በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት በሰበታ ገላን ጉዳና ፉሪ የዓለም ገና ደብረ ቀርሜሎስ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ተባረከ

ሚያዝያ 22 ቀን 2018 ዓ.ም
በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት በሰበታ ገላን ጉዳና ፉሪ ክፍላተ ከተማ ቤተክህነት የዓለም ገና ደብረ ቀርሜሎስ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ሕንጻ ቤተክርስቲያን ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም የበላይ ኃላፊ ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የራያና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳሰ፣ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የቅድስት ሀገር የኢየሩሳሌም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ መልአከ ሰላም ዓለማየሁ ሺፈራው የሸገር ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አሥኪያጅ፣ መልአከ ኃይል አባ አፈወርቅ ዮሐንስ የ3ቱም ክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ዋና ስራ አሥኪያጅ፣ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣የሰንበት ትምሕርት ቤት ዘማሪያን እና ዘማሪያት፣ በርካታ ምዕመናንና ምዕመናት በተገኙበት በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተባርከዋል።
ይህ ታላቅ ቤተ መቅደስ በኪነ ሕንጻ አሰራር በአይነቱ በውበቱ ዘመን ተሻጋሪ መሆኑን ቤተ መቅደስ ሲሆን ግንባታ በተጀነርፕ በ13ኛ ዓመት ተጠናቆ ላዛሬው ለምእቃት ቀ. በቅቷል ።
ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ይህ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ተሠርቶ ይጠነቀቃል ተብሎ ባይታሰብም በእግዚአብሔር መልካም ፍቃድ እና በእናንተ ብርታት ለምርቃት በመብቃቱ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ በበኩላቸው ይሄንን የደከማችሁበትን ሕንጻ ቤተክርስቲያን ለምርቃት በቅቶ ስላያችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ካሉ በኋላ በቤተክርስቲያን የምንሰበሰበብ ለዘለዓለማዊ ድኅነት ነው፤ ቤተክርስቲያን መማጸኛ እንዲሁም የሰውና የቅዱሳን መገናኛ ናትም ብለዋል ስለዚህ ወደ ቤተክርስቲያን የምንመጣው ምድራዊው በረከት፣ ሰማያዊ ክብር ለማግኘት ነውና ቤተክርስቲያን ልንጠብቃት፣ ልንከባከባት ያስፈልጋል በማለት አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በተጨማሪም በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አመራር ሰጪነት ብዙ ልማቶች እየተሠሩ እንደሆነም ጠቅሰዋል፤ ብፁዕነታቸው አክለውም እግዚአብሔር ህዝቡን የሚያገለግል፣ ቤተክርስቲያንን የሚያንጽ አባት ስለተሰጣችሁ እግዚአብሔርን ልታመሰግኑ ይገባልም በማለት ቃለ ቡራኬያቸውን አስተላልፈዋል።
በተመሳሳይ ሁኔታ ለሕንጻ ቤተክርስቲያኑ መሠራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉት ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
በተጨማሪም ደብሩ ለሚያከናውናቸው መሠረታዊ የልማት ሁለገብ G-1 ሕንጻ የመሠረት ድንጋይ አኑረዋል ።
በመጨራሻም በብፁዓን አባቶች ቃለምዕዳንና ቡራኬ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል።©ም/ዙ/መ/ገ/ሚዲያ

“የአበው ሥርዓት ለቤተ ክርስቲያን አንድነት” በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የቆየውን የገዳማት አበምኔቶችና እመምኔቶች አገር አቀፍ ጉባኤ ተጠናቀቀ

ሚያዚያ ፳፫ ቀን ፳፻፲ወ፰ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የገዳማት አስተዳደር መምሪያ ባዘጋጀው መርሐ ግብር፤ ከመላው ኢትዮጵያ የአንድነት ገዳማት ለተውጣጡ አበምኔቶች እና እመምኔቶች “የአበው ሥርዓት ለቤተ ክርስቲያን አንድነት” በሚል ርዕስ ሲሰጥ የነበረው የሥልጠና እና የምክክር ጉባኤ ፍጻሜውን አግኝቷል።
ከሚያዝያ ፳፪ እስከ ሚያዚያ ፳፫ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
ድረስ ለሁለት ተከታታይ ቀናት በተካሄደው በዚህ ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ፤ የገዳማቱን አስተዳደራዊ እና መንፈሳዊ አቅም የሚያጎለብቱ ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል። ከዚህም ባለፈ ተሳታፊዎቹ አባቶች እና እናቶች እርስ በርስ የልምድ ልውውጥና ጥልቅ ምክክር ያደረጉ ሲሆን፣ ከብፁዓን አባቶችም አባታዊ ቃለ ምዕዳን ተሰጥቷቸዋል።
በጉባኤው ላይ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የደቡብ ምዕራብና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ፣
የመንበረ ፓትርያርክ የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የባሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንዲሁም ብፁዕ አቡነ ቶማስ የምሥራቅ ጎጃም፣ የመተከል እና አዊ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተገኝተዋል። በተጨማሪም
የገዳማት መምሪያ ዋና ኃላፊ መጋቤ ካህናት አባ ሀብተ ጊዮርጊስ ዓሥራትን ጨምሮ ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የመጡ የገዳማት
አበምኔቶች (አባቶች) እና እመምኔቶች (እናቶች) የጉባኤው ተካፋይ ነበሩ።
በመዝጊያው መርሐ ግብር ላይ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ሰፋ ያለ አባታዊ መልእክትና መመሪያ አስተላልፈዋል። ብፁዕነታቸው በንግግራቸው “ገዳማት የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የጽናት መሠረቶች ናቸው” በማለት አጽንዖት ሰጥተው፣ አባቶችና እናቶች በአንድነት መሰባሰባቸውና መወያየታቸው ትልቅ ውጤት ያመጣ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። አክለውም “ለገጠሙን ችግሮች በጋራ ባደረግነው ውይይት መፍትሔ አግኝተናል፤ ቤተ ክርስቲያኒቱ አሁን ካለችበት ሁኔታ አኳያ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው የጸኑ ጠንካራ
መነኮሳት በእጅጉ ያስፈልጓታል። ስለዚህም ወደ ቀደመው እና ወደ ጥንታዊው የአበው መንፈሳዊ ሕይወት መመለስ ግድ ይለናል”
ብለዋል።
ከተሳታፊዎች ለተነሳው የማረፊያ ቦታ ጥያቄ በተመለከተም፣ ጉዳዩን አጥንተው ለቅዱስ ሲኖዶስ እንደሚያቀርቡ ብፁዕነታቸው ቃል ገብተዋል።
በመጨረሻም ገዳማውያኑ የቅዱስ ሲኖዶስ የጸሎት መሠረት መሆናቸውን በማስታወስ፣ “ጾምና ጸሎት ትልልቅ
መንፈሳዊ የጦር መሣሪያዎች በመሆናቸው ለሀገር እና ለቤተ ክርስቲያን ሰላም በትጋት ጸልዩ” ሲሉ አደራ ብለዋል።
ለሁለት ቀናት በስኬት ሲካሄድ የቆየው ይህ የምክክር እና የሥልጠና ጉባኤም፣ በአረጋዊው አባት በብፁዕ አቡነ ዮሴፍ
አባታዊ ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ ተጠናቋል።©EOTC t.v.