በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም
በሸገር ሀገረ ስብከት በስሉልታና መነአብቹ ክፍላተ ከተማ በአትሌት ፕሮጀክት መንደር የተገነባ የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል፣ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ እና ልደታ ለማርያም አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በዛሬ ዕለት ግንቦት 19/2018 ዓ/ም በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የምስካየ ሕዙናን መድኃኔዓለም ገዳም የበላይ ጠባቂ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተባርኮ ተመርቋል።©Eotc tv