የአዳማ ሰቀቀሎ ደብረ ገነት ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤቱ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከበረ
ግንቦት ፪ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም አዳማ — በአዳማ ከተማ በውብ የኪነ-ሕንጻ ጥበብ የታነጸው የአዳማ ሰቀቀሎ ደብረ ገነት ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ ቤተ መቅደስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎችና በሺዎች የሚቆጠሩ ምእመናን በተገኙበት በዛሬው ዕለት ቅዳሴ ቤቱ በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት ተከብሯል።
ትላንት ግንቦት ፩ ቀን በብፁዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ (የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ቋሚ አባልና የኢትዮጵያ ሃይማኖቶች ተቋማት የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሰብሳቢ) እንዲሁም በብፁዕ አቡነ ጢሞቲዎስ (የዳውሮ፣ ኮንታ እና የከንባታ ሀላባ ጠንባሮ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ ቋሚ አባል) ቡራኬ ተባርኮ የተመረቀው ይህ ቤተ መቅደስ በዛሬው ዕለት ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል።
በክብረ በዓሉ ላይ በመገኘት ቡራኬና ትምህርት የሰጡት ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ፣ ምእመናን የእግዚአብሔርን ቤት በመሥራታቸው ያለቸውን ደስታ ገልጸው የሚከተለውን መልእክት አስተላልፈዋል፦
“ዛሬ አሳንጻችሁ የወልደ እግዚአብሔርን ሥጋውን የምንበላበት፣ ደሙን የምንጠጣበት የእግዚአብሔርን ቤት ሠርታችኋል። በዚህ ቤተ መቅደስ እመቤታችንን ቅድስት ድንግል ማርያም ፣ ቅዱሳን መላእክትን፣ ጻድቃንና ሰማዕታትን እናገኝባቸዋለን። ይህ ሥፍራ ያዘነ የሚጽናናበት፣ የደከመ የሚበረታበት፣ ያጣ የሚያገኝበትና የተቸገረ ከችግሩ የሚላቀቅበት ዘላለማዊ ቤት ነው” ብለዋል።
ብፁዕነታቸው አክለውም፣ እግዚአብሔር ከምእመናን የሚፈልገው በዋናነት ራሳቸውን እንደሆነ ገልጸው፤ ምእመናን በንስሓ ሕይወት በመመላለስ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን መቀበል እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ በበኩላቸው፣ በሀገረ ስብከታቸው እየተከናወኑ ያሉ የቤተ ክርስቲያን የልማት ሥራዎችን በማድነቅ ጥልቅ የሆነ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክትና ቃለ ምዕዳን አስተላልፈዋል።
“ለሁሉም ነገር መሠረቱ ሕዝብ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝበ ክርስቲያን በሰላም፣ በአንድነትና በመቻቻል ተሳስሮ የኖረ ድንቅ ሕዝብ ነው። ይህ ሕዝብ ቤተ ክርስቲያኑን ሠርቶ በማስፈጸም ረገድ ያለውን ጥንካሬ የምናደንቀው ቢሆንም፤ ከምንም በላይ ግን ይህንን ለዘመናት የቆየ ሰላሙን፣ አንድነቱንና መቻቻሉን ጠብቆ ማስቀጠል አለበት” ብለዋል።
አክለውም አዳማ ከተማ የፍቅርና የአንድነት ከተማ መሆኗን ጠቅሰው፣ ከልጅ እስከ አዋቂ በገንዘባቸውና በጉልበታቸው ለደከሙ ሁሉ “እንኳን ደስ አላችሁ” በማለት በአባታዊ ቡራኬና ቃለ ምዕዳን ሰጥተዋል።
በዕለቱ የሀገረ ስብከቱ የስብከተ ወንጌል ኃላፊ መጋቤ ሐዲስ ቆሞስ አባ ኃይለ ገብርኤል ተስፋ፣ በብፁዕነታቸው መልካም ፈቃድ “የማትፈርስ መቅደስ” በሚል ርዕስ ጥልቅ የሆነ የወንጌል ትምህርት አስተምረዋል። መርሐ ግብሩን ደግሞ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሣሕል ቀሲስ ነጋሽ ሀብተ ወልድ በብቃት መርተውታል።
በመጨረሻም ሕንጻ ቤተ መቅደሱ ከጅምሩ እስከ ፍጻሜው እንዲደርስ በእውቀታቸው፣ በጉልበታቸውና በገንዘባቸው ከፍተኛ ድጋፍ ላደረጉ ምእመናንና ባለሙያዎች ዕውቅናና ምስጋና ተሰጥቷል።
የሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ ማጠቃለያ ዕይታ ፤ ይህ ውብ ሕንጻ ቤተ መቅደስ ከ108 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበት ለፍጻሜ መብቃቱ፣ ከመንፈሳዊ ጥንካሬ ባለፈ የታላቅ አመራርና የተናበበ ሥራ ውጤት መሆኑን ነው።
በተለይም የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ገነት ቀሲስ ታፈሰ ተስፋዬ፣ ግንባታው ከመሠረት ድንጋይ ጀምሮ እዚህ ደረጃ ላይ እስኪደርስ ድረስ የነበራቸው ሚና የሚደነቅ ነው። አስተዳዳሪው ከዲቁና የክህነት ማዕረግ ጀምሮ በዚህ ደብር ውስጥ በማገልገልና አሁን ላይም በኃላፊነት በመምራት፣ የአዳማ ከተማን ምእመናን በአንድነት በማስተባበር ያሳዩት ቁርጠኝነት ለቤተ መቅደሱ ግንባታ መሳካት ዋነኛ ምሰሶ ሆኖ ተገኝቷል።
ይህ ክስተት የሚያሳየው፣ አንጋፋ አባቶች ከሕዝበ ክርስቲያኑ ጋር በፍቅርና በትሕትና ሲሰለፉ፣ እንደዚህ ያሉ ታላላቅ የልማት ሥራዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ማከናወን እንደሚቻል ነው። ሚዲያችን እንደተመለከተው፤ የአስተዳዳሪው የረጅም ዘመን አገልግሎትና ከምእመናን ጋር የገነቡት ጥንካሬ፣ ዛሬ ለታየው ታላቅ መንፈሳዊ ድልና ለቤተ ክርስቲያኒቱ ክብር መጎናጸፊያ ሆኗል። ይህም ለሌሎች አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎችም ትልቅ ትምህርትና አርአያ የሚሆን ተግባር መሆኑን ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ ባደረገው ዳሰሳ አረጋግጧል።©ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ


ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል የዋሽንግተን እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰጡት የስጦታ መርሐ ግብር ላይ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተገኝተዋል።

በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሓዱ ኣምላክ ኣሜን!
ሚያዚያ ፳፯ ቀን ፳፻፲ወ፰ ዓ/ም
ሚያዝያ 27 ቀን 2018 ዓ.ም
በእንግሊዝ ለንደን ባት በተባለ ቦታ አርፎ እስከ1933 አገልግሎት እየሰጠ ቆይቷል በቀድሞ ስሙ ገነተ ልዑል ቤተ መንግስት የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2 ዓመታት ከቆየ በኃላ በቀድሞ ስሙ ቤተ ሳይዳ ወይም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሆስፒታል የአሁኑ የካቲት 12 ሆስፒታል ማረፊያ ተዘጋጅቶለት ከቆየ በኃላ ሚያዚያ 27 1942 ዓ.ም ወደ አሁኑ ያለበት ስፍራ በመምጣት በገዳምነት እያገለገለ ይገኛል።
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን — በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን

ሚያዚያ ፳፭ ቀን ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም

ሚያዚያ ፳፬ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
ሚያዚያ 24 ቀን 2018 ዓ.ም