የላሊበላ ቅርሶችን ለመጠበቅ የሚያስችል ውይይት ሊደረግ መሆኑ ተገለጸ።
የ40 ሀገራት አምባሳደሮች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ቅዱስ ላሊበላ ከተማ መግባታቸው ይታወቃል።
በዚህ ጉብኝት ከ800 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩትን ውቅር አብያተክርስቲያናት ድንቅ የታሪክና የጥበብ ሥራዎች ከመመልከት ባለፈ፣ ከቤተክርስቲያን አባቶችና ከአካባቢው ማኅበረሰብ ጋር ውይይት ይደረጋል ተብሎም ይጠበቃል።
እንደ ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ዘገባ ከሆነ ከ”ዘላቂ ላሊበላ ፕሮጀክት” ተወካዮች እንዲሁም ከፈረንሳይ ኤምባሲ ጋር በመሆን ቅርሶቹን ከተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ አደጋዎች ለመጠበቅ እንዲሁም በዘላቂ ልማት ዙሪያ ሰፊ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።
ቅዱስ ላሊበላ በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፋት በተጓዙ አካላት በተደረገ ጥናትና በዩሮኒውስ በተዘገበው መረጃ መሠረት፣ በዓለም ካሉ የዓለም ቅርስ መዳረሻዎች መካከል ቀዳሚ ከሆኑ አምስት ምርጥ መዳረሻዎች አንዱ ሆኖ መመረጡ ይታወሳል።
©የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ