የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች በጠቅላይ ቤተ ክህነት እየተገነባ ያለውን ዘመናዊ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ የግንባታ ሂደትን ጎበኙ።

July 18, 2026
ሐምሌ ፲ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም.| ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
“የሕዝብ ግንኙነት ስኬት ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት” በሚል መሪ ቃል ለአገር አቀፍ የአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች የተዘጋጀው ፫ኛው ዙር ሥልጠና በዛሬው ዕለትም ተሰጥቶ የዋለ ሲሆን፤ ሠልጣኞቹ የዕለቱን መርሐ ግብር ካጠናቀቁ በኋላ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ ውስጥ እየተገነባ ያለውን ሁለገብ ዘመናዊ የስብከተ ወንጌል አዳራሽን የግንባታ ሂደትን ጎብኝተዋል።
ይህ ጉብኝት የተከናወነው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሥራ አስኪያጅና የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በተገኙበት የተከናወነ ሲሆን፤ ከብፁዕነታቸው ጋር በመሆን ሠልጣኞቹን ያስጎበኙት ኢንጂነር ሔኖክ ልዑልሰገድ ናቸው። ኢንጂነር ሔኖክ በጉብኝቱ ወቅት በዋናነት ትኩረት ስለተሰጠውና ዘመናዊ መገልገያዎችን ስላካተተው ዓለም አቀፍ የስብሰባ አዳራሽ ግንባታ ሂደት፣ እንዲሁም ስለ ሕንጻው አጠቃላይ ይዘትና ሁኔታ ዝርዝር ማብራሪያዎችን ለሰልጣኞቹ በሰፊው አቅርበዋል።
በማብራሪያው ላይ እንደተገለጸው፤ ይህ በ2,500 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈው ግዙፍና ዘመናዊ ሕንጻ በአንድ ጊዜ 2,500 ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል ትልቅ አዳራሽ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ መደበኛ ስብሰባ አዳራሽ፣ በ282 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ አነስተኛ የበታች ኮሚቴዎች መሰብሰቢያ አዳራሽ፣ የክብር እንግዶች ማረፊያ፣ ዘመናዊ ምግብ ቤት እንዲሁም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ በርካታ ቢሮዎችን ያካተተ ነው። ሕንጻው ከመደበኛ የግንባታ ጥበቡ ባሻገር እስከ 30 ቋንቋዎችን በቅጽበት መተርጎም የሚችል የትርጉም ክፍል፣ ዘመናዊ ዲጂታል መጻሕፍት ማከማቻ፣ የጋዜጣዊ መግለጫ መስጫ ክፍል፣ ከውጭ የሚመጣን ድምፅ ሙሉ በሙሉ መከላከል የሚችል አሠራር፣ ዘመናዊ የሙቀትና ቅዝቃዜ ማስተካከያ አየር መቆጣጠሪያ እና ደረጃቸውን የጠበቁ የዕይታ ስክሪኖች የተገጠሙለት በመሆኑ የዘመኑ ግብዓቶች የተሟሉለት መሆኑ ተገልጿል። ከዚሁ ጋር ተያይዞም 16 ሰዎችን በአንዴ መጫን የሚችሉ ሁለት የሰው ማደያ ሊፍቶች፣ ለ90 ሰዎች የሚሆኑ ዘመናዊ መጸዳጃ ቤቶች፣ የተፈጥሮ አካባቢ ጥበቃን ያማከለ ሀገር በቀል ዕፅዋት ልማት፣ የከርሰ ምድር ውሃ አቅርቦት እና ከ300 በላይ መኪናዎችን በአንዴ ማቆም የሚችል ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያ ሥፍራ ተዘጋጅቶለታል።
የዕለቱ ከፍተኛ መርሐ ግብር የተከናወነው ከጉብኝቱ መልስ ሲሆን፤ የቤተ ክርስቲያኒቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ለሥልጠናው ተሳታፊዎች እጅግ ታሪካዊና አባታዊ የሆነ ቃለ ምዕዳንና መመሪያ አስተላልፈዋል። ብፁዕነታቸው በቃለ ምዕዳናቸው፤ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች በተሠማሩበት አገልግሎት ሁሉ ሳይታክቱና ሳይሰለቹ በርትተው እንዲሠሩና ቤተ ክርስቲያናቸውን በጽናት እንዲያገለግሉ አጥብቀው አሳስበዋል። በተለይም የሕዝብ ግንኙነት ሥራ ዋነኛ ዓላማ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እውነተኛ መልእክት፣ ታሪክና ሥርዓት ለምዕመናን ያለምንም መቆራረጥና ሳይዛባ በትክክል ማድረስ መሆኑን የገለጹት ብፁዕነታቸው፤ ኃላፊዎቹ በዕውቀትና በታማኝነት ተጋድሏቸውን እንዲወጡ አባታዊ መመሪያ ሰጥተዋል። በመጨረሻም ብፁዕነታቸው ለአህጉረ ስብከቱ የሕዝብ ግንኙነት መሪዎች ለቀጣይ የሥራ ዘመናቸው ስኬትና ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን አንድነት የሚሆን ሰፊ ጸሎትና መንፈሳዊ ቡራኬ በመስጠት መርሐ ግብሩን በታላቅ ክብር አጠናቀዋል።
Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/pr000038.jpeg 336 448 eotceth https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg eotceth2026-07-18 00:44:562026-07-18 00:44:56የአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች በጠቅላይ ቤተ ክህነት እየተገነባ ያለውን ዘመናዊ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ የግንባታ ሂደትን ጎበኙ።
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ወቅታዊ ጉዳዮች በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።
  • ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት የተሰሩ የልማት ሥራዎችን ተመለከቱ፤ በድሬዳዋ መልካ ጀብዱ መካነ ቅዱሳን አቡነ አረጋዊ ወአርሴማ ገዳም የሚገኙ እጓለማውታ ሕጻናትን ጎበኙ።
  • የድሬዳዋ ሳባ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ያስገኘባው ባለ ሦስት ወለል ሁለገብ ሕንጻ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና በብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጸሎተ ቡራኬ በዛሬው ዕለት ተመረቋል።
  • የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ሕንጻ ቤተክርስቲያን ዕድሳት ተጠናቆ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው ተባረከ።
  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ ወደ ቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ተጓዘ።

Archives

  • July 2026
  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የቤተ ክርስቲያን የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች ሥልጠና በአሰልጣኞች ማጠቃለያ ሁለተኛ ቀኑን አጠናቀቀ Link to: የቤተ ክርስቲያን የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች ሥልጠና በአሰልጣኞች ማጠቃለያ ሁለተኛ ቀኑን አጠናቀቀ የቤተ ክርስቲያን የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች... Link to: የቤተክርስቲያንን የሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት በዘመናዊ መንገድ ለማጠናከር የሚያስችል የምክክርና የሥልጠና መርሐ ግብር የአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች በተገኙበት ተካሔደ። Link to: የቤተክርስቲያንን የሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት በዘመናዊ መንገድ ለማጠናከር የሚያስችል የምክክርና የሥልጠና መርሐ ግብር የአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች በተገኙበት ተካሔደ። የቤተክርስቲያንን የሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top