በሸገር ሀገረ ስብከት የዓለምገና ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የስብከተ ወንጌል አዳራሽ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ተመረቀ
ግንቦት 09 2018 ዓ/ም
በመርሐ ግብሩ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የኤድመንተንና የመካከለኛው ካናዳና ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የሲያትልና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ጤሞቴዎስ የዳውሮና ኮንታ አህጉረ ስብከት ጳጳስ ተገኝተዋል።
በተጨማሪም መልአከ ሰላም አለማየሁ ተፈራ የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ፤ ቆሞስ አባ አፈወርቅ ዮሐንስ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የለሚኩራ ክፍላተ ከተማና በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የሦስቱ ክፍላተ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ፣ መልአከ ምሕረት ፀጋየ ስለሽ የዓለምገና ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ዋና አስተዳዳሪ ፤ ካህናት ፣ መምህራን እና ምእመናን ተገኝተዋል።
ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የተመረቀው የዓለምገና ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የስብከተ ወንጌል አዳራሽ በሸገር ሀገረ ስብከት በስፋት እየተካሄደ የሚገኘውን የትምህርተ ወንጌል አገልግሎት ይበልጥ ለማጠናከር የሚረዳ ነው ተብሏል።©Eotc tv