሕ፣ ፍቅርና ስምምነት እንዲጠበቅ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ

  • የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አሰራር ግልጽ፣ ለሁሉም ተደራሽና ችግር ፈቺ እንዲሆን ማድረግ

ዕሴቶች

  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅሊናን የሚረታ፣ አእምሮን የሚመሥጥ፣ ከጥንተ ፍጥረት ተነሥቶ በዘመነ አበው በሕገ ልቡና፣ በዘመነ ብሉይ በሕግ ኦሪት፣ ተራምዶ መዳረሻውን ሕገ ወንጌል ያደረገ ጥንታዊ ክርስቶሳዊና ሐዋርያዊ ትምህርተ ሃይማኖት፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን፣ በያሬዳዊ ጣዕመ ዜማ የታጀበ ሥርዐተ አምልኮ፣ በጽሑፍና በትውልድ ቅብብሎሽ የተወረሰ የረጅም ጊዜ ትውፊት ባህልና ታሪክ

  • በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የበለጸገ፣ እግዚአብሔርን የሚወድና የሚፈራ ለእግዚአብሔር የሚታዘዝና ምክረ ካህን የሚቀበል ከስልሳ ሚልዮን በላይ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ

  • ለምጣኔ ሃብት ዕድገት እጅግ የምትጠቅም በውብ ሥነ ተፈጥሮና በሥነ ጽሑፍ፣ በሥነ ጥበብና በኪነ ጥበብ፣ በታሪክና በቅርስ ሃብት የበለጸገች እንዲሁም በሃይማኖት፣ በነጻነትና በአንድነት የደመቀች ሃገር

  • የእግዚአብሔርን ቃል ከሃገር ውስጥ ባሻገር ለመላው ዓለም ማዳረስ የሚችሉ ከግማሽ ሚልዮን ያላነሱ ሊቃውንት፣ ቀሳውስት፣ ዲያቆናት፣ ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ከሁለት ሺሕ ያላነሱ ገዳማት

  • መላውን ዓለም እያዳረሰና እየሰፋ የሚገኝ ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ የተዋቀረ ጠንካራ መዋቅር ያላት መሆኗ

ያግኙን

+251 111 55 0098 P.O.Box 1283 A.A. 5 KILLO, ADDIS ABABA, ETHIOPIA በፌስቡክ ያግኙን የዩትዩብ ቻነል የቴሌግራም ቻነል