የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ትርጓሜ ምስክር ት/ቤት በባሕር ዳር ከተማ ለሚያስገነባው “የሕክምና መንደር” የመሠረት ድንጋይ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተቀመጠ።

ሰኔ ፲፱ቀን ፳፲፰ ዓ.ም
የገዳሙ ጉባኤ ቤት “ሰንፔር” ሲል ለሰየመው “የሕክምና መንደር” ግንባታ 30,000 ካሬ ቦታ ከባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ሰኔ ፲፱ቀን ፳፲፰ ዓ.ም መረከቡም ይታወቃል።
“የሕክምና መንደሩ” የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥ መርሐ ግብር ላይ እንደተገለፀው የሕክምና መንደሩ ዋና ዓላማ ለሁሉም የሰው ልጆች በምሕረት፡ እምነትን፣ ዘርንና ማንነትን ሳይለይ፣ ለሰው ልጅ ሁሉ የሚታዘንበት የምሕረት ማረፊያ እንዲሆንና ሁለንተናዊ ፈውስ ለመስጠት ነው ተብሏል።
ከዚህ በመለስ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በሀገራችን የነበራትን የጥበብ ታሪክ በዘመናዊ የምርምር ዐቅም ለማስቀጠል “የሕክምና መንደሩ” ከፍ ያለ ሚና እንደሚኖረው ተገልጿል።
ሌላው ቤተ ጉባኤው “የሕክምና መንደር” የሚያስገነባው የቅድመ ጋብቻ ትምህርት ለመስጠት የባለትዳሮች ደግሞ የልጅ አስተዳደግ ሥልጠና ለመስጠት እንዲሁም በሱስ የተጎዱ ወገኖቻችንን ለመንከባከብና እንደገና አዲስ ሰውነት እንዲያገኙ በማድረግ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለሀገራችን በጎና ባለ አእምሮ ትውልድ ለመፍጠር መሆኑን ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶች እና የእናቶች አንድነት ገዳም የ ፬ቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምስክር መምህር ተናግረዋል።
ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን አክለውም “የሕክምና መንደሩ” ሀገር በቀል የሕክምና ማዕከል እንዲሁም የሕክምና ኮሌጅና የምርምር ማዕከል ያካተተ ይሆናልም ብለዋል።
የሕክምና መንደሩ ወደ መሬት እንዲወርድ ለተባበሩት ሁሉ ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ “የጉባኤ አምላክ ይጠብቅልን” ሲሉ አመስግነዋል።
“የሕክምና መንደሩ” መሠረት ድንጋይ የማስቀመጥ መርሐ ግብር ላይ ብፁዕ አቡነ አቡነ ሚካኤል የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የባሕር ዳር እና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዘካርያስ የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የስካንዲቪያን እና የኖርዲክ አገራት አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የሥራ ሓላፊዎች ፣ የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣ ካህናት አባቶች ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር የሥራ ሓላፊዎች ተገኝተዋል።የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ትርጓሜ ምስክር ት/ቤት በባሕር ዳር ከተማ ለሚያስገነባ “የሕክምና መንደር” የመሰረት ድንጋይ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተቀመጠ።
የገዳሙ ጉባኤ ቤት “ሰንፔር” ሲል ለሰየመው “የሕክምና መንደር” ግንባታ 30,000 ካሬ ቦታ ከባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ሰኔ ፲፱-፳፲፰ ዓ.ም መረከቡም ይታወቃል።
“የሕክምና መንደሩ” የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥ መርሐ ግብር ላይ እንደተገለፀው የሕክምና መንደሩ ዋና ዓላማ ለሁሉም የሰው ልጆች በምሕረት፡ እምነትን፣ ዘርንና ማንነትን ሳይለይ፣ ለሰው ልጅ ሁሉ የሚታዘንበት የምሕረት ማረፊያ እንዲሆንና ሁለንተናዊ ፈውስ ለመስጠት ነው ተብሏል።
ከዚህ በመለስ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በሀገራችን የነበራትን የጥበብ ታሪክ በዘመናዊ የምርምር ዐቅም ለማስቀጠል “የሕክምና መንደሩ” ከፍ ያለ ሚና እንደሚኖረው ተገልጿል።
ሌላው ቤተ ጉባኤው “የሕክምና መንደር” የሚያስገነባው የቅድመ ጋብቻ ትምህርት ለመስጠት የባለትዳሮች ደግሞ የልጅ አስተዳደግ ሥልጠና ለመስጠት እንዲሁም በሱስ የተጎዱ ወገኖቻችንን ለመንከባከብና እንደገና አዲስ ሰውነት እንዲያገኙ በማድረግ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለሀገራችን በጎና ባለ አእምሮ ትውልድ ለመፍጠር መሆኑን ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶች እና የእናቶች አንድነት ገዳም የ ፬ቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምስክር መምህር ተናግረዋል።
ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን አክለውም “የሕክምና መንደሩ” ሀገር በቀል የሕክምና ማዕከል እንዲሁም የሕክምና ኮሌጅና የምርምር ማዕከል ያካተተ ይሆናልም ብለዋል።
የሕክምና መንደሩ ወደ መሬት እንዲወርድ ለተባበሩት ሁሉ ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ “የጉባኤ አምላክ ይጠብቅልን” ሲሉ አመስግነዋል።
“የሕክምና መንደሩ” መሠረት ድንጋይ የማስቀመጥ መርሐ ግብር ላይ ብፁዕ አቡነ አቡነ ሚካኤል የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የባሕር ዳር እና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዘካርያስ የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የስካንዲቪያን እና የኖርዲክ አገራት አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የሥራ ሓላፊዎች ፣ የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣ ካህናት አባቶች ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር የሥራ ሓላፊዎች ተገኝተዋል።
የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት
©EOTC tv

የላሊበላ ቅርሶችን ለመጠበቅ የሚያስችል ውይይት ሊደረግ መሆኑ ተገለጸ።

የ40 ሀገራት አምባሳደሮች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ቅዱስ ላሊበላ ከተማ መግባታቸው ይታወቃል።
በዚህ ጉብኝት ከ800 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩትን ውቅር አብያተክርስቲያናት ድንቅ የታሪክና የጥበብ ሥራዎች ከመመልከት ባለፈ፣ ከቤተክርስቲያን አባቶችና ከአካባቢው ማኅበረሰብ ጋር ውይይት ይደረጋል ተብሎም ይጠበቃል።
እንደ ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ዘገባ ከሆነ ከ”ዘላቂ ላሊበላ ፕሮጀክት” ተወካዮች እንዲሁም ከፈረንሳይ ኤምባሲ ጋር በመሆን ቅርሶቹን ከተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ አደጋዎች ለመጠበቅ እንዲሁም በዘላቂ ልማት ዙሪያ ሰፊ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።
ቅዱስ ላሊበላ በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፋት በተጓዙ አካላት በተደረገ ጥናትና በዩሮኒውስ በተዘገበው መረጃ መሠረት፣ በዓለም ካሉ የዓለም ቅርስ መዳረሻዎች መካከል ቀዳሚ ከሆኑ አምስት ምርጥ መዳረሻዎች አንዱ ሆኖ መመረጡ ይታወሳል።
©የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (አይሲቲ) እና የዲጂታል ሽግግር አማካሪ ኮሚቴ ለአስተዳደር ጉባኤው በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ እየሠራ ያለውን የተለያዩ የጥናት ሰነዶች አቀረበ፡፡

ሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (አይሲቲ) እና ዲጂታል ሽግግር አማካሪ ኮሚቴ በዘመናዊ የዲጂታል ዓለም ውስጥ ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎቷን ተደራሽ ማድረግ የምትችልባቸውንና አስተዳደራዊ አቅሟን ለማሳደግ የሚረዱ ሙያዊ ምክረ ሐሳቦችንና ስልታዊ ጥናቶችን በማቅረብ እንዲሠራ የተቋቋመ ኮሚቴ ነው፡፡
የኮሚቴው ሰብሳቢ ቀሲስ ዮሐንስ ተስፋዬ ለአስተዳደር ጉባኤ ባቀረቡት ጥናት “ቤተክርስቲያን በቴክኖሎጂ የዳበረ ዘመናዊ የቤተክርስቲያን አስተዳደር ሥርዐትን ለመገንባት ከመንፈሳዊ እሴቶች ጋር የተጣጣመ፣ ደኅንነቱ የተጠበቀ ለቀጣይ ትውልድ አገልግሎት መስጠት የሚችል የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂን መጠቀም እንደሚያስፈልጋት አስረድተዋል፡፡
የዲጂታል ቴክኖሎጂ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤትክርስቲያን ስብከተ ወንጌል ለማስፋፋት፣ አስተዳደሯን ለማዘመን፣ የፋይናንስ ሥራዎቿን ለማቀላጠፍ፣ የቤተክርስቲያን ጥንታዊና ታሪካዊ ቅርሶቿን ለማስጠበቅና ለማስተዳደር ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መሆኑ በጥናቱ ተመላክቷል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስቀድሞ ለአገልግሎት ትጠቀምባቸው የነበሩ ሀርድ ኮፒዎች ዲጂታይዝ ለማድረግ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ (አይሲቲ) እና ዲጂታል ሽግግር አማካሪ ስትራቴጂክ ሰነድ መዘጋጀቱን ሰብሳቢው ገልጸዋል።
ቤተክርስቲያን ለዘመናት የቆዩ የብራና መጻሕፍት፣ የቅኔ፣ የያሬዳዊ ዜማዎችና የቅዱሳት ሥዕላት ባለቤት መሆኖከአጥቢያ እስከ መንበረ ፓትርያርክ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ካህናትና ምእመናንን የምትመራ ቢሆንም እነዚህ ሁሉ ትላልቅ መረጃዎችና መዛግብት ግን በአንድ ላይ ተሰንደው ከመቀመጥ ይልቅ በተበታታነ ሁኔታ እንደሚገኙ ተገልጿል። በመሆኑም የቤተክርስቲያን ቅርስና ሀብት ዘመኑ የሚጠይቀውን የዲጂታል ቴክኖሎጂ በመጠቀም በአንድ ማዕከል ሠንዶ ማስቀመጥ እንደሚገባ ሰብሳቢው አስገንዝበዋል ፡፡
የአስተዳደር ጉባኤ አባላቱም በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አመራር ለዘርፉ የተሰጠውን ትኩረትና የተከናወኑ ተግባራትን በማድነቅ አስተያየት የሰጡ ሲሆን፤ እነዚህ ትላልቅ ሥራዎች በአጭር ጊዜ ተጠናቀው በአዲሱ በጀት ዓመት ተግባራዊ ሊሆኑ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጥናቱን በማዘጋጀት ያቀረቡ የኮሚቴ አባላትን አመስግነው፤ ዲጂታል ቴክኖሎጂ ለቤተክርስቲያን አገልግሎት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት በግንቦት ፳፻፲፰ ዓ.ም የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ አጀንዳው መቅረቡን ጠቅሰዋል። ምልዓተ ጉባኤውም በአጀንዳውና የቀረቡለት የተለያዩ ሥራዎችን በመገምገም የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ መመሪያ መስጠቱን አውስተዋል።ዛሬ የቀረቡትም የተለያዩ የጥናት ሰነዶችም ይህንኑ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውሳኔ መሠረት በማድረግ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
በመጨረሻም በብፁነታቸው የተመራው የአስተዳደር ጉባኤ አባላት በመንበረ ፓትርያተርክ ቅጽር ግቢ የሚሠራውን የልማት ሥራ ተመልክተውዋል፤ በተለይም ለብፁዓን አባቶች ማረፊያ ቤት አጠገብ የሚሠራውን ግንባታ በልዩ ትኩረት በአፋጣኝ ተሠርቶ እንዲጠናቀቅ አባታዊ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡©Eotc tv