የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ትርጓሜ ምስክር ት/ቤት በባሕር ዳር ከተማ ለሚያስገነባው “የሕክምና መንደር” የመሠረት ድንጋይ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተቀመጠ።
ሰኔ ፲፱ቀን ፳፲፰ ዓ.ምየገዳሙ ጉባኤ ቤት “ሰንፔር” ሲል ለሰየመው “የሕክምና መንደር” ግንባታ 30,000 ካሬ ቦታ ከባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ሰኔ ፲፱ቀን ፳፲፰ ዓ.ም መረከቡም ይታወቃል።
“የሕክምና መንደሩ” የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥ መርሐ ግብር ላይ እንደተገለፀው የሕክምና መንደሩ ዋና ዓላማ ለሁሉም የሰው ልጆች በምሕረት፡ እምነትን፣ ዘርንና ማንነትን ሳይለይ፣ ለሰው ልጅ ሁሉ የሚታዘንበት የምሕረት ማረፊያ እንዲሆንና ሁለንተናዊ ፈውስ ለመስጠት ነው ተብሏል።
ከዚህ በመለስ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በሀገራችን የነበራትን የጥበብ ታሪክ በዘመናዊ የምርምር ዐቅም ለማስቀጠል “የሕክምና መንደሩ” ከፍ ያለ ሚና እንደሚኖረው ተገልጿል።
ሌላው ቤተ ጉባኤው “የሕክምና መንደር” የሚያስገነባው የቅድመ ጋብቻ ትምህርት ለመስጠት የባለትዳሮች ደግሞ የልጅ አስተዳደግ ሥልጠና ለመስጠት እንዲሁም በሱስ የተጎዱ ወገኖቻችንን ለመንከባከብና እንደገና አዲስ ሰውነት እንዲያገኙ በማድረግ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለሀገራችን በጎና ባለ አእምሮ ትውልድ ለመፍጠር መሆኑን ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶች እና የእናቶች አንድነት ገዳም የ ፬ቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምስክር መምህር ተናግረዋል።
ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን አክለውም “የሕክምና መንደሩ” ሀገር በቀል የሕክምና ማዕከል እንዲሁም የሕክምና ኮሌጅና የምርምር ማዕከል ያካተተ ይሆናልም ብለዋል።
የሕክምና መንደሩ ወደ መሬት እንዲወርድ ለተባበሩት ሁሉ ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ “የጉባኤ አምላክ ይጠብቅልን” ሲሉ አመስግነዋል።
“የሕክምና መንደሩ” መሠረት ድንጋይ የማስቀመጥ መርሐ ግብር ላይ ብፁዕ አቡነ አቡነ ሚካኤል የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የባሕር ዳር እና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዘካርያስ የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የስካንዲቪያን እና የኖርዲክ አገራት አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የሥራ ሓላፊዎች ፣ የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣ ካህናት አባቶች ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር የሥራ ሓላፊዎች ተገኝተዋል።የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ትርጓሜ ምስክር ት/ቤት በባሕር ዳር ከተማ ለሚያስገነባ “የሕክምና መንደር” የመሰረት ድንጋይ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተቀመጠ።
የገዳሙ ጉባኤ ቤት “ሰንፔር” ሲል ለሰየመው “የሕክምና መንደር” ግንባታ 30,000 ካሬ ቦታ ከባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ሰኔ ፲፱-፳፲፰ ዓ.ም መረከቡም ይታወቃል።
“የሕክምና መንደሩ” የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥ መርሐ ግብር ላይ እንደተገለፀው የሕክምና መንደሩ ዋና ዓላማ ለሁሉም የሰው ልጆች በምሕረት፡ እምነትን፣ ዘርንና ማንነትን ሳይለይ፣ ለሰው ልጅ ሁሉ የሚታዘንበት የምሕረት ማረፊያ እንዲሆንና ሁለንተናዊ ፈውስ ለመስጠት ነው ተብሏል።
ከዚህ በመለስ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በሀገራችን የነበራትን የጥበብ ታሪክ በዘመናዊ የምርምር ዐቅም ለማስቀጠል “የሕክምና መንደሩ” ከፍ ያለ ሚና እንደሚኖረው ተገልጿል።
ሌላው ቤተ ጉባኤው “የሕክምና መንደር” የሚያስገነባው የቅድመ ጋብቻ ትምህርት ለመስጠት የባለትዳሮች ደግሞ የልጅ አስተዳደግ ሥልጠና ለመስጠት እንዲሁም በሱስ የተጎዱ ወገኖቻችንን ለመንከባከብና እንደገና አዲስ ሰውነት እንዲያገኙ በማድረግ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለሀገራችን በጎና ባለ አእምሮ ትውልድ ለመፍጠር መሆኑን ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶች እና የእናቶች አንድነት ገዳም የ ፬ቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምስክር መምህር ተናግረዋል።
ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን አክለውም “የሕክምና መንደሩ” ሀገር በቀል የሕክምና ማዕከል እንዲሁም የሕክምና ኮሌጅና የምርምር ማዕከል ያካተተ ይሆናልም ብለዋል።
የሕክምና መንደሩ ወደ መሬት እንዲወርድ ለተባበሩት ሁሉ ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ “የጉባኤ አምላክ ይጠብቅልን” ሲሉ አመስግነዋል።
“የሕክምና መንደሩ” መሠረት ድንጋይ የማስቀመጥ መርሐ ግብር ላይ ብፁዕ አቡነ አቡነ ሚካኤል የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የባሕር ዳር እና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዘካርያስ የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የስካንዲቪያን እና የኖርዲክ አገራት አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የሥራ ሓላፊዎች ፣ የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣ ካህናት አባቶች ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር የሥራ ሓላፊዎች ተገኝተዋል።
የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት
©EOTC tv


የ40 ሀገራት አምባሳደሮች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ቅዱስ ላሊበላ ከተማ መግባታቸው ይታወቃል።
ሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም