የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የለገጣፎ ደብረ ብፁዓን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣ አቡነ ሀብተ ማርያም እና አቡነ ሐራ ድንግል ዘመናዊ የፀበል ቤት በብፁዕ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ተባርኮ ተመረቀ

May 19, 2026

ግንቦት 10 ቀን 2018 ዓ.ም
በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት፣ በለገጣፎ ለገዳዲ እና ኩራ ጂዳ ክፍለ ከተማ ሥር የሚገኘው የደብረ ብፁዓን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣ አቡነ ሀብተ ማርያም ወአቡነ ሐራ ድንግል በዘመናዊ መልክ ያስገነባው የፀበል ቤት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ የለገጣፎ ለገዳዲ እና ኩራ ጂዳ፣ የቡራዩ ገፈርሳ፣ የጉጄ መልካ ኖኖ ክፍላተ ከተማ እንዲሁም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ኃይል አባ አፈወርቅ ዮሐንስ፣ የክፍለ ከተማው ዋና ጸሐፊ መጋቤ አእላፍ ስዩም ብዙአየሁ፣ የደብሩ አስተዳዳሪ መጋቤ ሐዲስ ሙሴ በለጠ፣ አባቶች ካህናት እና በርካታ ምዕመናንና ምዕመናት ተገኝተዋል።
በዚሁ መርሐ ግብር ላይ የደብሩ አስተዳዳሪ መጋቤ ሐዲስ ሙሴ በለጠ የደብሩን አጠቃላይ የሥራ ሪፖርት ለብፁዕነታቸው አቅርበዋል።
ብፁዕነታቸው በእለቱ ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት፤ “በጌጠኛ ቤትህ ልማት ይሁን” በሚል ኃይለ ቃል ሰፊ ትምህርት የሰጡ ሲሆን፣ ቤተ ክርስቲያን ሁለት ዓይነት ልማቶችን እንደምታከናውን አብራርተዋል።
የመጀመሪያውና ዋናው ልማት የክርስቶስ ሕንጻ የሆነውን የሰውን ልጅ አእምሮ በወንጌል ማልማትና የጠፉትን በጎች ፈልጎ ወደ በረቱ መመለስ ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ምዕመናን የሚፈወሱበትን የፀበል ቤት ማዘጋጀትና ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ሕንጻዎችን በመገንባት ቤተ ክርስቲያን ራሷን እንድትችል ማድረግ ነው ብለዋል። አክለውም ፀበሉ ለሕሙማንና ለድውያን ትልቅ የፈውስ ቦታ መሆኑን ገልጸዋል።
በመቀጠልም የፀበል ቤቱን ግንባታ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ሙሉ በሙሉ ያሠሩትን ለኃይለ ሚካኤል እና ለባለቤታቸው ለወይዘሮ ሥርጉተ ገብርኤል ብፁዕነታቸው የላቀ የምስጋና የምስክር ወረቀት አበርክተውላቸዋል።
በተመሳሳይ መልኩ በዕውቀታቸው፣ በጉልበታቸውና በሐሳባቸው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ምዕመናን የሽልማትና የምስጋና መርሐ ግብር ተከናውኗል።
በመጨረሻም መርሐ ግብሩ በብፁዕነታቸው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ተጠናቋል።© ሸገር ሀገረ ስብከት ሚዲያ

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/000035.jpg 252 448 Temesgen Tomas https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg Temesgen Tomas2026-05-19 03:05:582026-05-19 03:05:58የለገጣፎ ደብረ ብፁዓን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣ አቡነ ሀብተ ማርያም እና አቡነ ሐራ ድንግል ዘመናዊ የፀበል ቤት በብፁዕ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ተባርኮ ተመረቀ
Search Search

Recent Posts

  • የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም 81ኛ ዓመት የአንድነት ኑሮ ምሥረታ ክብረ በዓል ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ተከብረ
  • የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአዲስ አበባ የሰላምና የያብሮነት የጸሎት መርሐ ግብር ” ሃይማኖታዊ እሴቶቻችን ለዘላቂ ሰላማችን ” በሚል መሪ ቃል ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የሌሎች ሃይማኖት ተቋማት ተወካዮች በተገኙበት አደረገ
  • የአዳማ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምህረት ካቴድራል 1ኛ ዓመት የቅዳሴ ቤት ክብረ በዓል ብፁዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ በተገኙበት ተከበረ
  • በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ቤት ተከበረ
  • ደንበኛ ተኮር ስርዓት የወለደው የነዋሪዎች አንድነት ከድርጅቱ አልፎ ከጠቅላይ ጽ/ቤቱ ጋርም እያስተሳሰረ መሆኑ ተገለጸ

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: በአዶላ ወዩ በሚገኙ አድባራት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ክፍል ለሚማሩ ደቀመዛሙርት አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ተሰጠ Link to: በአዶላ ወዩ በሚገኙ አድባራት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ክፍል ለሚማሩ ደቀመዛሙርት አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ተሰጠ በአዶላ ወዩ በሚገኙ አድባራት የሰንበት ትምህርት... Link to: ክፍል ሁለት …..” ከግንቦት እስከ ግንቦት ” እንደሚከተለው ይቀርባል Link to: ክፍል ሁለት …..” ከግንቦት እስከ ግንቦት ” እንደሚከተለው ይቀርባል ክፍል ሁለት …..” ከግንቦት እስከ ግንቦት...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top