በብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ተጀምሮ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ትጋት ለፍጻሜ ዹበቃው ባለ 480 ካሬ ሜትር ሁለገብ ሕንጻ ተመሹቀ

ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ኹፍተኛ ዚሥራ ኃላፊዎቜና ምዕመናን በተገኙበት፣ በአዲስ አበባ አሮጌ ቄራ አካባቢ ዚተገነባው ዘመናዊ ሁለገብ ሕንጻ በዛሬው ዕለት በደመቀ ሁኔታ ተመርቋል። ይህ በ480 ካሬ ሜትር ቊታ ላይ ያሚፈውና ባለ 11 ወለል (B+G+10) ዹሆነው ሕንጻ፣ ግንባታው ዹተጀመሹው በብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅነት ዘመነ ሢመት ነበር። ሆኖም ግንባታው በአራት ዚተለያዩ ኮንትራክተሮቜ እጅ በማለፉ ምክንያት ኹፍተኛ መጓተት አጋጥሞት ቆይቷል።
​ይህንን መጓተት ለመቅሹፍ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ዹመንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላላ ቀተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ኚተሟሙ በኋላ፣ ዚአሠራር ሥርዓቱን በማስተካኚልና ለሮሃ ኮንስትራክሜን ሙሉ ኃላፊነት በመስጠት፣ ግንባታው በአጭር ጊዜ ውስጥ ማለትም በ40 ቀናት አካባቢ ተጠናቆ ዛሬ ግንቊት 6 ቀን 2018 ዓ.ም ለምሹቃ እንዲበቃ ሆኗል።
​በምሹቃ መርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ዹመንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላላ ቀተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ዚቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጞሐፊ፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት እንዲሁም ዚቀተ ክርስቲያኒቱ ዚመምሪያና ዚድርጅት ኃላፊዎቜ ተገኝተዋል።
​ዚሕንጻውን ዝርዝር ሁኔታ በሚመለኚት ዚግንባታ አማካሪው ኢንጂነር ቀሲስ ደመቀ አሾናፊ እንዳብራሩት፣ ሕንጻው ለእያንዳንዱ ቀተሰብ ምቹ ዹሆኑ ባለ ሊስት መኝታ ቀቶቜን ዚያዘ ሲሆን፣ በውስጡም ዘመናዊ መጞዳጃ ቀቶቜና ባልኮኒዎቜ ተካተውለታል። በተጚማሪም ሕንጻው ዚሚኚተሉትን ዘመናዊ ዚደኅንነት ሥርዓቶቜ ያካተተ ነው፩
​ሙሉ ሕንጻውን ዚሚቆጣጠር ዚሎርቚላንስ ካሜራ ተገጥሞለታል።
​ሙቀትና ጭስን ለይቶ ዚሚያውቅና አደጋ ሲኚሰት አላርም ዚሚያደርግ ዹፋዹር ሲስተም ኮንትሮል አለው።
​በእያንዳንዱ ወለል ላይ ዚእሳት አደጋ መኚላኚያ (ፋዹር ሃይድራንት) እና ዹአደጋ ጊዜ መውጫ (ኢመርጀንሲ ኢግዚት) ተዘጋጅቶለታል።
​ይህ ታላቅ ዹምሹቃ ሥነ ሥርዓት በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ጞሎትና ቡራኬ ተጠናቋል።

ኚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዹተሰጠ መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡
ኚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዹተሰጠ መግለጫ
ዚእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኀ፣ ዚጌታቜንና ዚመድኀኒታቜን ዚኢዚሱስ ክርስቶስ አካልና ዚመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ዚሆነቜው ቅድስት ኊርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያናቜን ሲኖዶሳዊ በመሆኗ አበው ቅዱሳን በፍትሕ መንፈሳዊና በጉባኀ አድያም ዘአንጟኪያ “ወይኩን ሲኖዶስ ዘጳጳሳት ፪ተ ጊዜያተ በበዓመት – ዚጳጳሳት ጉባኀም በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን” ብለው በደነገጉት ቀኖና መሠሚትፀ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ዚሚመራው፣ ዚሐዋርያት መንበር ወራሜ ዹሆነው ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዹርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኀውን በኅብሚተ መንፈስ ቅዱስ ኚሚያዝያ 28 እስኚ ግንቊት 6 ቀን 2018 ዓ/ም ድሚስ አካሄዷል፡፡
ምልዓተ ጉባኀው ስለ ሀገር ሰላም፣ ስለ ቀተ ክርስቲያን አንድነትፀ ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነትና ክብር፣ በአጠቃላይ ወቅታዊ ጉዳዮቜን በተመለኹተ ሰፊ ውይይቶቜን በማድሚግ ዘመኑን ዹዋጁ ውሳኔዎቜን አሳልፏል፡፡ ኚውሳኔዎቹም መካኚል፡-
ዚቀተ ክርስቲያናቜንን አንድነት መጠበቅና ማስጠበቅ ዚቅዱስ ሲኖዶስ ተግባር በመሆኑ ጥንታዊትና ሐዋርያዊት ዚሆነቜውን ቀተ ክርስቲያን በአንድነቷና በሉዓላዊነቷ እንደተሚኚብናት ለወደፊቱም ሉዓላዊ ክብሯ ተጠብቆ እንድትቀጥል በምልዓተ ጉባኀው ዹተሠዹመው በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ዚሚመራው “ዚሀገራዊ ሰላምና ዚቀተ ክርስቲያን አንድነት” ኮሚ቎ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ በተሹጋጋ መንገድ እንዲካሄድ፣ ለሀገር ሰላምና ለሕዝብ አንድነት በሚጠቅም ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ቅድስት ቀተ ክርስቲያን ዚምትጞልይ ሲሆን ምርጫው በሁሉም ወገን ለኢትዮጵውያን ዘላቂ ሰላምንና መሚጋጋትን ዚሚያስገኝ ሆኖ እንዲፈጞም ቅዱስ ሲኖዶስ በአጜንዖት ያሳስባል፡፡
ብፁዕ አቡነ ኀልሳዕ ዚአርሲ ሀገሹ ስብኚትን በሊቀ ጵጵስና በቋሚነት እንዲመሩ፣ ሕዝቡን እንዲያጜናኑ እዚደሚሰ ያለውን ቜግር ኹቋሚ ሲኖዶስና በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ኚሚመራው ዹሰላም ኮሚ቎ ጋር በመሆን ዹሚመለኹተውን ዚመንግሥት አካል በማነጋገር ዘላቂ መፍትሔ እንዲያፈላልጉ ዚቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኀ ወስኗል፡፡
ኚጥንት ጀምሮ “ቅዱስ ሲኖዶስ” በሚል ርእስ እዚተዘጋጀ ይታተም ዹነበሹው ታሪካዊ መጜሔት ዚቅዱስ ሲኖዶስ ቀኖናዊ ውሳኔዎቜን በማካተት በቅዱስ ሲኖዶስ ጜ/ቀት አስፈጻሚነት ሕትመቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
ዚቀተ ክርስቲያናቜንን ደንቊቜ መመሪያዎቜ መርምሮ ማጜደቅ ዚቅዱስ ሲኖዶስ ሉዓላዊ ሥልጣን በመሆኑ፡-
ዚስብኚተ ወንጌል ሐዋርያዊ ተልእኮ ማስፈጞሚያ ደንብ በብፁዕ አቡነ ማርቆስ ሰብሳቢነት
ዚአንድነት ገዳማት ኅብሚት መተዳደሪያ ደንብ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጊስና ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ባሉበት በድጋሚ እንዲታይና ሌሎቹም ለውሳኔ ዚቀሚቡ ደንቊቜ በሊቃውንትና በሕግ ባለሙያዎቜ ታርመው ለጥቅምት 2019 ዓ/ም ምልዓተ ጉባኀ እንዲቀርቡ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል::
ዚቀድሞው ዹሾዋ ሀገሹ ስብኚት ሊቀጳጳስ ዚነበሩት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ “ዚቀተ ክርስቲያን ታሪክ በዓለም መድሚክ”ና “ዚኢትዮጵያ ቀተ ክርስቲያን ታሪክ” በሚሉ አርእስት አዘጋጅተው ያሳተሟ቞ው መጻሕፍትን ዚማሳተምና ዚማሰራጚት ዚባለቀትነት መብት ኚሚያዝያ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ለዝዋይ ሐመሚ ብርሃን ቅዱስ ገብርኀል ገዳም እንዲሆን ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
ኚተለያዩ አህጉሹ ስብኚት በቀሚቡ ጥናቶቜና ዚማጣራት ውጀቶቜ መሠሚት፡-
ዚደቡብ ሱዳን ሀገሹ ስብኚት ኚምሥራቅ አፍሪካ ሀገሹ ስብኚት ጋር ተደርቩ በብፁዕ አቡነ ማ቎ዎስ ሊቀ ጳጳስ እንዲመራፀ
ብፁዕ አቡነ ሩፋኀል ሊቀ ጳጳስ ዚጋምቀላንና ዚቀንሻንጉል ጉምዝ አህጉሹ ስብኚትን ብቻ እንዲመሩፀ
ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ዹጅማ ሀገሹ ስብኚት ሊቀ ጳጰስ ዹሰሜን ጎንደር ሀገሹ ስብኚትን እንደያዙ እንዲቀጥሉፀ
ብፁዕ አቡነ ኀፍሬም ዚቡኖ በደሌ ሀገሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ ዹቄለም ወለጋ ሀገሹ ስብኚትን ደርበው በአባትነት እንዲመሩ፣
ዚኮንታ ዞን ሀገሹ ስብኚት እንዲሆን ዹቀሹበው ጥያቄ ዹጾደቀ በመሆኑ ሀገሹ ስብኚቱ ራሱን ቜሎ እንዲደራጅና በብፁዕ አቡነ ጢሞ቎ዎስ ሊቀ ጳጳስ እንዲመራ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗልፀ
ዹመንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቀተ ክህነት ዚልማት ተግባራትን ምልዓተ ጉባኀው በኹፍተኛ ደሹጃ በማድነቅ፣ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ዹመ/ፓ/ጠ/ቀ/ክ/ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዚደቡብ ምዕራብ ሾዋና ዹሾገር ሲቲ አህጉሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስፀ በአባታዊ አመራር ዚፈጞሙት አስደናቂ ዚሥራ አፈጻጞም በጉልህ ዚሚታይ ለውጥ፣ ቅድስት ቀተ ክርስቲያንን ዚሚጠቅም፣ ሉዓላዊ ክብሯን ዚሚያስጠበቅ፣ ለሁሉም አበው ምሳሌነት ያለው በመሆኑ ምልዓተ ጉባኀው እጅግ ኹፍ ባለ ክብር አመስግኗል፡፡
በዚህም መሠሚት በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጁ አባታዊ መሪነት እዚተኚናወኑ ያሉት ተግባራት ማለትም፡-
ዚቀተ ክርስቲያንን ቀደምት ሠነዶቜ በዲጂታል ቮክኖሎጅ እንዲደራጁ ዚተደሚገበት ሥልት ተጠናክሮ እንዲቀጥልፀ
ኹ1970 ዓ/ም ጀምሮ በመጋዝን ተኚማቜተው ዚቆዩ በርካታ ልዩ ልዩ መጻሕፍትን ዚማሠራጚት ሂደት በተጀመሹው መንገድ እንዲጠናቀቅፀ
ቅድስት ቀተ ክርስቲያናቜን ዚኢንፎርሜሜንና ኮምኒኬሜን ተጠቃሚ እንድትሆን ዹተጀመሹው ዘመኑን ዹዋጀ ቮክኖሎጂ በሁሉም ዚቀተ ክርስቲያናቜን መዋቅር በዹደሹጃው ተጠናክሮ ተግባራዊ እንዲሆንፀ
በመንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቀተ ክህነት ሥር ዚተጀመሩ ዹሕንፃ ግንባታዎቜና አጠቃላይ ዚልማት ሥራዎቜ በተያዘላ቞ው ዹጊዜ ሰሌዳ መሠሚት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ ሁሉም አህጉሹ ስብኚትና ባለድርሻ አካላት ዚበኩላ቞ውን አስተዋጜኊና ትብብር እንዲያደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጜንዖት ያሳስባል፡፡
በሰሜን አሜሪካ ዹሰሜን ካሊፎርኒያ፣ ኔቫዳና አሪዞና ሀገሹ ስብኚት ኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስና ቅድስት አርሮማ ገዳም ዚመንፈሳዊ ኮሌጅ፣ ዚአብነት ት/ቀት ሥርዓተ ትምህርት ዚቀተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ ቀኖና፣ ታሪክና ትውፊት በጠበቀ መልኩ ተጠናክሮ መዋቅራዊ ተጠሪነቱም በአግባቡ ተጠብቆ ሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
ዹመንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቀተ ክህነት ጜ/ቀት ያቀሚበውን ዹ2019 ዓ/ም በጀት በማጜደቅ በተገቢው መንገድ ሥራ ላይ እንዲውል ምልዓተ ጉባኀው ወስኗል፡፡
በመጚሚሻም ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በተነጋገሚባ቞ው ጉዳዮቜ በትኩሚት ዚተወያዚው ዚቀተ ክርስቲያናቜንን ሁለንተናዊ ዕድገትና ተቋማዊ ሕልውና ስለማስጠበቅ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ሀገራቜንን ጚምሮ በመላው ዓለም እዚታዚ ያለው ግጭትና ዹሰላም መታጣት በእጅጉ አሳስቊታል፡፡
በመሆኑም ስለ ዓለምና ስለ ሀገራቜን ሰላም፣ ስለ ሰው ልጆቜ ደኅንነት፣ በዚቊታው በሃማኖታ቞ው ምክንያት መኚራ ዚሚደርስባ቞ውን በዚቊታው ዹሚገኙና ግጭት ባለባ቞ው ቊታዎቜ ያሉ ኊርቶዶክሳውያንን በማሰብ በመጪው ዹ2018 ዓ/ም ጟመ ሐዋርያት በመላው ዓለም ባሉ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ገዳማት፣ አድባራትና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ጾሎተ ምሕላ እንዲደርስ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
በመላው ዓለም፣ በደቡብ አፍሪካና በሳውዲ ዐሚቢያ ዚሚኖሩ ዜጎቻቜን ሰብዓዊ መብት እንዲኚበር፣ ዚርኅራኄ ምሕሚትና ፍትሕ እንዲያገኙ ዚሚመለኚታ቞ው አካላት ተገቢውን ክትትል እንዲያደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ ሐዋርያዊ ጥሪውን በማቅሚብ ለሰባት ቀናት ሲያካሂድ ዹሰነበተውን ቀኖናዊ ጉባኀ ዛሬ ግንቊት 6 ቀን 2018 ዓ.ም. በጞሎት አጠናቋል፡፡
“እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቊቿን ይባርክ”
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወእጚጌ ዘመንበሹ ተክለሃይማኖት
አዲስ አበባ – ኢትዮጵያ
ግንቊት 6 ቀን 2018 ዓ/ም

ቅዱስ ሲኖዶስ በልማትና ዘመናዊ አሠራር ላይ ያተኮሩ ውሳኔዎቜን በማሳለፍ ለ6 ቀናት ሲያካሂድ ዹቆዹውን ዹ2018 ዓ.ም ዹርክበ ካህናት ጉባኀውን አጠናቀቀ

ግንቊት 5 ቀን 2018 ዓ.ም
ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ ለስድስት ተኚታታይ ቀናት ሲያካሂድ ዹቆዹውን መደበኛ ዚምልኣተ ጉባኀ ስብሰባውን በ22 አጀንዳዎቜ ላይ በመወያዚትና ለቀተክርስቲያናቜን ቀጣይ ጉዞ ወሳኝ ዹሆኑ ውሳኔዎቜን በማሳለፍ ማጠናቀቁን ዚቅዱስ ሲኖዶስ ዚኮሙኒኬሜን ጉዳዮቜ ኃላፊ፣ ሚዳት ፕሮፌሰር ቀሲስ ዳንኀል ሰይፈ-ሚካኀል ለEOTCTV በሰጡት ዕለታዊ መግለጫ አስታውዋል።
ኃላፊው በሰጡት ማብራርያ፣ ጉባኀው በተለይም በመንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጜሕፈት ቀት እዚተኚናወኑ ያሉትን ዚልማት፣ ዹዘመናዊ አሠራር እና ዹቮክኖሎጂ ሜግግር ሥራዎቜ በዝርዝር ኹገመገመ በኋላ ኹፍተኛ አድናቆቱን መግለጹን ተናግሚዋል።
በጠቅላይ ቀተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና ዚደቡብ ምዕራብ ሾዋና ዹሾገር ኹተማ አህጉሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ በሆኑት በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ አመራር እዚተኚናወኑ ያሉ ተግባራት በምስል እና ድምፅ ዹተደገፈ ሰፊ ሪፖርት ለምልአተ ጉባኀው መቅሚቡን ዚጠቀሱት ሚዳት ፕሮፌሰር ቀሲስ ዳንኀል፣ ሪፖርቱ “ቀተክርስቲያናቜን ለዘመናት ያላትን ታሪካዊ አስተዋጜኊ እያስጠበቀቜ፣ ኹዘመኑ ጋር ዚሚራመድ አሠራርን ለመገንባት እዚተደሚገ ያለውን ርብርብ በጉልህ አሳይቷል” ሲሉ ገልጞዋል።
በሪፖርቱ ኚቀሚቡት ዋና ዋና ጉዳዮቜ መካኚል በመንበሹ ፓትርያርክ ግቢ እና “በኮሪደር ልማት” በተገኙ መሬቶቜ ላይ ዚተጀመሩ ዚግንባታ ፕሮጀክቶቜ እንዲሁም ግቢውን ዚማስዋብና ምቹ ዚማድሚግ ሥራዎቜ እንደሚገኙበት ዚገለጹ ሲሆን ሚዳት ፕሮፌሰር ቀሲስ ዳንኀል እንዳብራሩት፣ “ምልአተ ጉባኀው በአጭር ጊዜ ውስጥ ዚተገኙትን እነዚህን ተጚባጭ ውጀቶቜ በማዚት ሥራዎቹን በኹፍተኛ አድናቆት ምልዓተ ጉባኀው ተቀብሏ቞ዋል።” ብለዋል።
ኹዚህም በተጚማሪ፣ ለዘመናት ተቀምጠው ዚነበሩ ታሪካዊ ዚሰነድ መዛግብትን በዲጂታል ቮክኖሎጂ ዚማስቀመጥ ሥራ መጀመሩና
አስተዳደራዊ መዋቅሩን በማዘመን ዚአገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋ ለማድሚግ እዚተሠራ መሆኑ ተብራርቷል።
ለሹጅም ጊዜ በመጋዘን ዚቆዩ ቅዱሳት መጻሕፍትን በማሳተም ለምዕመናን ተደራሜ ዚማድሚግ ሥራም በስፋት መኹናወኑን ኃላፊው አክለው ገልጞዋል።
ብፁዓን አባቶቜ በቀሹበው ሪፖርት ላይ ሰፊ ውይይት ካደሚጉ በኋላ፣ “ዚተጀመሩት ስራዎቜ ዚቀተክርስቲያኒቱን ክብርና ልዕልና
ዚሚያስጠብቁ፣ ተቋማዊ ህልውናዋን ዚሚያጠናክሩና ለምዕመናን ዹሚሰጠውን አገልግሎት ዚሚያዘምኑ ናቾው” በማለት ሙሉ ድጋፋ቞ውን መግለጻ቞ውን ሚዳት ፕሮፌሰር ቀሲስ ዳንኀል አስሚድተዋል።
በዚህም መሠሚት ምልኣተ ጉባኀው ዚተጀመሩት ዚልማትና ዹማዘመን ሥራዎቜ ተጠናክሹው እንዲቀጥሉ ኹመወሰኑም በላይ፣ ሌሎቜ አባቶቜም በዹአህጉሹ ስብኚታ቞ው ተመሳሳይ ማሻሻያዎቜን እንዲተገብሩ ጥሪ ማቅሚቡን ገልጞዋል።
ጉባኀው ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ዚጀመሩትን ሥራ አጠናክሹው እንዲቀጥሉ ሙሉ ድጋፍ እንደሚሰጥም አሹጋግጧል ተብለዋል ።
ጉባኀው በሌሎቜ አስተዳደራዊ ጉዳዮቜ ላይ ኹመኹሹ በኋላም፣ በቀጣዮቹ ስድስት ወራት በቋሚ ሲኖዶስ ውስጥ ዚሚያገለግሉ ብፁዓን አባቶቜን ምርጫ ማካሄዱን ዚኮሙኒኬሜን ኃላፊው ተናግሚዋል።
በመጚሚሻም፣ “ለቀናት በተለያዩ አገራዊና ሃይማኖታዊ አጀንዳዎቜ ላይ ሲመክር ዹቆዹው ዚቅዱስ ሲኖዶሱ ምልኣተ ጉባኀ፣ በነገው
ዕለት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጹጌ ዘመንበሹ ተክለሃይማኖት በሚሰጡት ቃለ ምዕዳንና አባታዊ ቡራኬ በይፋ ይጠናቀቃል” ሲሉ ሚዳት ፕሮፌሰር ቀሲስ ዳንኀል ሰይፈ-ሚካኀል ማብራርያ቞ውን አጠቃለዋል።©EOTc tv

ዚኢትዮጵያ ዚሃይማኖት ተቋማት ጉባኀ እና ዚኢትዮጵያ ፈደራል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ “ጠንካራ ትብብር ለሀገር ሰላም! ሰላም ዹወል ሀብታቜን ነው!” በሚል መሪቃል ስለሰላም በጋራ ለመሥራት ዚሚያስቜላ቞ውን ዚጋራ ስምምነት ተፈራሚመ

ግንቊት 4 ቀን 2018 ዓ.ም
ኚዚቀተ እምነቱ ዹተወኹሉ አባቶቜ በተገኙበት “ጠንካራ ትብብር ለሀገር ሰላም በሚል ዹተኹናወነው ዚኢትዮጵያ ዚሃይማኖት ተቋማት ጉባኀ እና ዚኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዚጋራ ስምምነት ፊርማ ፀ በሀገራቜን በሚኹናወኑ ምክክሮቜ ሰላምን ለማሚጋገጥ አዲስ ምዕራፍ ዚሚኚፍት መሆኑ ተገልጿል ።
ዚስምነት ስነዱን ዚኢትዮጵያ ዚሃይማኖት ተቋማት ጉባኀ ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ እና ዚፌደራል ፖሊስ ኮሚሜነር ጀነራል ደመላሜ ገብሚሚካኀል ተፈራርመዋል ።
በዚሁ ስምምነት ውስጥ ወንጀለኞቜን መኹላኹል ፣ በጋራ በመሆን ወንጀል ሳይፈጠር አስቀድሞ መኹላኹል ዚሚያስቜል አቅም መፍጠር ፣ በሕግ ገደብና ነጻነት አንዱ በሌላው ጣልቃ ሳይገባ፣ ዚእምነት ተቋማት እና ዹሕግ አስኚባሪው አካል በዚራሳ቞ው ዹሕግ ማዕቀፍ እንዲሠሩ ድንበር ዹለዹ መሆኑ ተገልጿል ።
ሚስጥራዊነት በጋራ ስራዎቜ ወቅት ዹሚገኙ መሚጃዎቜና በመድሚኩ መልዕክት ያስተላለፉ ንቡሚ ዕድ ኀልያስ አብርሃ ዹመንበሹ ፓትርያርኚሰ ጠቅላይ ቀተክህነት ዚመንፈሳዊ ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ “እግዚአብሔር ዹሚናገሹውን እሰማለሁ፥ ሰላምን ለሕዝቡና ለቅዱሳኑ ይናገራልና” ዹሚለውን ቃል በመጥቀስ፣ ቀተክርስቲያን ሁልጊዜ ስለ ፍጻሜውም ሰላም እንደምትጞልይ ገልጾዋል ።
ሌህ ኢብራሂም ቱፋ ዚኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮቜ ምክር ቀት ፕሬዚዳንት ” ሰላም እንዲመጣ ዚሃይማኖት ሕግጋትን በማክበር እያንዳንዱ አማኝ ዚእምነቱን አስተምህሮ እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል።
ዚኢትዮጵያ ወንጌል አማኞቜ አብያተክርስቲያናት ካውንስልን በመወኹል ንግግር ያደሚጉት ቄስ ደሹጀ ጅምበሩ ዚክርስትና እምነት ዓላማ ሰላምን ማጜናት ፣ እንደሆነ ገልጾው መጜሐፍ ቅዱስ ለሰላም ወሳኝ እንደሆነ አስገንዝበዋል ።
ይህ ዚጋራ ስምምነት ሀገራቜንን ሰላምና ደኅንነት በመጜሐፍ ቅዱሳዊ መሠሚት ላይ ለማቆም ትልቅ ሚና እንደሚኖሚው ተወስቷል።© EOTC t.v

ኚግንቊት እስኚ ግንቊት

ክፍል አንድ
አምና በዚህ ወቅት ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኀ ዚግንቊቱን ርክበ ካህናት ጉባኀውን በሚያካሒድበት ወቅት አንዱ አጀንዳ አድርጎ ዚያዘው ዹጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና ዚቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጾሐፊ ምርጫን ነበር።
በምርጫውም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ዚደቡብ ምዕራብ ሾዋና ዹሾገር ኹተማ አህጉሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስን ዹጠቅላይ ቀተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ዚራያ ሀገሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስን ዚቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጾሐፊ በማድሚግ በኹፍተኛ ድምጜ መርጩ ሟማ቞ው።
ወዲያውኑም ሁለቱ ብፁዓን አባቶቜ ኚብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጚጌ ዘመንበሹ ተክለሃይማኖት አባታዊ ቡራኬና መመሪያን በመቀበል፣አስፈላጊና ውሳኔ ዚሚሹ ሥራዎቜን በቋሚ ሲኖዶስ በማስወሰንና ውሳኔዎቜን በጜኑ በማስፈጞም ሥራዎቻ቞ውን በውጀታማነት ለማኹናወን ጥሚት ማድሚግ ሲጀምሩ አንድነታ቞ውንና ወንድማማቜነታ቞ውን በአስተማማኝ ሁኔታ ማጜናት መሰሚታዊ ጉዳይ መሆኑን በማመን ተናበውና ተመካክሚው ዘመነ ሢመታ቞ውን በስኬት ለመፈጾም ቆርጠው ተነሱ።
ይህንንም ለማድሚግ በዕቅድ ላይ ዹተመሠሹተ ዚትኩሚት አቅጣጫን ነድፈው ዕቅዳ቞ውን ለማሳካት ዚሚያስቜል ዚሥራ ኃላፋዎቜ ዝውውርና ምደባን በማድሚግ ዚሚኚተሉትን ጉዳዮቜ ለማሳካት በሙሉ ኃላፊነት ወደ ሥራ ሲገቡ መንፈሳዊ፣አስተዳደራዊና ልማታዊ ዚሥራ ዘርፎቜን በውጀታማነት ለማኹናወን ዹሹጅም ጊዜ ልምዳ቞ው፣ዚመሪነት አቅማቾውና ዚማስፈጞም ብቃታ቞ውን በሚገባ ተጠቅመዋል።
በዚህም መሰሚት ባሳለፍነው አንድ ዓመት ውስጥ በቀተክርስቲያናቜን ታሪክ ታይቶና ተሰምቶ ዚማያውቅ ውጀት ማስመዝገብ ቻሉ።
በመሆኑም በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ዹመንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቀተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ዚደቡብ ምዕራብ ሾዋና ዹሾገር ኹተማ አህጉሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ አመራር ሰጪነትና ኹፍተኛ ክትትል ኚግንቊት እስኚ ግንቊት ምን ውጀቶቜ ተመዘገቡ? ዚሚሉትን ጥያቄዎቜ ለመመለስ እንቜል ዘንድ ጥቂቶቹን ለማሳያነት ያህል እንደሚኚተለው እናቀርባለን ።
1.ኛ. ስብኚተ ወንጌልን ለማስፋፋትና ለማጠናኹር ዚሚያስቜሉ በርካታ ዚውይይት መድሚኮቜ ፣ዚሰባኪያነ ወንጌልን አቅም ሊገነቡ ዚሚቜሉ ሥልጠናዎቜ፣ዚስብኚተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ አገልግሎትን በማኅበራዊ ሚዲያ ዚማስፋፋት ሥራዎቜ ፣ለበርካታ ዓመታት ሳይሰበሰብ ዹቀሹውን ዚስብኚተ ወንጌል አገልግሎት አንድ ፐሚሰንት ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብም ዚመምሪያውን ገቢ ዚማሳደግና በበጀት እጥሚት ምክንያት አገልግሎቱ እንቅፋት እንዳይገጥመው ዚማድሚግ ሥራ፣ ዚስብኚተ ወንጌል ስምሪትና ዚመምሪያውን ሥራ ዹበለጠ ለማጠናኹር ዚሚያስቜሉ ልዩልዩ ጥናቶቜም ተደርገዋል።በመደሚግም ላይ ይገኛሉ።
በሾገር ኹተማና ደቡብ ምዕራብ ሾዋ አህጉገሹ ስብኚት ደሹጃ በብፁዕነታ቞ው አመራር ሰጪነት ዹተቋቋመው ወጣትነት ለቀተክርስቲያን በተሰኘው ማኅበር አማካኝነትም ታላላቅ ዚስብኚተ ወንጌል መርሐ ግብሮቜም ተካሒደዋል።
በአጠቃላይ በስብኚተ ወንጌል ዘርፍ ዹተኹናወኑና በመኹናወን ላይ ዹሚገኙ ስኬታማ ሥራዎቜ በዘርፉ ቀተክርስቲያን ዹበለጠ ውጀታማ ሥራን ማኹናወን እንድትቜል ዚሚያደርጋት ነው።
2.ኛ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን ዚቀቶቜና ሕንጻዎቜ አስተዳደርና ልማት ድርጅትን አሠራር ማዘመን ይቻል ዘንድ ብፁዕነታ቞ው ዚሰጡትን አመራር ተኚትሎ ኹፍተኛ ሥራ ተሠርቷል። በዚህም ዚገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱ ዘመናዊና ዲጃታል እንዲደሚግ፣ድርጅቱ ዚራሱ ዹሆነ ማኅበራዊ ሚዲያ እንዲኖሚውና በድርጅቱ ዚሚሠሩ ሥራዎቜ ሁሉ በዹጊዜውም ውጀታ቞ው ለሕዝብ ይፋ እንዲደሚግ ተደርጓል፣ዚድርጅቱን ገቢ ዚሚጎዱና ግለሰቊቜን ዹሚጠቅሙ ዚኪራይ አሰባሰብ ሥርዓቶቜን በማስወገድ ዚቀተ ክርርቲያን ገቢ በአግባቡ ዚሚሰበሰብበት ሥርዓት ተፈጥሯል፣ በጎ አድራጊዎቜን በማስተባበር ዚድርጅቱ ቢሮ በዘመናዊና ዚቀተክሚስቲያናቜንን ክብር በሚመጥን መልኩ እንዲታደስ ተደርጓል።በአጠቃላይ በድርጅቱ ውስጥ ኹፍተኛ መነቃቃትና ዚሥራ ተነሳሜነት እንዲጎለብት፣አሠራሩ እንዲዘምንና ውጀታማ ተቋም እንዲሆን ዚማድሚግ ሥራ በማኹናወን ድርጅቱን ግንባር ቀደም ዚቀተክርስቲያናቜን ዚልማት ተቋም ማድሚግ ተቜሏል።
3.ኛ እጅግ በጣም ለበርካታ ዓመታት ኚዕቅድ፣ኚፍላጎትና ኚሥርጭት ጋር ሳይጣጣሙ በኹፍተኛ ወጪ ታትመው ዚተኚማቹ መጻሕፍቶቜን ዚመለዚት፣ዚማደራጀት፣ዚማሰባሰብና ዚማሰራጚት ሥራ መላውን ዚቀተክህነት ሠራተኛን በማሳተፍ እንዲኚናወን በማድሚግ መጻሕፍቶቹ በጚሚታ ተሾጠው ዚቀተክርስቲያን ገቢ በአግባቡ እንዲሰበሰብ፣መጻሕፍቱም አገልግሎት ላይ እንዲውሉ ዚማድሚግ ታሪካዊ ሥራ ተሰርቷል።
4.ኛ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያንን ታሪኮቿ፣ ዚቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎቜን፣ልዩልዩ ሃብቶቿን፣ዚቀተ ክርስቲያናቜንን ሁለንተናዊና ተቋማዊ ሕልውናን ዚሚመሰክሩ ማኅደሮቜ በተበታተነና ለአያያዝ ምቹ ባልሆኑ ሥፍራዎቜ ተኚማቜተው ለአደጋ ተጋልጠውና ለመጥፋት ተቃርበው ዚነበሩ ሲሆን እነዚህን ፋይሎቜ በሚገባ ተለይተው፣ተደራጅተውና በዘመናዊ መልኩ ወደ ዲጂታል ፋይል ተቀይሹው ለታሪክና ለትውልድ እንዲተላለፉ እንዲደሚግ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ዹተሰጠውን መመሪያ ተኚትሎ ፋይሎቹን ወደ ዲጂታል ዚመቀዚሩ ሥራ እዚተኚናወነ ይገኛል። ቀደም ሲል ዚቀተክርስቲያናቜንን አሠራር ወደ ዘመናዊና በICT ዚተደራጀ እንዲሆን ለማድሚግ ዹተጀመሹውን ሥራ ማስቀጠል እንዲቻልም ኹፍተኛ ባለሙያዎቜን ዚያዘ ኮሚ቎ በማደራጀትም ትርጉም ያለው ሥራ እዚተሠራ ይገኛል።
5.ኛ ለበርካታ ዓመታት ሳይጞዳ ዹኖሹው ለእይታ ዹማይመቾውና ዚቀተክርስቲያንን ክብርና ልዕልናን ዚማይመጥነውን ዹመንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቀተክህነት ቅጜር ጊቢ በሚገባ ጞድቶ፣
አምሮና ተውቊ፣ለዕይታ ዚሚማርክ፣ዚቀተክርስቲያንን ክብር ዚሚመጥን፣ዚሥራ ተነሳሜነትን ዚሚፈጥር፣ቅጜሚ ጊቢ እንዲሆን ተደርጓል። ዚቅጜሚ ጊቢው ማማር እጅግ በጣም ኹፍተኛ በሆነ ወጪ በመገንባት ላይ ለሚገኘው ዘመናዊው ዚመሰብሰቢያ አዳራሜ ተጚማሪ ውበትን ያጎናጞፈ ሲሆን ዹዘመናዊ አዳራሜ ግንባታው አፈጻጞምም እስኚዛሬ ኹነበሹው እጅግ በተሻለ ሁኔታና ፍጥነት መኹናወን በመቻሉ እነሆ ዚማጠቃለያ ሥራ ላይ ይገኛል። ዚግንባታ ሥራው ሙሉበሙሉ ተጠናቆ ሥራ በሚጀምርበት ወቅትም ታላላቅ ዚስብኚተ ወንጌል መርሐ ግብሮቜን በማኹናወን ዚስብኚተ ወንጌል እንቅስቃሎዎቜን ኚማስፋፋት ጎን ለጎን ሀገራቜን
ዚምታኚናውና቞ውን ዓለም ዓቀፋዊ ስብሰባዎቜን ጭምር በማስተናገድ ዚቀተክርስቲያን እና ዹሀገር ኩራት ዹሚሆን ተቋም በመሆን እንደሚያገለግል ይታመናል።
6.ኛ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ዚቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጞሐፊ፣ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ በነበሩ ጊዜ በተለምዶ አሮጌው ቄራ በመባል በሚታወቀው ቊታ ላይ በመሠራት ላይ ዚነበሩት ሁለት ግዙፋን ሁለገብ ሕንጻዎቜም ትኩሚት ሰጥቶ ለውጀት ዚሚያበቃ቞ው አጥተው ለበርካታ ዓመታት ዚቀተክርስቲያን ሀብት ሲባክንባ቞ው ኹርመው በአሁኑ ወቅት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ፣ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ዚቅዱስ ሲኖዶስ ጾሐፊ በመሆን ዳግም ወደ አመራርነት ሲመጡ በልዩ ትኩሚትና በፍጥነት እንዲሠሩ በመደሹጋቾው እነሆ በአራት መቶ ሰማኒያ ካሬ ላይ ያሚፈው ሕንጻ ግንባታ ተጠናቆ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ፣ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ዚመንግሥት ኹፍተኛ ዚሥራ ኃላፊዎቜ በተገኙበት በዛሬው ዕለት በደማቅ ሥነሥርዓት ለምርቃት ሲበቃ በአንድ ሺህ ካሬ ሜትር ቊታ ላይ ያሚፈው ሕንጻ ግንባታ ደግሞ ዚግንባታ ሥራው በመፋጠን ላይ ይገኛል። ይ ቀ ጥ ላ ል …
ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን
ዚሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ግንቊት ፳፻ ፲ወ፰ ዓ.ም
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጚጌ ዘመንበሹ ተክለሃይማኖት በሳዑዲ ዓሚቢያ ዚሞት ፍርድ ተፈርዶባ቞ው በአስጚናቂ ሁኔታ ውስጥ ዹሚገኙ ወገኖቜን በማስመልኚት ለኢትዮጵያና ለሳዑዲ መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ ዚሰብአዊ መብት ተሟጋቜ ተቋማት እና ለመላው ዚኢትዮጵያ ሕዝብ አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።

ግንቊት 4 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

ቅዱስነታ቞ው ያስተላለፉት አባታዊ መልእክት እንደሚኚተለው ነው፩

መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

‹‹ተዘኚሩ መቁሓነ ዘኹመ ተሞቃሕክሙ ምስሌሆሙ ወእለ ተሣቀዩ ኹመ ዘሀለውክሙ በሥጋክሙ፡-
ኚእነርሱ ጋር አብራቜኋ቞ው እንደታሰራቜሁ ሆናቜሁ እስሚኞቜን ዐስቡፀ መኚራ ዚጞናባ቞ውንም በሥጋቜሁ ኚእነርሱ ጋር እንዳላቜሁ ሆናቜሁ ዐስቡ››
(ዕብ. 13፡3)

እውነተኛ እምነትም ሆነ ጀናማ አመለካኚት ዹሚመዘነው መኚራ ስለሚቀበሉ ሰዎቜ ሰምቶና አይቶ በዝምታ ባለማለፍፀ ይልቁንም በእነርሱ ሕመም ውስጥ ራስን በማስገባት በሚሰማው ጥልቅ ኀዘን እና በሚደሹገው ድጋፍ ነው፡፡ ይልቁንም በዚቜ ዓለም ዹምንኖር ለቜግርና ለመኚራ ቅርብ እንደመሆናቜን ዚታሰሩትን መጎብኘት፣ ዚተገፉትን ማጜናናት፣ በስደት ምድር ላይ ሆነው በሞት ፍርድ ዚሚጚነቁትን ወገኖቜ ስቃይም እንደራሳቜን ስቃይ በመቁጠር ስለእነርሱ ድምፅ መሆንና ማዘን ስንቜል በሰማያዊው መንግሥት ዹማይጠፋ ዚጜድቅ ዋጋን እናኚማቻለን፡፡

ዚተወደዳቜሁ ዚመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቜን!

እሚኛ በበሚት ውስጥ ያለቜው አንዲት በግ ስትጠፋ ወይም ለአደጋ ስትጋለጥ ዝም ብሎ እንደማያይ ሁሉ፣ በሳዑዲ ዓሚቢያ ምድር በሞት ጥላ ሥር ሆነው ‹‹ዚፍትሕ ያለህ›› እያሉ ዚሚጮኹፀ በጭንቀት ቀናትን ዚሚቆጥሩና ድምፅ ዹሌላቾው ኢትዮጵያውያን ልጆቻቜን ዚተሻለ ኑሮ እናገኛለን ብለው በተሰደዱበት ሀገር ሕይወታ቞ው በጅምላ ሊቀጠፍ እንደሆነ መሹጃውን ኚልዩ ልዩ መገናኛ ብዙኃን ዚተገነዘብን በመሆኑ ዚዲፕሎማሲ ግንኙነት ጠቀሜታው ዹሰው ልጆቜን ሕይወት ለመጠበቅ ነውና ዚኢትዮጵያ መንግሥት በኹፍተኛ ደሹጃ ኹሚገኙ ኚሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር በመነጋገር በግፍ ዚተፈሚደባ቞ው ልጆቻቜን ዚሞት ፍርድ እንዲነሳላ቞ውና ወደ ሀገራ቞ው ዚሚመለሱበት መንገድ ይመቻቜ ዘንድ ዚተጀመሩ ሥራዎቜ ልዩ ትኩሚት እንዲሰጥባ቞ውፀ ወገኖቻቜንም በቋንቋ እጥሚትና በሕግ አማካሪ እጊት ለሞት እንዳይዳሚጉ ኚአደራ ጭምር እናሳስባለን ፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ለሰው ልጅ ዹሰጠው ታላቅ ስጊታ ሕይወት ነውፀ “አትግደል” ዹሚለው ሕግም በማንኛውም ምድርና ቋንቋ ዚሚሠራ ሲሆን ፍርድ ያለ ምሕሚት ኹሆነ አምላካዊ ቁጣን ይጋብዛልና ዚሳዑዲ ባለሥልጣናት ዚሁለቱን ሀገራት ዹቆዹ ታሪክና ወዳጅነት አስበው፣ በሞት ፍርድ ጥላ ሥር ላሉት ወገኖቻቜን ምሕሚትን እንዲያደርጉ፣ ቅጣቱንም ወደ እስራት እንዲቀይሩ በአባታዊ ርኅራኄ እንጠይቃለን ፡፡

ዓለም አቀፍ ዚሰብአዊ መብት ተሟጋ቟ቜም በማያውቁት ቋንቋ እንዲሁም ባልተሚዱት ዹሕግ ሂደት ሞት ዚተፈሚደባ቞ውን ወገኖቜ ስቃይ ተመልክተው ዚፍትሕ መዛባትን እንዲቃወሙና ዚንጹሐንን ነፍስ እንዲታደጉ ጥሪያቜንን እናቀርባለን።

በመጚሚሻም፣ ማንኛውም በእግዚአብሔር አምሳል ዹተፈጠሹ ሰው ሕይወቱ ሊጠፋ አይገባምና ኊርቶዶክሳውያን ልጆቻቜን ዚክርስትናቜን አንዱ መገለጫ ዹአንደኛው ወገን ሕመምን በጋራ መካፈል እንደሆነ ተሚድታቜሁ ወደ ፈጣሪያቜን በጞሎት እንድትማጞኑፀ መላው ኢትዮጵያውያንም ለመፍትሔው ዚበኩላቜሁን ጥሚት እንድታደርጉ ስንል አባታዊ መልእክታቜንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቊቜዋን ይባርክ!!

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጹጌ ዘመንበሹ ተክለ ሃይማኖት
ግንቊት 4 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

ዚአዳማ ሰቀቀሎ ደብሚ ገነት ቅዱስ በዓለ ወልድ ቀተ ክርስቲያን ቅዳሎ ቀቱ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተኹበሹ

ግንቊት ፪ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም አዳማ — በአዳማ ኹተማ በውብ ዚኪነ-ሕንጻ ጥበብ ዚታነጞው ዚአዳማ ሰቀቀሎ ደብሚ ገነት ቅዱስ በዓለ ወልድ ቀተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ ቀተ መቅደስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ዹሀገሹ ስብኚት ዚሥራ ኃላፊዎቜና በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ምእመናን በተገኙበት በዛሬው ዕለት ቅዳሎ ቀቱ በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት ተኚብሯል።
ትላንት ግንቊት ፩ ቀን በብፁዕ አባታቜን አቡነ ጎርጎርዮስ (ዚምሥራቅ ሾዋ ሀገሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ፣ ዹዝዋይ ሐመሚ ብርሃን ቅዱስ ገብርኀል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ ዹበላይ ኃላፊ፣ ዚቅዱስ ሲኖዶስ ቋሚ አባልና ዚኢትዮጵያ ሃይማኖቶቜ ተቋማት ዚሥራ አስፈጻሚ ቊርድ ሰብሳቢ) እንዲሁም በብፁዕ አቡነ ጢሞቲዎስ (ዚዳውሮ፣ ኮንታ እና ዚኚንባታ ሀላባ ጠንባሮ አህጉሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስና ዚቅዱስ ሲኖዶስ ቋሚ አባል) ቡራኬ ተባርኮ ዹተመሹቀው ይህ ቀተ መቅደስ በዛሬው ዕለት ቅዳሎ ቀቱ ተኚብሯል።
በክብሚ በዓሉ ላይ በመገኘት ቡራኬና ትምህርት ዚሰጡት ብፁዕ አቡነ ጢሞ቎ዎስ፣ ምእመናን ዚእግዚአብሔርን ቀት በመሥራታ቞ው ያለ቞ውን ደስታ ገልጾው ዹሚኹተለውን መልእክት አስተላልፈዋልፊ
“ዛሬ አሳንጻቜሁ ዹወልደ እግዚአብሔርን ሥጋውን ዚምንበላበት፣ ደሙን ዚምንጠጣበት ዚእግዚአብሔርን ቀት ሠርታቜኋል። በዚህ ቀተ መቅደስ እመቀታቜንን ቅድስት ድንግል ማርያም ፣ ቅዱሳን መላእክትን፣ ጻድቃንና ሰማዕታትን እናገኝባ቞ዋለን። ይህ ሥፍራ ያዘነ ዚሚጜናናበት፣ ዹደኹመ ዚሚበሚታበት፣ ያጣ ዚሚያገኝበትና ዹተቾገሹ ኚቜግሩ ዚሚላቀቅበት ዘላለማዊ ቀት ነው” ብለዋል።
ብፁዕነታ቞ው አክለውም፣ እግዚአብሔር ኚምእመናን ዹሚፈልገው በዋናነት ራሳ቞ውን እንደሆነ ገልጞውፀ ምእመናን በንስሓ ሕይወት በመመላለስ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን መቀበል እንዳለባ቞ው አሳስበዋል።
ዹሀገሹ ስብኚቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አባታቜን አቡነ ጎርጎርዮስ በበኩላ቞ው፣ በሀገሹ ስብኚታ቞ው እዚተኚናወኑ ያሉ ዚቀተ ክርስቲያን ዚልማት ሥራዎቜን በማድነቅ ጥልቅ ዹሆነ ዚእንኳን አደሚሳቜሁ መልእክትና ቃለ ምዕዳን አስተላልፈዋል።
“ለሁሉም ነገር መሠሚቱ ሕዝብ ነው። ዚኢትዮጵያ ሕዝበ ክርስቲያን በሰላም፣ በአንድነትና በመቻቻል ተሳስሮ ዹኖሹ ድንቅ ሕዝብ ነው። ይህ ሕዝብ ቀተ ክርስቲያኑን ሠርቶ በማስፈጞም ሚገድ ያለውን ጥንካሬ ዹምናደንቀው ቢሆንምፀ ኹምንም በላይ ግን ይህንን ለዘመናት ዹቆዹ ሰላሙን፣ አንድነቱንና መቻቻሉን ጠብቆ ማስቀጠል አለበት” ብለዋል።
አክለውም አዳማ ኹተማ ዹፍቅርና ዚአንድነት ኹተማ መሆኗን ጠቅሰው፣ ኹልጅ እስኚ አዋቂ በገንዘባ቞ውና በጉልበታ቞ው ለደኹሙ ሁሉ “እንኳን ደስ አላቜሁ” በማለት በአባታዊ ቡራኬና ቃለ ምዕዳን ሰጥተዋል።
በዕለቱ ዹሀገሹ ስብኚቱ ዚስብኚተ ወንጌል ኃላፊ መጋቀ ሐዲስ ቆሞስ አባ ኃይለ ገብርኀል ተስፋ፣ በብፁዕነታ቞ው መልካም ፈቃድ “ዚማትፈርስ መቅደስ” በሚል ርዕስ ጥልቅ ዹሆነ ዹወንጌል ትምህርት አስተምሚዋል። መርሐ ግብሩን ደግሞ ዹሀገሹ ስብኚቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአኹ ሣሕል ቀሲስ ነጋሜ ሀብተ ወልድ በብቃት መርተውታል።
በመጚሚሻም ሕንጻ ቀተ መቅደሱ ኚጅምሩ እስኚ ፍጻሜው እንዲደርስ በእውቀታ቞ው፣ በጉልበታ቞ውና በገንዘባ቞ው ኹፍተኛ ድጋፍ ላደሹጉ ምእመናንና ባለሙያዎቜ ዕውቅናና ምስጋና ተሰጥቷል።
ዹሐመሹ ተዋሕዶ ሚዲያ ማጠቃለያ ዕይታ ፀ ይህ ውብ ሕንጻ ቀተ መቅደስ ኹ108 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበት ለፍጻሜ መብቃቱ፣ ኚመንፈሳዊ ጥንካሬ ባለፈ ዚታላቅ አመራርና ዹተናበበ ሥራ ውጀት መሆኑን ነው።
​በተለይም ዚደብሩ አስተዳዳሪ መልአኹ ገነት ቀሲስ ታፈሰ ተስፋዬ፣ ግንባታው ኚመሠሚት ድንጋይ ጀምሮ እዚህ ደሹጃ ላይ እስኪደርስ ድሚስ ዚነበራ቞ው ሚና ዹሚደነቅ ነው። አስተዳዳሪው ኚዲቁና ዚክህነት ማዕሹግ ጀምሮ በዚህ ደብር ውስጥ በማገልገልና አሁን ላይም በኃላፊነት በመምራት፣ ዚአዳማ ኹተማን ምእመናን በአንድነት በማስተባበር ያሳዩት ቁርጠኝነት ለቀተ መቅደሱ ግንባታ መሳካት ዋነኛ ምሰሶ ሆኖ ተገኝቷል።
​ይህ ክስተት ዚሚያሳዚው፣ አንጋፋ አባቶቜ ኹሕዝበ ክርስቲያኑ ጋር በፍቅርና በትሕትና ሲሰለፉ፣ እንደዚህ ያሉ ታላላቅ ዚልማት ሥራዎቜን በአጭር ጊዜ ውስጥ ማኹናወን እንደሚቻል ነው። ሚዲያቜን እንደተመለኚተውፀ ዚአስተዳዳሪው ዹሹጅም ዘመን አገልግሎትና ኚምእመናን ጋር ዚገነቡት ጥንካሬ፣ ዛሬ ለታዚው ታላቅ መንፈሳዊ ድልና ለቀተ ክርስቲያኒቱ ክብር መጎናጞፊያ ሆኗል። ይህም ለሌሎቜ አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎቜም ትልቅ ትምህርትና አርአያ ዹሚሆን ተግባር መሆኑን ሐመሚ ተዋሕዶ ሚዲያ ባደሚገው ዳሰሳ አሚጋግጧል።©ሐመሚ ተዋሕዶ ሚዲያ

ብፁዕ አቡነ ፋኑኀል በቃሊቲ አካባቢ ለበጎ አድራጎት ሥራ ኹ23 ዓመት በፊት ያስገነቡትን Gተ1 ዚመኖሪያ ሕንጻ ለመቄዶንያ ዚአሚጋውያንና ዚአእምሮ ሕሙማን መርጃ ማኅበር በስጊታ አበሚኚቱ

ብፁዕ አቡነ ፋኑኀል ዚዋሜንግተን እና አካባቢው ሀገሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ በሰጡት ዚስጊታ መርሐ ግብር ላይ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ዚቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጞሐፊ፣ዚራያ ሀገሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተገኝተዋል።
ብፁዕ አቡነ ፋኑኀል ለበጎ አድራጎተት እንዲውል ዚሕንጻ ቁጥሩ 982 ዹሆነውንና በግል ገንዘባ቞ው በ544 ካሬ ሜትር ቊታ ያሚፈ ሕንጻ በመገንባት ለዚሁ ዓላማ እንዲውል አድርገዋል።
ሕንጻው ያሚፈበት ቊታ 240 ካሬ ሜትር ሲሆን በግንባታ ወቅት ዚወጣበት ወጪ ኹ3ሚሊዮን በላይ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ባለው ዚገበያ ዋጋ ኹ120 ሚሊዮን በላይ ይገመታል።ሕንጻው ኚተገነባ 23 ዓመታትን ማስቆጠሩ ተገልጿል።
በመርሐ ግብሩ አቶ አምሓ ይልማ ባቀሚቡት መልእክት ብፁዕ አቡነ ፋኑኀል ሕንጻውን በገነቡበት ወቅት ያስተላለፉትን በሕግ ፊት ዹሚጾና ተብሎ ዹተመዘገበውን ዹኑዛዜ ሰነድ በጜሑፍ አቅርበውታል።
ቀቱን ለመቄዶንያ አሚጋውያንና አእምሮ መርጃ ማዕኹል ለማስተላለፍ ኚቀተ ሰብ ጭምር ኮሚ቎ (ቊርድ) ተቋቁሟል ተብሏል።
በመቀጠልም በስጊታ አድራጊ ብፁዕ አቡነ ፋኑኀልና በስጊታ ተቀባይ መቄዶንያ ዹውል ስምምነት ሰነድ እና ካርታ ርክክብ ተፈጜሟል።
ብፁዕ አቡነ ፋኑኀል በስጊታ መርሐ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልእክት እግዚአብሔር ዹሰጠኝን ቀት ለእግዚአብሔር አስሚክቀያለሁ ብለዋል። ብፁዕነታ቞ው ጹምሹው እንደገለጹት 19 ዓመት ዚቀቱ ኪራይ ለበጎ አገልግሎት ውሏል ብለዋል።
መስጠት ዹማይፈልጉ ኃይሎቜ ዚእኔን ስጊታ ሲተቹ ሰምቻለሁ።
ይህ ግን አግባብነት ዹለውም ብለዋል። ብፁዕነታ቞ው እኔ ዹሚቆጠር ንብሚት ዹለኝም ያሉ ሲሆን በመጚሚሻም ካርታውንና ዚቀቱን ቁልፍ ዚመቄዶንያ መሥራቜ ብኒያም በለጠ ተሹክበው ዚምስጋና መልእክት አስተላልፈዋል።
ብፁዕ አቡነ ፋኑኀል 18 ዓመታ቞ው ስለመነኮሱ እግዚአብሔር ዚመቄዶንያ መሥራቜ ብንያም በለጠ ዚጠራ቞ው አባት መሆናቾውን እናምናለን። ስጊታ቞ውን ዚሚያጣጥሉ ኃይሎቜ መፈጠራ቞ው አሳዝኖናል ብለዋል።
ቀድሞም ዚቀት ኪራዩን ሜቄዶንያ ሲጠቀምበት ዹቆዹ መሆኑ ዹተገለጾ ሲሆን ቀቱ ብፁዕ አቡነ ፋኑኀል 58ኛ መቄዶንያ ቅርንጫፍ እንዲባል ጠይቀዋል።
በመቄዶንያ ታሪክ ትልቁ ስጊታ ይህ ነው በማለት ዚመቄዶንያ መሥራቹ ብኒያም በለጠ ተናግሚዋል።
በመቀጠልም ዚሃይማኖት ተቋማት መሪዎቜ ስለስጊታው አርአያነት ያለው ነው በማለት አድናቆታ቞ውን ገልጞዋል።
ዚመቄዶንያ አሚጋውያንና አእምሮ ሕሙማን ማዕኹል ተሚጅዎቜም ምስጋና቞ውን አቅርበዋል።
ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ዚስብኚተ ወንጌልና ሐዋርያዊ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ አባታዊ ትምህርት ዚሰጡ ሲሆን ብፁዕነታ቞ው በሰጡት ትምህርት ዚትንሣኀው በኩር ዹሆነው ኢዚሱስ ክርስቶስ ኚእኔ ተማሩ በማለት ያስተማሚውን ትምህርት ብፁዕ አቡነ ፋኑኀል በተግባር አውለውታል ብለዋል።
ብፁዕነታ቞ው ራሳ቞ውን በመስጠት ትልቁን መሰናኹል አልፈዋል ብለዋል። ዛሬ ያጣነው ዚሚሠራ እንጂ ዚሚያወራ አይደለም ሲሉ መልዕታ቞ውን አጠቃለዋል።
በመጚሚሻም በብፁዕ አቡነ ኀልያስ ዚኖርዲክ ሀገራት እና ዚግሪክ አህጉሹ ስብኚት ሊቀጳጳስ ዚመጚሚሻ ትምህርትና ጞሎት መርሐ ግብሩ ተጠናቋል።©Eotc tv.

መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ

በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሓዱ ኣምላክ ኣሜን!
ብፁዕ ኣቡነ ሳዊሮስ
ዹመንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቀተ ክህነት ዋና ስራ ኣስኪያጅፀ
ብፁዕ ኣቡነ ዲዮስቆሮስ
ዚቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጞሓፊፀ
ብፁዕ ኣቡነ ሕርያቆስ
ዚኣዲስ ኣበባ ሃገሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ፣
ብፁዓን ኣበው ሊቃነ ጳጳሳት ዚቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት፣
በኣጠቃላይ በዚህ ዓመታዊ ዚቅዱስ ሲኖዶስ ምልኣተ ጉባኀ ዚተገኛቜሁ በሙሉ፩
ማሕዚዊት በምትሆን ሞቱ ሰማያውያንና ምድራውያንን ያስታሚቀ፣ በቅድስት ትንሣኀውም ዚሙታንን ሕይወት በተስፋ ያለመለመ ጌታቜን፣ ኣምላካቜንና መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ፣ እንኳን ለዓመታዊው ዹሹክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልኣተ ጉባኀ ኣደሚሰን ኣደሚሳቜሁ!
“እስመ ተዋለጠ እግዚአብሔር ዓለመ በክርስቶስ ኣናኅስዮ ኃጢኣቶሙ ወኢነጺሮ ጌጋዮሙፀ ወሹሰዹ ላዕሌነ ቃለ ሥምሚቱፀ ወወሃበነ መልእክተ ሣህሉ፡- እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ኚራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና በደላቾውን ኣይቈጥርባ቞ውም ነበርፀ በእኛም ዚማስታሚቅ ቃል ኣኖሚ” (2ቆሮ. 5፥19)።
ዚእግዚአብሔርም ልጅ፣ ዹሰውም ልጅ ዹሆነው ጌታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም በሰብእነት ሲገለጜ ግልጜ ዹሆነ ዓላማና ግብ እንደነበሚው ቅዱስ መጜሓፍ ይነግሚናልፀ እሱም በሰማይም፣ በምድርም ያሉትን በሙሉ ማስታሚቅ፣ ማገናኘትና ኣንድ ማድሚግ ነበሚፀ
ጌታቜን ይህንን ሲያደርግ ሰማያውያኑንና ምድራውያኑን ዚለያዚው ምክንያት በማስወገድ ነውፀ ዚመለያዚቱ ምክንያት ክፉ ኅሊና ኣምጊ ዹወለደው በደልና እሱን ተኚትሎ ዹተኹሠተው ኃጢኣት ነበሚፀ በኃጢኣት ምክንያት ዚገባው ሞት ደግሞ ዚቅጣቱ ማሳያ ፍርድ ነበሚ።
ዚመጀመሪያዎቹ ሰዎቜ በፈጞሙት ስሕተት መነሻነት ምድርንና ምድራውያንን ለኚባድ ቅጣትና መርገም ዚዳሚገው ይህ መለያዚት ለሰማያውያኑም ተርፎኣልፀ
ምክንያቱም መለያዚቱ በእግዚአብሔርና በሰው፣ በመላእክትና በሰው፣ በሰውና በሰው፣ በነፍስና በሥጋ ጭምር ዚጥል ግድግዳን ገንብቶ እስኚ ክርስቶስ ዕለተ ስቅለት መዝለቁን በቅዱስ መጜሓፍ ዹምናውቀው ስለሆነ ማለት ነው።
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ዚቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት!
ቀዳማዊና ዘላለማዊ ዹሆነው ወልደ እግዚአብሔር ኢዚሱስ ክርስቶስ ሰብእናቜንን ተዋሕዶ በዚህ ዓለም ዹተገለጾው ሰማያውያንንና ምድራውያንን ዚለያዚው ዚጥል ግድግዳን ለማፈራሚስ ነውፀ
ለመለያዚት ምክንያት ዚሆነቜውን ኃጢኣት በሰውነቱ በመቅጣት ዹሕግን ትእዛዝ ኹፈጾመ በኋላ ዹዕርቁን ተግባር በወሳኝ መልኩ ኣኚናውኖታልፀ
በክርስቶስ ቀዛነት ዹሆነው ይህ ዕርቅ በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ ዹተወደደ ነበሹና እሱ ራሱ በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ኚራሱ ጋር ኣስታሚቀፀ
ለዚህም ነው ተበዳይ እሱ፣ ቀዛዊ መሥዋዕት ሆኖ ዹቀሹበው እሱ፣ ኣስታራቂ እሱ፣ ታራቂ እሱ ሆኖ ዚምናገኘውፀ ለሱ ዚሚሳነው ነገር ዹለምና ለኛ ግር ዹሚል ቢመስልም ለሱ ቀላል ነበሚ።
በዚህ ዹዕርቅ ተግባር ሰውና እግዚአብሔር፣ ሰውና መላእክት፣ ሰውና ሰው፣ ነፍስና ሥጋ ታርቀው በይፋ ተገናኙፀ በኅብሚትና በኣንድነትም መኖር ቻሉፀ በቀኙ ለተሰቀለው ሜፍታ “ዛሬውኑ ኹኔ ጋር በገነት ትኖራለህ” ዹሚለው ቃለ ምሕሚትና “ኣባት ሆይ፥ ነፍሮን በእጅህ ኣደራ እሰጣለሁ” ዹሚለው ቃለ ኣማሕፅኖ ዚዕርቁ፣ ዚግንኙነቱና ዚኣንድነቱ ማሳያ ኣስሚጅ ና቞ው።
ስቅለተ ክርስቶስ ነፍሶቻቜን ወደ ግዞት ቀት ሳይሆን ወደ ገነት እንዲገቡ፣ ዹሚቀበላቾውም ራሱ እግዚአብሔር እንዲሆን ያስቻለ ታላቅ መለኮታዊ ፍጻሜ ነውፀ
እኛ “ክርስቶስ መድኃኒታቜን ነውፀ ኣድኖናል” ብለን በልበ ሙሉነት ዚምንመሰክሚው፣ እሱም “ሰላሜን ሰጠኋቜሁ” ብሎ ዚሚያሚጋጋን በመሰቀሉ ይህንን ውጀት ስላስገኘልን ነው።
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ዚቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት!
ዚድኅነታቜንና ዚሰላማቜን መሠሚት ዚሆኑትን ዚክርስቶስ ሞትና ትንሣኀ ለዓለም ማኅበሹ ሰብ ዚማብሰርና ዚማሥሚጜ ተግባር ዚቅድስት ቀተ ክርስቲያን ቍጥር ኣንድ ተልእኮ ነውፀ
ነገሹ ሞቱና ነገሹ ትንሣኀው በኣስተውሎት፣ በጥልቀትና በተመሥጊ ስናስተምር በውስጡ ዹምናገኘው ዚዕርቅ፣ ዹሰላምና ዚኣንድነት ምስጢር ነውፀ
እንደ እውነቱ ኹሆነ እኛ ዚክርስቶስ መልእክተኞቜ እንደ ቃሉ ራሳቜንን ክደን በሚጠበቀው መጠን ተልእኮኣቜንን መወጣት ብንቜል ኖሮ፣ ኣሁን በዓለማቜን ዹተፈጠሹው መለያዚትና ግጭት ኣይኖርም ነበርፀ
ቜግሩን ሙሉ በሙሉ ማስቀሚት ባንቜልም በእጅጉ መቀነስና ዓቅሙን ማዳኚም እንቜል ነበርፀ ነገር ግን ተልእኮኣቜንን በኣግባቡ ኣለመወጣት ኣንድ ነገር ሆኖ ዹዓለሙ መሳሪያ ሆነን መገኘታቜን “በዕንቅርት ላይ
” ሆኖ ይስተዋላል።
ይሁንና ኣሁንም ሕዝቡን ወደ ኣንድነት፣ ወደ ፍቅር፣ ወደ ሰላም፣ ወደ ዘላቂ ዚጋራ ጥቅምና ወደ ፈሪሐ እግዚአብሔር ማምጣት ዚጉባኀያቜን ዓቢይ ተግባር ሊሆን ይገባልፀ እነዚህ ካሉ ዚምናጣውም ሆነ ዚሚያመልጠን ዹለምና ነውፀ
ሃገርን በኃላፊነት ተሚክባቜሁ በላዕላዊ፣ በማእኚላዊና በታሕታዊ መዋቅር ዚምትገኙ፣ እንደዚሁም ኣማራጭ ሓሳብ ኣለን ብላቜሁ ዚምትንቀሳቀሱ ልኂቃነ ሃገር ፣ ሁላቜሁም እግዚአብሔርን ኚሚያውቅ፣ ኚሚያመልክና ኚሚፈራ ሕዝብ ዚተገኛቜሁ ናቜሁና በልባቜሁ እግዚአብሔርን ፍሩፀ ድምፁንም ስሙፀ ዚሱ ገንዘብ በሆኑ ፍጡራንም ኣትጚክኑፀ ሰውን መያዝ ዚሚቻለው ኅሊናን በመርታት እንጂ በሌላ ኣይደለምና፣
ዚሕዝቡን ፍላጎትና ዚልብ ትርታ በሚገባ ኣዳምጡፀ ሕዝቡ ዹሚፈልገው በኣንድነትና በእኩልነት መኖር፣ በሰላም ወጥቶ መግባት፣ ፍትሕን ማስፈን፣ ለኑሮው ዹሚበቃ ምጣኔ ሃብትን ማግኘት፣ ዚእምነት ነጻነትና እኩልነት መሚጋገጥ ዚመሳሰሉት ና቞ው።
ሕዝቡ እነዚህ ኚተሟሉለት ተደመጠ ማለት ነውፀ ኹተደመጠ ደግሞ እሱም በበኩሉ ያደምጣልፀ ይኚተላልምፀ
ስለሆነም ለሁሉም ልጆቻቜንና ወገኖቻቜን ዚምናስተላልፈው ወቅታዊ ጥሪ ሁሉንም ቜግሮቻቜን በሰላምና በሰላም ብቻ ለመፍታት ተባበሩ ዹሚል ነውፀ ኹዚህ ውጭ ዹሚደሹገው ኣማራጭ ሁሉ ለዘላቂ ሰላማቜን ኣይበጅም እንላለን።
በመጚሚሻምፊ
በቀኖና ቀተ ክርስቲያን መሠሚት ኹበዓለ ትንሣኀ በኋላ በሃያ ኣምስተኛው ቀን ዚሚካሄደው ዓመታዊው ዹሹክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልኣተ ጉባኀ በዛሬው ዕለት ዹተጀመሹ መሆኑን ለሕዝበ ክርስቲያኑና ለመላው ኢትዮጵያውያን እናበስራለን!!!
እግዚአብሔር ጉባኀያቜንን ይባርክ!
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቊቿን ይባርክ!
ወስብሓት ለእግዚአብሔርፀ
አሜን!!!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘኣኵስም ወዕጹጌ ዘመንበሹ
ተክለ ሃይማኖትፀ
ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም
ኣዲስ ኣበባ – ኢትዮጵያ

ዚ፳፻ ፲ወ፰ ዓ/ም ዹርክበ ካህናት ዚቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኀ ዚጞሎት መርሐ ግብር በመንበሹ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተኹናወነ

ሚያዚያ ፳፯ ቀን ፳፻፲ወ፰ ዓ/ም
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ዚ፳፻ ፲ወ፰ ዓ/ም ዚቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኀ ዚመክፈቻ ጞሎት መርሐ ግብር በመንበሹ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተኚናወነ።
በመንበሹ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በተኹናወነው ዚጞሎት ሥነ-ሥርዓት ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጚጌ ዘመንበሹ ተክለሃይማኖት፣ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ዹጠቅላይ ቀተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ዚደቡብ ምዕራብ ሾዋና ዹሾገር ኹተማ አህጉሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆርስ ዚቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጾሐፊና ዚራያ ሀገሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ዚጠቅላይ ቀተክህነት ዚዚመምሪያውና ዚድርጅቶቹ ኃላፊዎቜ ተገኝተዋል።
ዚግንቊት ፳፻ ፲ወ፰ ዓ/ም ዚቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኀ በቋሚ ሲኖዶስ ተዘጋጅተው በአጀንዳ አሪቃቂ ኮሚ቎ ታይተውና በምልዓተ ጉባኀ ተመርምሹው በሚጞድቁ አጀንዳዎቜ ዙሪያ በጥልቀት በመወያዚት ልዩ ልዩ ውሳኔዎቜን ያስተላልፋል።