የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ትርጓሜ ምስክር ት/ቤት በባሕር ዳር ከተማ ለሚያስገነባው “የሕክምና መንደር” የመሠረት ድንጋይ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተቀመጠ።

July 4, 2026
ሰኔ ፲፱ቀን ፳፲፰ ዓ.ም
የገዳሙ ጉባኤ ቤት “ሰንፔር” ሲል ለሰየመው “የሕክምና መንደር” ግንባታ 30,000 ካሬ ቦታ ከባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ሰኔ ፲፱ቀን ፳፲፰ ዓ.ም መረከቡም ይታወቃል።
“የሕክምና መንደሩ” የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥ መርሐ ግብር ላይ እንደተገለፀው የሕክምና መንደሩ ዋና ዓላማ ለሁሉም የሰው ልጆች በምሕረት፡ እምነትን፣ ዘርንና ማንነትን ሳይለይ፣ ለሰው ልጅ ሁሉ የሚታዘንበት የምሕረት ማረፊያ እንዲሆንና ሁለንተናዊ ፈውስ ለመስጠት ነው ተብሏል።
ከዚህ በመለስ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በሀገራችን የነበራትን የጥበብ ታሪክ በዘመናዊ የምርምር ዐቅም ለማስቀጠል “የሕክምና መንደሩ” ከፍ ያለ ሚና እንደሚኖረው ተገልጿል።
ሌላው ቤተ ጉባኤው “የሕክምና መንደር” የሚያስገነባው የቅድመ ጋብቻ ትምህርት ለመስጠት የባለትዳሮች ደግሞ የልጅ አስተዳደግ ሥልጠና ለመስጠት እንዲሁም በሱስ የተጎዱ ወገኖቻችንን ለመንከባከብና እንደገና አዲስ ሰውነት እንዲያገኙ በማድረግ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለሀገራችን በጎና ባለ አእምሮ ትውልድ ለመፍጠር መሆኑን ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶች እና የእናቶች አንድነት ገዳም የ ፬ቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምስክር መምህር ተናግረዋል።
ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን አክለውም “የሕክምና መንደሩ” ሀገር በቀል የሕክምና ማዕከል እንዲሁም የሕክምና ኮሌጅና የምርምር ማዕከል ያካተተ ይሆናልም ብለዋል።
የሕክምና መንደሩ ወደ መሬት እንዲወርድ ለተባበሩት ሁሉ ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ “የጉባኤ አምላክ ይጠብቅልን” ሲሉ አመስግነዋል።
“የሕክምና መንደሩ” መሠረት ድንጋይ የማስቀመጥ መርሐ ግብር ላይ ብፁዕ አቡነ አቡነ ሚካኤል የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የባሕር ዳር እና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዘካርያስ የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የስካንዲቪያን እና የኖርዲክ አገራት አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የሥራ ሓላፊዎች ፣ የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣ ካህናት አባቶች ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር የሥራ ሓላፊዎች ተገኝተዋል።የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ትርጓሜ ምስክር ት/ቤት በባሕር ዳር ከተማ ለሚያስገነባ “የሕክምና መንደር” የመሰረት ድንጋይ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተቀመጠ።
የገዳሙ ጉባኤ ቤት “ሰንፔር” ሲል ለሰየመው “የሕክምና መንደር” ግንባታ 30,000 ካሬ ቦታ ከባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ሰኔ ፲፱-፳፲፰ ዓ.ም መረከቡም ይታወቃል።
“የሕክምና መንደሩ” የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥ መርሐ ግብር ላይ እንደተገለፀው የሕክምና መንደሩ ዋና ዓላማ ለሁሉም የሰው ልጆች በምሕረት፡ እምነትን፣ ዘርንና ማንነትን ሳይለይ፣ ለሰው ልጅ ሁሉ የሚታዘንበት የምሕረት ማረፊያ እንዲሆንና ሁለንተናዊ ፈውስ ለመስጠት ነው ተብሏል።
ከዚህ በመለስ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በሀገራችን የነበራትን የጥበብ ታሪክ በዘመናዊ የምርምር ዐቅም ለማስቀጠል “የሕክምና መንደሩ” ከፍ ያለ ሚና እንደሚኖረው ተገልጿል።
ሌላው ቤተ ጉባኤው “የሕክምና መንደር” የሚያስገነባው የቅድመ ጋብቻ ትምህርት ለመስጠት የባለትዳሮች ደግሞ የልጅ አስተዳደግ ሥልጠና ለመስጠት እንዲሁም በሱስ የተጎዱ ወገኖቻችንን ለመንከባከብና እንደገና አዲስ ሰውነት እንዲያገኙ በማድረግ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለሀገራችን በጎና ባለ አእምሮ ትውልድ ለመፍጠር መሆኑን ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶች እና የእናቶች አንድነት ገዳም የ ፬ቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ምስክር መምህር ተናግረዋል።
ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን አክለውም “የሕክምና መንደሩ” ሀገር በቀል የሕክምና ማዕከል እንዲሁም የሕክምና ኮሌጅና የምርምር ማዕከል ያካተተ ይሆናልም ብለዋል።
የሕክምና መንደሩ ወደ መሬት እንዲወርድ ለተባበሩት ሁሉ ቆሞስ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ “የጉባኤ አምላክ ይጠብቅልን” ሲሉ አመስግነዋል።
“የሕክምና መንደሩ” መሠረት ድንጋይ የማስቀመጥ መርሐ ግብር ላይ ብፁዕ አቡነ አቡነ ሚካኤል የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የባሕር ዳር እና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዘካርያስ የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የስካንዲቪያን እና የኖርዲክ አገራት አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የሥራ ሓላፊዎች ፣ የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣ ካህናት አባቶች ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር የሥራ ሓላፊዎች ተገኝተዋል።
የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት
©EOTC tv
Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/pr0000025.jpeg 207 448 eotceth https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg eotceth2026-07-04 10:13:392026-07-04 10:13:39የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ትርጓሜ ምስክር ት/ቤት በባሕር ዳር ከተማ ለሚያስገነባው “የሕክምና መንደር” የመሠረት ድንጋይ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተቀመጠ።
Search Search

Recent Posts

  • የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ትርጓሜ ምስክር ት/ቤት በባሕር ዳር ከተማ ለሚያስገነባው “የሕክምና መንደር” የመሠረት ድንጋይ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተቀመጠ።
  • የላሊበላ ቅርሶችን ለመጠበቅ የሚያስችል ውይይት ሊደረግ መሆኑ ተገለጸ።
  • በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (አይሲቲ) እና የዲጂታል ሽግግር አማካሪ ኮሚቴ ለአስተዳደር ጉባኤው በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ እየሠራ ያለውን የተለያዩ የጥናት ሰነዶች አቀረበ፡፡
  • የቤቶችና ሕንጻዎች ልማት ድርጅት ሠራተኞቹን አመሰገነ።
  • “ተመራቂዎች በየተሰማሩበት የስምሪት መስክ ሁሉ እንደ መብራት ሊያበሩ ይገባል” ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ

Archives

  • July 2026
  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የላሊበላ ቅርሶችን ለመጠበቅ የሚያስችል ውይይት ሊደረግ መሆኑ ተገለጸ። Link to: የላሊበላ ቅርሶችን ለመጠበቅ የሚያስችል ውይይት ሊደረግ መሆኑ ተገለጸ። የላሊበላ ቅርሶችን ለመጠበቅ የሚያስችል ውይይት...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top