የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት መጪውን በዓል ምክንያት በማድረግ ለቤተ ክርስቲያኗ ከፍተኛ መሪዎች «የእንኳን አደረሳችሁ» ስጦታ አበረከተ።

ጳጉሜ ፪ ቀን ፪፻ ፲ወ፰
አዲስ-አበባ-ኢትዮጵያ
ስጦታው ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፣ለብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የሸገር ከተማና የደቡብ ምዕራብ ሸዋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም የበላይ ኀላፊ ለብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅርሳ ቅርስ ወመዘክርና የማኅበራት ክትትል መምሪያዎች የበላይ ኃላፊ ለብፁዕ አቡነ ሳሙኤል የልማት ኮምሽንና የድርጅቱ የበላይ ሊቀ ጳጳስ የቀረበ ሲሆን፤ ተቋሙ ለቤተ ክርስቲያኗ ከፍተኛ መሪዎችና አባቶች ያለውን ጥልቅ አክብሮት፣ ፍቅርና የመታዘዝ መንፈስ የሚያንጸባርቅ ነው ተብሏል።
ስጦታው ድርጅቱ የቤተ ክርስቲያኗን ሀብትና ንብረት በጥንቃቄ የመጠበቅና የማልማት ኃላፊነቱን በሚወጣበት እንቅስቃሴ ውስጥ አባቶች ላደረጉለት ያልተለየ ድጋፍ፣ አባታዊ መመሪያና ጸሎት የታላቅ ምስጋና መግለጫ እንደሆነ ተገልጿል።
ይህ የበዓል እንኳን አደረሳችሁ ስጦታ የማበርከትና ከአባቶች ቡራኬ የመቀበል ሥነ ሥርዓት ድርጅቱ አምናም ሲፈጽመው የቆየና እንደ መልካም ተቋማዊ ባህል አጠናክሮ የያዘው ተግባር ነው። በየዓመቱ በበዓላት ወቅት አባቶችን ማሰብ፣ ማክበርና መንፈሳዊ ቡራኬያቸውን መቀበል የተቋሙ ጽኑ እምነት እንደሆነና ይህ በጎ ልማድ ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተጠቅሷል።
በስጦታ ማበርከቱ ሥነ-ሥርዓት ወቅት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ እስከአሁን ድርጅቱ ያደረገውን በጎ አፈጻጸም አድንቀው አዲስ ዓመት አዲስ የሚሆነው አዲስ ነገር ሲሠራበትና ቤተክርስቲያንን ከፍከፍ ስናደርግበት ነውና በአዲሱ ዓመት ይህንኑ አድርገን እስከ አሁን ከምናውቀው በተሻለ አፈጻጸም እንደምትመጡ አምናለሁ ብለዋል።
በመቀጠልም ብፁዕ ጠቅላይ ሥራአስኪያጁ ባለፈው አንድ ዓመት ድርጅቱ ያሳየው ትጋት እጅግ የሚያስደንቅ መሆኑን ገልጸው ወደፊትም ቢሆን እኛን ያሰባሰበችን ቅድስት ቤተክርስቲያንን ማስቀደም ግድ ስለሆን እርሷን አስቀድመን ጠንክረን መሥራት ይገባናል ብለዋል።
ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው በበኩላቸው የድርጅቱ መነቃቃትና ትጋት በዚሁ እንዲቀጥል አሳስበው ለተደረገው የመልካም ምኞት ስጦታን አመስግነዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከሸማኔ መወርወሪያ በሚፈጥነው ጊዜ ውስጥ እየኖርን ለሥራ አለመፍጠን አይቻልምና ልክ እንደ 2018ዓ.ም ቀጣዩን ዓመትም በዚሁ ልክ እየሠራን ልናሳልፍ ይገባል ያሉት ደግሞ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል የድርጅቱ የበላይ ሊቀ ጳጳስ ናቸው።
በመጨረሻም አባቶች በደርጅቱ የተበረከተላቸውን ስጦታ በደስታ የተቀበሉ ሲሆን፤ ድርጅቱ የቤተ ክርስቲያኗን ንብረቶች በማልማትና ገቢዋን በማሳደግ በኩል እያከናወነ ያለውን እንቅስቃሴ አድንቀዋል። አባቶች አክለውም ተቋሙ በቀጣይ በዘመናዊ አሠራርና በግልጽነት የታገዘ የልማት ሥራ በማከናወን የድርሻውን እንዲወጣ አባታዊ መመሪያና ቡራኬያቸውን አስተላልፈዋል።
© ኢኦተቤክ_ቤሕአልድ

የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት ላለፉት ሁለት ዓመታት ያሰተማራቸውን ደቀ መዛሙርት አስመረቀ !!!

ጷጉሜን 01 ቀን 2018 ዓ/ም
የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት ላለፉት ሁለት ዓመታት ያሰተማራቸውን ደቀ መዛሙርት በዛሬው ዕለት አስመረቀ
በመርሐ ግብሩም ላይ መጋቤ ኅሩያን አባ ኤልያስ በልሁ የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም አስተዳዳሪ ፣ መልዓከ ብርሃናት ዶ/ር አባ ጴጥሮስ ሰለሞን የገዳሙ ስብከተ ወንጌል እና የአስተዳደር ቦርድ ፀሐፊ ፣የገዳሙ አበው መነኮሳት ፣ የተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት ነባር አባላት እና የሥራ አስፈጻሚዎች ፣ ተመራቂ ደቀ መዛሙርት እና የተመራቂ ደቀ መዛሙርት ቤተሰቦች በተገኙበት ተከናውኗል ።
በዕለቱም በመምህር አባ ገብርኤል አያሌው የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ስብከተ ወንጌል አገልጋይ “ተዘከሩ መኳንንቲክሙ ዘነገሩክሙ ቃለ እግዚአብሔር” የእግዚአብሔርን ቃል የነገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ ዕብራውያን 13፣8 ። በሚል ኃይለ ቃል መነሻ በማድረግ የሚያረጋጋና የሚያጸና ትምህርተ ወንጌል ተሰጥቷል ።
ተማራቂ ደቀ መዛሙርት መሠረታዊ የሃይማኖት ትምህርቱ በማዕከላውያን ክፍል ፣ መስማት በተሳናቸው ክፍል ፣ በቅዳሜ እና እሑድ ፣ በእሑድ ብቻ ፣ ሰኞ እና ረቡዕ በማታ መርሐ ግብር ፣ ሰኞ እስከ ሐሙስ በምሳ ሰዓት እንዲሁም በርቀት በአጠቃላይ ከ219 በላይ ትምህርታቸውን ለ12ወራት እንዲሁም ለሁለት ዓመታት የተከታተሉ መሆኑ ተገልጿል ።
ተመራቂዎች በለፉት ዓመታት
፩• ሀልዎተ እግዚአብሔር እና ሥነ ፍጥረት
፪• ኦርቶዶክሳዊ የስብከት ዘዴ
፫• አምሥቱ አእማደ ምሥጢራት
፬ • የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት
፭ • ነገረ መንፈስ ቅዱስ ፣ ነገረ ማርያም ፣ነገረ ቅዱሳን ነገረ ሃይማኖት ፣ነገረ ድኅነት
፮• ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር
፯ • ዕቅበተ ዕምነት
፰ • ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን
፱• የቤተ ክርስቲያን ታሪክ በኢትዮጵያ እና በዓለም መድረክ
፲•ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ትምህርቶችን ተምረው አጠናቀዋል ።
የገዳሙ ተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት እጅግ አንጋፋ እና ስመጥር ከመሆኑም በላይ ብዙ የቤተ ክርስቲያን እና የሀገር ባለውለታውችን ያፈራ፣ ወንጌልን ለሁሉም ይደርስ ዘንድ መስማት ለተሳናቸው ወገኖች በምልክት ቋንቋ የሚያስተምር እንዲሁም በአርድዕት ጉባኤ የነገ የቤተ ክርስቲያን ተረካቢ ሕጻናትን የአብነት ትምህርት በማስተማር ዋነኛ ዓላማ አድርጎ እየሠራ ያለ ባለታሪክ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው።
ባለፉት ዓመታት በሰንበት ትምህርት ቤቱ ያሳለፍናቸው ግዚያት ያካበትነው እውቀት ለነገው ህይወታችን ትልቅ መሠረት ነው ለዚህ ቀን ያበቃን ፈጣሪ ይመስገን ሲሉ ተመራቂ ተማሪዎች ተናግረዋል ።
በመርሐ ግብሩ ላይ በተመራቂ ተማሪዎች የወረብ ዝማሬና ስነፅሁፍ ያቀረቡ ሲሆን ለመምህራን፣ለደረጃ ተማሪዎች የምስክር ወረቀትና ሽልማት ተሰጥቷል።
የገዳማችን አስተዳዳሪ መጋቤ ኅሩያን አባ ኤልያስ በልሁ እንኳን ደስ ያላችሁ በማለት መልዕክት ያስተላለፍ ሲሆን የተመራቂዎች የመመረቅ ዋና ዓላማ የራቁትን ለመሰብሰብና ያልፀኑትን ለማፅናት እንደሆነ በመግለፅ በአገልግሎት እንዲተጉ እና እንዲጠነክሩ አሳስበው በጸሎት የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል ።©ምስካየኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም

ጳጉሜ የሚለው ስያሜ ‹‹ኤፓጉሜኔ›› ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ‹‹ጭማሪ›› ማለት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭)

ወርኃ ጳጉሜን እንደሌሎቹ ወራት ፴ ቀናት ሳይሆን በአራት ዓመት አንዴ ማለትም በዘመነ ዮሐንስ ስድስት ቀናት ሲኖራት በዘመነ ማርቆስ፣ በዘመነ ሉቃስና በዘመነ በማቴዎስ ደግሞ አምስት ቀናት ብቻ ይኖራታል፤ ነገር ግን የዓመቱ ዐሥራ ሦስተኛ ወር ተደርጋ ትቆጠራለች፡፡
ወርኃ ጳጉሜን ካሳለፍነው ዓመት ወደ አዲሱ ዓመት፣ ከዘመነ ክረምት ወደ ጸደይ መሸጋገሪያ በመሆኗ የዓለም ፍጻሜ (የዳግም ምፅአት) መታሰቢያ ተደርጋም ትታሰባለች፡፡
ጳጉሜን ከዘመነ ክረምት ወደ ጸደይ መሸጋገሪያ እንደሆነች ሁሉ ዳግም ምጽአት ከምድራዊ ሕይወት ወደ ዘለዓለማዊ ሕይወት መሸጋገሪያ ናት፡፡ ጳጉሜን የክረምት ማብቂያ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም እንዲሁም የዚህ ዓለም ኑሮ ማብቂያ ናት፡፡ ወርኃ ጳጉሜን አዲሱን ዓመት ለመቀበል የዝግጅት ጊዜ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም ጻድቃን አዲሲቷን ምድር (መንግሥተ ሰማያትን) ለመውረስ የበቁትን ‹‹እናንተ የአባቴ ብሩካን ዓለም ሳይፈጠር የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ›› የሚባሉባት ዕለት ናት፡፡
በዚህም የተነሣ ብዙ ምእመናን በወርኃ ጳጉሜን በጾምና በጸሎት ይተጋሉ፡፡ ከዚህም ጋር ተያይዞ በቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ በዓል በጳጉሜን ሦስት ሰማያት የሚከፈቱበት (ርኅዎተ ሰማይ) በመሆኑ በዚህች በተከበረችው ዕለት ምእመናን ጸሎታቸው ያርግላቸው ዘንድ ከምን ጊዜውም በበለጠ ተግተው ይጸልያሉ፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን የተባልን የእኛን ጸሎታችንን በምልጃቸው የሚያሳርጉልን ቅዱሳን መላእክትም መሥዋዕቱን የሚያሳርጉበትና የአምላካችንን ምሕረት ቸርነት ለሰው ልጆች የሚያወርዱበት ዕለት ነው፡፡

የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ሠራተኞች ለተባባሪ ፕሮፌሰር ለብፁዕ አቡነ ፊልጶስ(ዶ/ር) የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በመመረቃቸው ልዩ የደስታና የምስጋና መርሐ ግብር አካሄዱ።

ነሐሴ ፴ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት እና የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለተባባሪ ፕሮፌሰር ለብፁዕ አቡነ ፊልጶስ(ዶ/ር) በሰሜን አሜሪካ ከሚገኘው Liberty University በEducational Leadership (Doctor of Education) በከፍተኛ መዐርግ የዶክተሬት ዲግሪያቸውን በማጠናቀቃቸው የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ መምህራን፣ ሠራተኞች፣ የዩኒቨርሲቲው ቦርድና ሴኔት አስተዳደር ደስታቸውን ገልጸዋል።
መልአከ ኃይል አባ ጽጌ ደንግል የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚደንት ለእንግዶች የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል። በመልእክታቸውም በብፁዕ አቡነ ፊልጶስ (ዶ/ር) እና በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ ስም፣ የደስታ፣ የምስጋናና የክብር በዓል እንኳን በሰላም መጣችሁ ብለዋል። አያይዘውም ዛሬ በዚህ ታላቅ ቀን እዚህ ተሰብስበን ያለነው የዩኒቨርሲቲያችን መሪና አባት፣ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ (ዶ/ር)፣ በአሜሪካ ከሚገኘው ሊበርቲ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት አመራር የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በስኬት በማጠናቀቃቸው የምርቃታቸውን ደስታ በጋራ ለመጋራት መሆኑን ገልጸዋል።
“ለእኛ ለዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ይህ የደስታ ቀን ከመደበኛ የምርቃት በዓል የተለየ ትርጉም አለው” ያሉት መልአከ ኃይል “ዛሬ የምናከብረው የአንድ ሰው የትምህርት ስኬት ብቻ ሳይሆን፣ ለዩኒቨርሲቲያችን፣ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሚመጣው ትውልድ የሚተላለፍ የዕውቀትና የተስፋ ምንጭ ነው።እኛ የምንከተለውን የትምህርትና የአመራር መንገድ በተግባር የሚመሰክር የዕውቀት፣ የጥበብና የትጋት ፍሬ ነው” በማለት አብራርተዋል።“የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ዛሬ በብፁዕነትዎ ስኬት እጅግ ደስ ብሎናል። ያገኙት ትምህርት፣ የጨመሩት ዕውቀትና የተጎናጸፉት የዶክትሬት ደረጃ ለእርስዎ የስኬት አክሊል ብቻ ሳይሆን፣ ለዩኒቨርሲቲያችንም ትልቅ አቅምና ክብር የሚጨምር ነው። ለእኛ ደግሞ የተሻለ ነገን የሚያመለክት ተስፋ በመሆኑ፤ ይህ ስኬት የብፁዕነትዎ ብቻ ሳይሆን፣ የቤተ ክርስቲያናችንና በተለይም የዩኒቨርሲቲያችን ማኅበረሰብ የጋራ ደስታና ኩራት ነው” በማለት ገልጸዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ የብፁዕነታቸውን የሕይወት ታሪክ የሚያስረዳ ፍኖተ ሕይወት መጽሔት እና ከአሜሪካ እስከ ጂንካ የሚል ዘጋቢ ፊልም ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የዩኒቨርሲቲውን ከምሥረታ ጀምሮ አሁን የደረሰበትን ደረጃ የሚያሳይ ዐውደ ርዕይ ቀርቧል። በዐውደ ርዕዩ በ፲፱፴፯ ዓም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተመሠረተው ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ከመጀመሪያው የካህናት ማሠልጠኛ ጀምሮ እስከ ዘመናዊው ዩኒቨርሲቲ ድረስ ተቋሙ በርካታ ሊቃውንት፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እንዳፈራ፣ ራሱንም በትምህርት እያሳደገ እንደመጣ የሚሳይ ነው፡፡
ፕሮፌሰር አባ ኃይለ ገብርኤል ግርማ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት የብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የዶክትሬት ዲግሪ መመረቂያ ጽሑፍ ዳሰሳ ጥናት አቅርበዋል። በዳሰሳ ጥናት እንዳብራሩት፡- የብፁዕ አቡነ ፊልጶስን (ዶክተር፣ ተባባሪ ፕሮፌሰር) የላቀ የትምህርት ስኬትን በታላቅ ደስታ በማክበር ብፁዕነታቸው ከስድስት ዓመታት በላይ ትጋት በተሞላ ጥናትና፣ ምርምር እንዲሁም በጽናት መንፈስ ሰሜን አሜሪካ ቨርጂንያ ከሚገኘው ከታዋቂው ከሊብርቲ ዩኒቨርሲቲ (Liberty University) በትምህርት ሥራ አመራር ዘርፍ የዶክትሬት (Ed.D.) ዲግሪያቸውን በስኬት በዚሁ ዓመት አጠናቀዋል። የብፁዕነታቸው የዶክትሬት ማሟያ ጥናታዊ ጽሑፍ (Dissertation) ርዕስም፦ Servant Leadership in the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church: The Lived Experiences of Work Engagement and Spirituality. – (አገልጋይ መሪ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በአገልግሎት ተሳትፎ እና በመንፈሳዊነት ላይ የተመሠረተ የሕይወት ተሞክሮ) የሚል መሆኑን ገልጸዋል፡፡
“የመመረቂያ የጥናት ጽሑፉ ሦስት ዋና ዋና የምርምር ክፍተቶችን ለይቶ አሳይቷል” የሚሉት ፕሮፌሰር እነዚህም፡- አገልጋይ መሪነትን በኢኦተቤ በሥራ ላይ ባሉ ኃላፊዎች በተኖረ የሕይወት ልምድ በኩል የሚመረምሩ ተግባራዊ ጥናቶች አነስተኛ መሆኑን ተጠቁሟል። ከዚህ ቀደም በዚህ ዘርፍ የተጠኑ ጥናቶች አለመኖሯቸው እነዚህም የምርምር ክፍተት መሆኗቸው ተገልጿል። የጥናቱ ዋና አስተዋፅኦ አገልጋይ መሪነትን፣ የሥራ ተነሣሽነትን እና መንፈሳዊነትን በኢኦተቤ ዐውድ ውስጥ ማቀናጀቱ አስፈላጊ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
በአጠቃላይ የብፁዕነታቸው የመመረቂያ ማሟያ ጥናት ጽሑፉ አስፈላጊና በበቂ ሁኔታ ያልተጠናን ርዕስ የሚዳስስ መሆኑን በዳሰሳ ጥናታቸው አሳይተዋል፡፡ የጥናቱ ጥንካሬም አገልጋይ መሪነትን በቀላሉ የውጫዊ የመሪነት ንድፈ-ሐሳብን ከመተግበር ይልቅ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መሪዎች የተኖረ የሕይወት ልምድን መመርመሩ ነው። የአገልጋይ መሪነት፣ የሥራ ተነሣሽነት እና የመንፈሳዊነት ቅንጅት በሥራ ዘርፎች መካከል ያለውን የምርምር አስተዋፅኦን ያጠናክራል። ከሁሉም በላይ ጥናቱ ኦርቶዶክሳዊ ነገረ-ሰብእ (Anthropology)፣ ቤተ ክርስቲያናዊ አስተምህሮ እና መንፈሳዊነት የመሪነትን ትርጉምና ትግበራ እንዴት እንደሚቀርፁ ያሳየ ነው፡፡ ስለሆነም የጽሑፉ አስተዋጽኦ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውስጥ አገልጋይ መሪነትን ከመለየት አልፎ፣ መሪነትን እንደ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎት፣ መንፈሳዊ እድገት እና በክርስቶስ ማዕከልነት ያለው ጥሪ አድርጎ የሚያስረዳ መሆኑን የዳሰሳ ጥናታቸው አሳይቷል፡፡
ተባባሪ ፕሮፌሰር ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ(ዶ/ር) በአዳራሹ ለተገኙት በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበው የሚከተለውን አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ “የሚማር ሰው ውጤታማ እንዲሆን አምስት ነገሮችን መያዝ አለበት” ብለዋል፡፡ እነዚህንም ሲያብራሩ፡- አንደኛ ግልጽ ዓላማ ማስቀመጥ ለአንድ ተማሪ አስፈላጊ ነው፡፡ ሁለተኛ ጽናትን ራስን መግዛት ሊኖረው ይገባል፡፡ በትምህርት ጉዞ መሰልቸት፣የተለያዩ የሥነ ልቦና ጫናዎች ቢያጋጥሙም ያንን መቋቋም አለበት፡፡ ሦስተኛው ውጤታም የጊዜ አጠቃቀምና ዕቅድ አራተኛ ትክክለኛ የጥናት ስልት መከተል አለበት፤ አምስተኛ የአካባቢና ማኅበራዊ ጉዳዮች ድጋፍ ናቸው፤ ብለዋል፡፡ ብፁዕነታቸው አያይዘውም “ዛሬ በዚህ የተሰባሰብነው ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የዩኒቨርሲቲው መምህራንና ሠራተኞች፣ የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት የመጣችሁ፣ መንፈሳዊ ቤተሰቦቼ ጠቅላላ ይሄ ደስታ የቤተክርስቲያን ደስታ ነው፤ ይህ ውጤት የቤተክርስቲያን ውጤት ነው ብላችሁ አክብራችሁ ስለመጣችሁ በጣም ነው የማመሰግነው” ሲሉ ደስታቸውን ገልጸዋል፡፡
በመጨረሻም ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ባስተላለፉት መልእክት ዛሬ ቤተክርስቲያን ትልቅ እረኛ አባት፣ ምሳሌ የሚሆኑ፣ ጊዜውን የዋጁ አባት አይተናል፡፡ ሁላችንም አባቶች ደስ ብሎናል፡፡ ዛሬ በዚህ ዘመን በጎችን ጠብቅ የተባለው እንዲህ ነው፡፡ የዛሬው በግ ጥበቃ እንደ ትናንቱ አይደለም፡፡ የትናንቱ በትናንቱ ነው የሚታየው፡፡ ዛሬ ደግሞ ከሀገር በቀል ዕውቀት ጋር ዓለም አቀፍ የሆነ የዘመኑ ዕውቀት መያዝ ያስፈልጋል፡፡ የብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ዘመኑን የዋጀ ትምህርት ለትውልዱ ትልቅ ትምህርት ነው፡፡ ቤተክርስቲያናችን በእውነት ትልቅ አባት አግኝታለች፡፡ አባታችን ለሁላችንም አርአያ፣ ምሳሌ ሆነውናል፡፡ ስለዚህ አባታችን እንኳ ደስ አለዎ፣ እንኳን ተወለዱ እንደነዚህ ያሉ አባቶች ደጋግመው ይወለዱ ለሀገር ለቤተክርስቲያን ያስፈልጋሉና ሲሉ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ዕንጦንስ የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ኤፍሬም ቡኖ በደሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል የምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣የጠቅላይ ቤተክህነት የመምሪያና የድርጅት ኃላፊዎች፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ የዩኒቨርሲቲው የቦርድ፣ የሴኔትና የአስተዳደር አባላት፣መምህራንና ሠራተኞችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡©Eotc tv

“መስከረም በአታ የሃያ ሺህ ሰዎች ምሥረታ” በሚል የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም የአብነት ትምህርት ቤት ሕንጻ ግንባታ ድጋፍ ማስጀመሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ በተገኙበት ተሰጠ።

ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓም
ታሪካዊና ጥንታዊው የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም፣ የቤተ ክርስቲያናችንን የትምህርትና የመንፈሳዊ ሀብት መሠረት የሆነውን የአብነት ትምህርት ቤት ዘመናዊ ሕንጻ ለመገንባት የሚያስችል ታላቅ ሀገራዊና መንፈሳዊ ጥሪ አቅርቧል።
ገዳሙ “መስከረም በአታ የሃያ ሺህ ሰዎች ምሥረታ” በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው መርሐ ግብር፣ የመሠረት ድንጋይ ለማኖር የሚሆንና ግንባታውን ለማስጀመር የሚያስችል የ5,000 ብር ቻሌንጅ ማስጀመሩን አስመልክቶ ዛሬ ለጋዜጠኞችና ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ የሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በንግግራቸው በአታ ለማርያም ገዳም ዛሬ ትልቅ ሥራ ለመስራት ጽንስ ላይ ነችና ቅዱስ እግዚአብሔር በሰላም ይገላግላት ዘንድ ልንማጸን እና ልንረዳ ይገባል በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ሊቀ ሊቃውንት ቆሞስ አባ ተክለ ሃይማኖት ወልዱ የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም ዋና አስተዳዳሪ ”ግንባታ” ለበአታ 20 ሺህ ሰዎች ድጋፍን ተከትሎ በመስከረም 3 ቀን 2019 ዓ.ም በበአታ ለማርያም ዕለት የግንባታው የመሠረት ድንጋይ የሚቀመጥ መሆኑን ገልፀዋል ።
በመርሐ ግብሩም ጥንታዊውንና ታሪካዊውን የአብነት ትምህርት ቤት ደረጃውን የጠበቀ ሕንጻ በመገንባት ለተተኪ ትውልድ ሊቃውንት ምቹ የመማርያና የመኖሪያ ቦታ ማዘጋጀት ፤ 20,000 (ሃያ ሺህ) በጎ ፈቃደኛ ምእመናንን እያንዳንዳቸው 5,000 ብር በቻሌንጅ በማሳተፍ ለቦታው የመሠረት ድንጋይ ማኖሪያና ለግንባታ ማስጀመሪያ የሚሆን በቂ ገቢ መሰብሰብን ግብ አድርጎ መነሳቱ ተጥቅሷል።
ይህ ጥንታዊ እና ታሪካዊ ጥሪ የሁላችንንም ተሳትፎ የሚጠይቅ በመሆኑ፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንንና ቅርሶቿን የምንወድ፣ የሃይማኖታችንና የታሪካችን ጥበቃ የሚያስጨንቀን ምእመናን በሙሉ በዚህ በጎ ሥራ ላይ በቻሌንጁ በመሳተፍ የበረከቱ ተካፋይ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
የመሠረት ድንጋይ ማኖር ሥነ ሥርዓትም መስከረም 03 ቀን 2019 ዓ/ም እንደሆነም ተገልጿል። ይህ ታሪካዊ ገዳም የዳግማዊ አጼ ምኒልክ፣ የእቴጌ ጣይቱ እና የንግሥት ዘውዲቱ መካነ መቃብር የሚገኝበትና በርካታ ጥንታዊ ቅርሶችን የያዘ መሆኑ፣ ይታወቃል ።
ግንባታው 4 መሠረታዊ ሕንጻዎችን የያዘ መሆኑም፣ የግንባታ ፍቃድ መውሰዱም እና 2.5 ቢሊዮን ብር የሚፈጅ መሆኑን በተጨማሪም ግንባታው ሲጠናቀቅ 1500 የአብነት ተማሪዎችን እንደሚቀበል ተብራርቷል።
በዕለቱም ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ የሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ፤ አባ ተክለ ሃይማኖት የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም ዋና አስተዳዳሪ ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
እያንዳንዱ የ5,000 ብር አስተዋጽኦ የአብነት ትምህርቱንና የታሪካችንን መሠረት ያጠናክራል።
©የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/

See less
May be an image of dais and text. No photo description available.. May be an image of text that says ‘ំលមស្យ መስከረም በአታ የሃያ ሺህ ሰዎች ም ምሥረታ <ኹላቸውም እረኞች ካልተሰበለል አንችልም። ጋዜጣዊ ጋዜማዊመግለጫ መግለጫ ግንባታ ለበአታ mpt MRUPE ፊኒልት 고그고사수 ያሴንጅ 我的行護护 አስተዋጽም ለማድረ O0 ንንክእና e ቁጥር- 0316 ቴሊ 1C+0950-433333 IC+0950-433333 IIN ንዶች ነባይ 2112675810916’. No photo description available.. May be an image of ‎dais and ‎text that says ‘‎ግንባታ ለበአታ 李街 HWEY 秋 ARGFE teV ንንባታለበአታ ግንባታ ለስኢታ 20 APICIe ንንጌታ ገንሳታለበአታ ለበእታ ግንናታ ለበእታ 秒以 ЛAP AMEPY ال ቴሌ ብር ንግድ ባንክ 1 አዋሽ ባንክ 0 .ዋሽ ባንክ 0 9 ግንባታ ለበአት 品 WETe ALA 14P ግገባታለበኢታ ግንባታ ሰበኤታ ግንባታ ለበአታ 二のぎ +. HPI ሰማርያም 1P ግንባታ ለበአታ ንተቁ “pTc‎’‎

በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት አዘጋጅነት ሲካሄድ የነበረው «ቅድሚያ ለወንጌል» ሥልጠና የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ።

ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት «ቅድሚያ
ለወንጌል» በሚል መሪ ቃል ሲሰጥ የነበረው የሥልጠና መርሐ ግብር በተሳታፊዎች የጋራ የአቋም መግለጫና በሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኃላፊ መምህር ሰለሞን በቀለ ፤ መመሪያ ማጠቃለያ ተጠናቋል።
ከነሐሴ 25 እስከ 28 ቀን 2018 ዓ.ም. ለሦስት ቀናት በቃሊቲ መካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ሲካሄድ በቆየው በዚህ ሥልጠና ላይ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ ዋና ጸሐፊዎች፣ ሒሳብ ሹሞች፣ ቁጥጥርና ገንዘብ ያዦች፣ ምክትል ሊቃነ መናብርት፣ የሚዲያና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች፣ የሰንበት ትምህርት ቤት አመራሮች፣ የወጣት ማኅበራት ተወካዮች፣ እንዲሁም ብዙ ንስሐ ልጆች ያሏቸው ካህናትና ሰባክያነ ወንጌል በሥልጠናው ተሳትፈዋል።
የሥልጠናው ተሳታፊ የሆኑት ሰባክያነ ወንጌል በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ ባወጡት ባለ 12 ነጥብ የጋራ የአቋም መግለጫ መርሐ
ግብሩን ላዘጋጀው ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነትና ለክፍለ ከተማው ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ካህናት ዕዝራ ንዋይ ምስጋናቸውን አቅርበው፣ መሰል አቅምን የሚገነቡ ሥልጠናዎች በቀጣይም ተጠናክረውና በተከታታይነት እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል። አገልጋዮቹ በአብያተ ክርስቲያናትና በገዳማት የተሰጣቸውን
አደራ መሠረት በማድረግ በተሻለ ትጋት፣ ቅንነትና ትሕትና ለማገልገልና በሥልጠናው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር ለመለወጥ ቃል
የገቡ ሲሆን፣ ስብከተ ወንጌል የቤተክርስቲያን ቀዳሚና ዋና ዓላማ መሆኑን በመገንዘብ የአጥቢያ ሰበካ ጉባኤዎችና የበላይ
ኃላፊዎች ለወንጌል አገልግሎት ተገቢውን ትኩረትና ክብር እንዲሰጡ እንዲሁም ምቹ ሁኔታዎችን እንዲፈጥሩ አሳስበዋል።
በተጨማሪም በሰዓት አጠቃቀም ዙሪያ የሚታዩ አለመናበቦችን በመቅረፍ በተለይ በሰንበት ቀናትና በበዓላት ለስብከተ ወንጌል በቂ ጊዜ
እንዲመደብና ሰባክያነ ወንጌል ያለአግባብ ጣልቃ ገብነት አገልግሎታቸውን በሥርዓት እንዲያከናውኑ አስገዳጅ መመሪያ እንዲሰጥ
የጠየቁት ተሳታፊዎቹ፣ በአንዳንድ አጥቢያዎች ለስብከተ ወንጌል የሚመደበው በጀት እጅግ አነስተኛ መሆኑን በመጠቆም በጀቱ
ከአገልግሎቱ ስፋትና አስፈላጊነት ጋር ተመጣጣኝ በሆነ መልኩ ተፈትሾ እንዲስተካከል ጠይቀዋል። በተመሳሳይም የተመደቡ አገልጋዮች የሙያ ብቃት፣ የዕውቀት ዝግጁነትና የአገልግሎት ተነሳሽነት ተፈትሾ አስፈላጊው የማሻሻያና የማብቃት እርምጃዎች እንዲወሰዱ አጽንዖት ሰጥተዋል። በዘመኑ ስብከተ ወንጌልን ለማጠናከር ማኅበራዊ ሚዲያና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በአግባቡና በጥንቃቄ በመጠቀም ከቅድስት ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ሳይወጡ ምዕመናንን ለማገልገልና የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ለማዳረስ ቃል ገብተዋል።
በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መምህር ሰለሞን በቀለ በበኩላቸው ባደረጉት ንግግር፣ ራስን ከመንፈሳዊ አገልግሎት ባሻገር ጽሕፈት ቤቶችን በማደራጀት የሕዝበ ክርስቲያኑንና የአገልጋዩን ሁኔታ ለመፈተሽ መሰል ሥልጠናዎችና የልምድ ልውውጦች እጅግ አስፈላጊ መሆናቸውን ገልጸው፣ መርሐ ግብሩን ግንባር ቀደም ሆኖ ላዘጋጀው የአቃቂ ቃልቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ዋና ሥራ አስኪያጁ አያይዘውም፣ የሀገረ ስብከቱ ትምህርትና ሥልጠና ክፍል በአዲስ መልኩ በ2019
ዓ.ም አዳዲስ ፕሮጀክቶችን አቅዶ፣ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የጀመረውን መልካም ተሞክሮ በማሳደግ በመላው ስምንቱ ክፍላተ
ከተማ ሰፊ ሥልጠናዎችን ለማዘጋጀት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን በሰፊው አብራርተዋል።
አስተዳደራዊ ጉዳዮችን በተመለከተም አስተዳዳሪዎች ሠራተኞችን ያላግባብ ከማገድ፣ ከማባረርና ከደረጃ ዝቅ ከማድረግ ተቆጥበው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ዕርቅን፣ ሥልጠናንና መግባባትን እንዲያስቀድሙ አሳስበዋል።
በአስተዳደር ክፍተቶች ምክንያት አገልጋዮችና
ቤተሰቦቻቸው ለችግር እንዳይዳረጉ ክፍተቶችን በጋራና በፍትሐዊነት ማረም እንደሚገባ አስገንዝበው፣ “የእያንዳንዱ ደብር አስተዳዳሪ
የብቃት መለኪያ ሊሆን የሚችለው በደብሩ ያለውን ካህን እዚያው አሰልጥኖ፣ አስተምሮና አቅፎ ማኖር ሲችል ነው፤ ያኔ ነው ሥልጠናው
ውጤታማ ሆነ የሚባለው” በማለት አስተዳደራዊና መንፈሳዊ መመሪያ ሰጥተዋል።
መርሐ ግብሩ «ቅድሚያ ለወንጌል» የሚለው መሪ ቃል በተግባር፣ በእቅድ፣ በበጀትና በጊዜ አጠቃቀም በመተግበር በጋራ ለመሥራት በመስማማት በጸሎት ተጠናቋል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት «ቅድሚያ ለወንጌል» በሚል መሪ ቃል ሲሰጥ የነበረው የሥልጠና መርሐ ግብር በተሳታፊዎች የጋራ የአቋም መግለጫና በሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኃላፊ መምህር ሰለሞን በቀለ ፤ መመሪያ ማጠቃለያ ተጠናቋል።
ከነሐሴ 25 እስከ 28 ቀን 2018 ዓ.ም. ለሦስት ቀናት በቃሊቲ መካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ሲካሄድ በቆየው በዚህ ሥልጠና ላይ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ ዋና ጸሐፊዎች፣ ሒሳብ ሹሞች፣ ቁጥጥርና ገንዘብ ያዦች፣ ምክትል ሊቃነ መናብርት፣ የሚዲያና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች፣ የሰንበት ትምህርት ቤት አመራሮች፣ የወጣት ማኅበራት ተወካዮች፣ እንዲሁም ብዙ ንስሐ ልጆች ያሏቸው ካህናትና ሰባክያነ ወንጌል በሥልጠናው ተሳትፈዋል።
የሥልጠናው ተሳታፊ የሆኑት ሰባክያነ ወንጌል በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ ባወጡት ባለ 12 ነጥብ የጋራ የአቋም መግለጫ መርሐ ግብሩን ላዘጋጀው ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነትና ለክፍለ ከተማው ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ካህናት ዕዝራ ንዋይ ምስጋናቸውን አቅርበው፣ መሰል አቅምን የሚገነቡ ሥልጠናዎች በቀጣይም ተጠናክረውና በተከታታይነት እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል። አገልጋዮቹ በአብያተ ክርስቲያናትና በገዳማት የተሰጣቸውን
አደራ መሠረት በማድረግ በተሻለ ትጋት፣ ቅንነትና ትሕትና ለማገልገልና በሥልጠናው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር ለመለወጥ ቃል የገቡ ሲሆን፣ ስብከተ ወንጌል የቤተክርስቲያን ቀዳሚና ዋና ዓላማ መሆኑን በመገንዘብ የአጥቢያ ሰበካ ጉባኤዎችና የበላይ
ኃላፊዎች ለወንጌል አገልግሎት ተገቢውን ትኩረትና ክብር እንዲሰጡ እንዲሁም ምቹ ሁኔታዎችን እንዲፈጥሩ አሳስበዋል።
በተጨማሪም በሰዓት አጠቃቀም ዙሪያ የሚታዩ አለመናበቦችን በመቅረፍ በተለይ በሰንበት ቀናትና በበዓላት ለስብከተ ወንጌል በቂ ጊዜ እንዲመደብና ሰባክያነ ወንጌል ያለአግባብ ጣልቃ ገብነት አገልግሎታቸውን በሥርዓት እንዲያከናውኑ አስገዳጅ መመሪያ እንዲሰጥ የጠየቁት ተሳታፊዎቹ፣ በአንዳንድ አጥቢያዎች ለስብከተ ወንጌል የሚመደበው በጀት እጅግ አነስተኛ መሆኑን በመጠቆም በጀቱ
ከአገልግሎቱ ስፋትና አስፈላጊነት ጋር ተመጣጣኝ በሆነ መልኩ ተፈትሾ እንዲስተካከል ጠይቀዋል። በተመሳሳይም የተመደቡ አገልጋዮች የሙያ ብቃት፣ የዕውቀት ዝግጁነትና የአገልግሎት ተነሳሽነት ተፈትሾ አስፈላጊው የማሻሻያና የማብቃት እርምጃዎች እንዲወሰዱ አጽንዖት ሰጥተዋል። በዘመኑ ስብከተ ወንጌልን ለማጠናከር ማኅበራዊ ሚዲያና ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በአግባቡና በጥንቃቄ በመጠቀም ከቅድስት ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ሳይወጡ ምዕመናንን ለማገልገልና የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ለማዳረስ ቃል ገብተዋል።
በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለ በበኩላቸው ባደረጉት ንግግር፣ ራስን ከመንፈሳዊ አገልግሎት ባሻገር ጽሕፈት ቤቶችን በማደራጀት የሕዝበ ክርስቲያኑንና የአገልጋዩን ሁኔታ ለመፈተሽ መሰል ሥልጠናዎችና የልምድ ልውውጦች እጅግ አስፈላጊ መሆናቸውን ገልጸው፣ መርሐ ግብሩን ግንባር ቀደም ሆኖ ላዘጋጀው የአቃቂ ቃልቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ዋና ሥራ አስኪያጁ አያይዘውም፣ የሀገረ ስብከቱ ትምህርትና ሥልጠና ክፍል በአዲስ መልኩ በ2019 ዓ.ም አዳዲስ ፕሮጀክቶችን አቅዶ፣ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የጀመረውን መልካም ተሞክሮ በማሳደግ በመላው ስምንቱ ክፍላተ
ከተማ ሰፊ ሥልጠናዎችን ለማዘጋጀት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን በሰፊው አብራርተዋል።
አስተዳደራዊ ጉዳዮችን በተመለከተም አስተዳዳሪዎች ሠራተኞችን ያላግባብ ከማገድ፣ ከማባረርና ከደረጃ ዝቅ ከማድረግ ተቆጥበው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ዕርቅን፣ ሥልጠናንና መግባባትን እንዲያስቀድሙ አሳስበዋል።
በአስተዳደር ክፍተቶች ምክንያት አገልጋዮችና
ቤተሰቦቻቸው ለችግር እንዳይዳረጉ ክፍተቶችን በጋራና በፍትሐዊነት ማረም እንደሚገባ አስገንዝበው፣ “የእያንዳንዱ ደብር አስተዳዳሪ
የብቃት መለኪያ ሊሆን የሚችለው በደብሩ ያለውን ካህን እዚያው አሰልጥኖ፣ አስተምሮና አቅፎ ማኖር ሲችል ነው፤ ያኔ ነው ሥልጠናው
ውጤታማ ሆነ የሚባለው” በማለት አስተዳደራዊና መንፈሳዊ መመሪያ ሰጥተዋል።
መርሐ ግብሩ «ቅድሚያ ለወንጌል» የሚለው መሪ ቃል በተግባር፣ በእቅድ፣ በበጀትና በጊዜ አጠቃቀም በመተግበር በጋራ ለመሥራት በመስማማት በጸሎት ተጠናቋል።
©የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/

የወሊሶ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ቡኡራ ቦሩ አጸደ ሕፃናት ትምህርት ቤት በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ተመረቀ።

ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም
በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኘው የወሊሶ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን አማካኝነት የተገነባው የቡኡራ ቦሩ አጸደ ሕፃናት ትምህርት ቤት በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ በጸሎተ ተባርኮ በይፋ ተመረቀ።
የቡኡራ ቦሩ አጸደ ሕፃናት ትምህርት ቤት ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም. የተመረቀ ሲሆን፣ በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ፣ የሸገር ከተማ እና የምስካየ ሕዙናን አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ እንዲሁም መልአከ ኃይል አባ አፈወርቅ ዮሐንስ፣ የለገጣፎ ለገዳዲ፣ የኩራ ጂዳ፣ የቡራዩ ገፈርሳ እና የጉጄ መልካ ኖኖ ክፍላተ ከተማዎች ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ በተጨማሪም የወሊሶ ከተማ ከንቲባ አቶ ገመቺስ አረዳ፣ የአካባቢው የጸጥታ አካላት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎችና በርካታ ምዕመናን ተገኝተዋል።
ብፁዕነታቸውንና ተጋባዦችን መርሐ ግብሩ በሚካሔድበት ሥፍራ ሲደርሱ የወሊሶ ከተማ ከንቲባ አቶ ገመቺስ አረዳ፣ የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ገነት ፍቅረ ሥላሴ እንዲሁም የአካባቢው የጸጥታ ኃይሎች በጋራ በመሆን ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ለአገልግሎት ክፍት የሆነው ይህ አዲስ የትምህርት ቤት ሕንፃ ከሀገር ውጭና በወሊሶ ከተማ በሚገኙ ምዕመናን አማካኝነት ግንባታው መካሄዱ ተገልጿል። ሕንፃው ሰባት የመማሪያ ክፍሎች ያሉት ሲሆን፣ ለሕፃናት የትምህርት እና የእውቀት መስፋፊያ እንዲሁም ለቀጣዩ ትውልድ መልካም መሠረት ለመጣል የሚያገለግል መሆኑ ተገልጿል።
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በምረቃው ሥነ ሥርዓት ላይ ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት፣ “ሕፃናት በዚህ ትምህርት ቤት ተምረው ቤተ ክርስቲያናቸውንና አገራቸውን ማገልገል እንዲችሉ የተሠራው ሥራ እጅግ መልካም ነው” ብለዋል።
ብፁዕነታቸው አክለውም፣ ቤተ ክርስቲያን ከጥንት ጀምሮ የትምህርት ሚኒስቴር፣ የሕክምና ተቋም፣ የማኅበረሰብ አስታራቂ ሽማግሌዎችና ካህናት መገኛ መሆኗን አስታውሰው፣ ለነገዋ አገር ተረካቢ የሆነ ትውልድ ማግኘት እንዲቻል እንዲህ ያሉ የትምህርትና የልማት ሥራዎች ሊበረታቱ እንደሚገባ ገልጸዋል።
“ትምህርት ቤት የሁሉም ሰው መገልገያ በመሆኑ ይህ የልማት ሥራ ተጠናክሮ ሊቀጥልና ሊስፋፋ ይገባል፤ የታሪክ አሻራችሁም መልካም ነው” ሲሉ ለተሳተፉትና ለዚህ ሥራ መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ምስጋና አቅርበዋል።
የወሊሶ ከተማ ከንቲባ አቶ ገመቺስ አረዳ በበኩላቸው ባደረጉት ንግግር፣ “ቤተ ክርስቲያን ሁልጊዜም የሰላምና የፍቅር ምንጭ ናት” ካሉ በኋላ፣ በተለይም ማኅበራዊ ኃላፊነቷን በመወጣትና እንዲህ ያሉ የልማት ሥራዎችን በመገንባት ረገድ የምታበረክተው ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸው የከተማ አስተዳደሩም ለትምህርት ቤቱና ለተያያዙ የልማት ሥራዎች ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በመጨረሻም ​በትምህርት ቤቱ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱት አካላት እውቅና የተሰጠ ሲሆን በሥራ አፈጻጸማቸው የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ የሥራ ኃላፊዎችም የማዕረግ ስም ተሰጥቷቸዋል።ሲል የሀገረ ስብከቱ ሚዲያ ክፍል በላከልን ዘገባ ገልጿል።

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 18ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የ2018 ዓ.ም የበጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ።

‎በጉባኤው ላይ ንቡረዕድ ኤሊያስ አብርሃ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመንፈሳዊ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ፤ የጉባኤው ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉኀን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ፤ የጠቅላይ ቤተክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች የቤተክርስቲያን ተወካይ አባቶች ፤ የልዩ ልዩ የሃይማኖት ተቋማት ተወካዮች እና ሥራ አስፈጻሚዎች፤ የክልል እና የአዲስ አበባ ተወካዮች፤ የተቋሙ የቦርድ አባላት እንዲሁም ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።
‎በወይይት መድረኩ ላይ ጉባኤው የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የሰራ አፈጻጸም ግምገማ ያደረገ ሲሆን በመርሐ ግብሩ ላይ የየተቋማቱ የበላይ ጠባቂ አባቶች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የሀገር ሸማግሌዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ያለፉት ዓመታት የጉባኤው የሥራ እንቅስቃሴዎች ተገምግሞ በቀጣይ የጋራ ጉዳዮች እና በሀገራዊ ሰላም ግንባታ ላይ አብሮ ለመሥራት የሚያስችሉ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
‎፦ ጉባኤው የበጀት ዓመቱን የሒሳብ ሪፖርት እና የኦዲት ሪፖርት ግምገማ አድርጓል ፣ በበጀት ዓመቱ የቀረበው የኦዲት ሪፖርት በጉባኤው ሙሉ ድምጽ ጸድቋል ።
‎በ2019 ዓ.ም በጅት ዓመት ዕቅድ በሰላም ግንባታ እና ማኅበራዊ ትሥሥር ማጎልበት፣ ወጣቶች ሴቶች እና ሕጻናት ተሳትፎን ማበልጸግ፣ በማኅበራዊ ዘርፍ፣ የሃይማኖት ተቋማት አቅም እና ዘላቂ ሀብት ማሰባሰብ፣ ተቋማዊ የሰላም ማዕከል ማቋዋቋም ተቀዳሚ ዓላማዉ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ጉባኤው በሀገራዊ እርቅ፣ በበጎ አድራጎት ሥራዎች እና ወጣቶችን በበጎ ምግባር ከማነጽ ረገድ ያለውን ሚና አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል። በመሆኑም በሚቀጥለው በጀት ዓመት ለሥራ አፈጻጸም በጀት ተመድቧል ።
‎በመድረኩ ላይ የሃይማኖት አባቶች ባስተላለፉት መልዕክት ሰላም እና አንድነት በሃይማኖት ተቋማት መካከል ያለውን አብሮነት እና ወንድማማችነት አጠናክሮ ማስቀጠል ለሀገር ሰላም መረጋገጥ ወሳኝ መሆኑ ገለጸው ፤ ጉባዔው የጋራ እሴቶቻችን በህዝቦች መካከል ያለውን የመከባበር፣ የፍቅር እና የደግነት እሴቶች ማጎልበት እንደሚገባም ተመልክቷል።
‎ጉባኤው በ15 ዓመት ውስጥ ቀላል መንገድ አልተጓዘም ያሉት ንቡረ ዕድ ኤሊያስ አብርሃ ጉባኤው እስካሁን ትልልቅ ሥራዎችን ሲሠራ ከታላላቅ አጋር ድርጅቶች ጋር መሆኑን ገለጸው አሁንም ድጋፉ በይበልጥ ተጥናክሮ መቅጥል የገባዋል ብለዋል።
‎ በቀጣይ አብሮነትን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ውሳኔዎች ላይ በመድረሰ ስምምነት ላይ የተደረሰ ሲሆን‎ ለጉባኤው ስኬት የሙያና የፋይናንስ ድጋፍ ላደረጉ ተቋማትና ግለሰቦች ጉባኤው ምስጋና አቅርቧል ።©EOTCTV

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አይሲቲና ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥራ ተጠናክሮ እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ።

ነሐሴ፳፯ ቀን፳፻ ፲ወ፰ ዓ.ም
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጥንታዊት፤ ብሔራዊት፤ ዓለም አቀፋዊት፤ሐዋርያዊት እና ሲኖዶሳዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆንዋ መጠን ዶግማዋን፣ ቀኖናዋን፤ትውፊቷንና ሥርዓቷን በጠበቀ መልኩ መንፈሳዊ እና ማኀበራዊ አገልግሎቷን ለማጠናከር እና ተደራሽ ለማድረግ ከምታከናውናቸው በርካታ ተግባራት መካከል ዘመኑ የደረሰበት የአይሲቲና የዲጂታል ሽግግር ሥራ ዋነኛው መሆኑ ይታወቃል::
ከዚሁ አንጻር የስብከተ ወንጌል አገልግሎትን በመላው ዓለም ለማስፋፋት፣ ታሪካዊ ቅርሶችን እና አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያን ሀብትና ንብረቷን ለመጠበቅ እንዲሁም አስተዳደራዊ ተግባራትን ለማሳለጥ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥራን በበላይነት የሚመራና የሚያስተባብር በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ እንዲሁም የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሽግግር አማካሪ ኮሚቴ ተቃቁሞ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወሳል፡፡
በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና ሸገር አህጉረ ስብከተ ሊቀ ጳጳስ ስምና ፊርማ ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በተላከ ደብዳቤ፤ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ መቋቋሙን ገልጾ ቀደም ሲል እንደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ያሉ አይሲቲን በዋና ክፍል አደራጅተው እየሠሩ የሚገኙ አህጉረ ስብከት በተላከላቸው ዝርዝር የሥራ መመሪያ ቁጥር 3/3018 መሠረት እስከ አጥቢያ ቤተ ከርስቲያን ጽ/ቤት ድረስ ሥራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንዲደረግ በተሰጠው መመሪያ መነሻነት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤትም በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ከመቸውም ጊዜ በተሻለ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥራ ተጠናክሮ እየሠራ ይገኛል ሲሉ ዶ/ር ዘሩ ብርሃኔ(ቀሲስ) የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዋና ክፍል ኃላፊ ገልጸዋል፡፡
ዶ/ር ዘሩ ብርሃኔ(ቀሲስ) እንደገለጹት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሽግግር አማካሪ ኮሚቴ ሰበሳቢ ቀሲስ ዮሐንስ ተስፋዬ እና የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊ መጋቤ ጥበብ ሙሉዓለም አስራት በጋር በመሆን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ያለውን የጂታል ቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ያለበትን ወቅታዊ ሁኔታ በአካል ተገኝተው የተመለከቱ ሲሆን በእርሳቸው አማካይነት ቀደም ሲል ስለተሠሩ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ሥራዎች ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡
በገለጻቸውም አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሥሩ ብዙ ሠራተኞች እና ሀብት የሚያስተዳድር ሀገረ ስብከት እንደመሆኑ ዘመናዊ ዲጂታል ቴክኖሎጂ መጠቀም ዘመኑ የሚጠይቀው ሥራ ሆኖ በመገኘቱ ቀደም ሲል ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ ክፍሉን በማደራጀት የሀገረ ስብከቱ ኦፊሻል ድረ-ገጽ www.eotcaa.org እና ሙሉ የሀገረ ስብከቱ ሕንፃ በኔትዎርክ በማገናኘት ፈጣን የብሮድ ባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት መስጠት የቻለ ሲሆን፣ የባለ ጉዳይ መመዝገቢያና መከታተያ ሲስተም www.aadapp.org በማበልጸግ እንዲሁም ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ የመዝገብ ቤት እና ንብረት አስተዳዳር ሲስተም ተሰርተው የሀገረ ስብከቱ ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዋና ክፍል እያስተዳደራቸው እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
ከዚህ በማስከተልም በማዕከል ደረጃ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት አማካኝነት ስለተዘጋጁትና ተግባራዊ ስለተደረጉት ስትራቴጂ፣ ፖሊሲ እና መመሪያዎች እንዲሁም በለሙት የሰው ሀብት፤ የሰበካ ጉባኤ አስተዳዳር ሲስተም፣ ዌብ ፖርታል እና በመሳሰሉት የቴክኖሎጂ ሥራዎች በተመለከተ ከሀገረ ስብከታችን ዋና ሥራ አስከያጅ ከክቡር መልአከ ብርሃን ሰለሞን በቀለ ጋር በመገናኘት ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡
ቀደም ሲል የለሙት የሀገረ ስብከቱ መዝገብ ቤት እና ንብረት ሀብት አስተዳደር ሲስተሞች በክፍላተ ከተማ እና በገዳማትና አድባራት በማዕከል ደረጃ አገልግሎቱን ማግኘት ካለመቻላቸውም በላይ አሁን ላይ ቴክኖሎጂው ከደረሰበት አንፃር በእጅጉ ወደ ኋላ የቀሩ ሆነው በመገኘታቸው ሲስተሞቹ እንዲዘምኑ፤ እንዲሻሻሉ፣ ወቅታዊ እንዲሆኑ እና ጥቅም ላይ እንዲውሉ በመልአከ ብርሃን ሰሎምን በቀለ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስከያጅ አማካኝነት ሥራው ለሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች የሥራ መመሪያ መስጠታቸው እና የባለ ጉዳይ መመዝገቢያና መመከታቲያ ሲስተም www.aadapp.org በተመለከተም በቂ ሥልጠና ተሰጥቶ ከመስከረም 2019 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ ሥራው እንዲጀምር የሥራ መመሪያ መተላለፉን የሀገረ ስብከቱ የአይሲቲ ዋና ክፍል ኃላፊ ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም የአይሲቲ ዋና ክፍል ኃላፊው በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የለሙ/የበለጸጉ ሲስተሞችን ከሀገረ ስብከቱ ጀምሮ እስከ አጥቢያ ድረስ ሥራ ለማጀመር ሀገረ ስብከቱ ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቅቆ እየጠበቀ መሆኑን ጠቅሰው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ክፍሎችና የገዳማትና አድባራት የሥራ ኃላፊዎች ከወዲሁ በቂ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕውቀት ሽግግር፣ የሰውና የቴክኖሎጂ ግብአት ዝግጅት እንዲያደርጉ እና ማንኛውም ከቴክኖሎጂ መሠረተ ልማቶች ጋር የተያያዙ ጉዳዮች መዋቅሩን ጠብቆ ቅዱስ ሲኖዶስ ባወጣቸው የአይሲቲ ፖሊሲና መመሪያዎች መሠረት ብቻ መከናወን እንዳለባቸው አውቀው ከዚህ ቀደም የለሙ እና ወደፊትም የታቀዱትን ሲስተሞች፣ ድረ ገጾች እና ማኅበራዊ ሚዲያዎችን ዝርዝር ለዋና ክፍሉ በደብዳቤ እንዲያሳውቁ አሳስበዋል።
ድረ-ገጽ፡ www.eotcaa.org
የባለ ጉዳይ መከታቲያ፡ www.aadapp.org

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 15ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል እና 18ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ::

ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም
​የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 15ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል እና 18ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል አካሂዷል።
​በዚህ ታላቅ ጉባኤ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ክብሩ አምባሳደር ታዬ አጽቀ ሥላሴ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ተወካይ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ፤ ብፁዕ አቡነ መልኬጸዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት እና የአቡነ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ፤ ፤ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች የተለያዩ የቤተክርስቲያን ተወካይ አባቶች ፤ የልዩ ልዩ የሃይማኖት ተቋማት ተወካዮች እና ሥራ አስፈጻሚዎች፤ የክልል እና የአዲስ አበባ ተወካዮች፤ የተቋሙ የቦርድ አባላት እንዲሁም የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።
​መርሐ ግብሩ በሃይማኖት አባቶች የመክፈቻ ጸሎት የተጀመረ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት የ15 ዓመታት የጉዞ ታሪክ የሚያሳይ ዘጋቢ ፊልም ቀርቧል።
​በተጨማሪም ጉባኤው ባሳለፋቸው 15 ዓመታት ከጎኑ በመቆም በአህጉራዊ ሰላምና ፀጥታ ዙሪያ፣ በሰብአዊ መብቶች እና በሴቶች ዙሪያ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን አብረው ሲያከናውኑ የቆዩ እንደ UNICEF (ዩኒሴፍ) እና ሰተርሊንግ ፋውንዴሽን ያሉ በርካታ ዓለም አቀፍ አጋር ተቋማትና ተወካዮች፣ ወደፊት በሚያከናወኑት አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ተልዕኮዎች ላይ ገለጻ በማድረግ የ15 ዓመታት ሰላማዊ የአብሮነት ጉዞን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
​የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉኀን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በበኩላቸው፣ ጉባኤው በይፋ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ አባል የሃይማኖት ተቋማት ከመንፈሳዊ አገልግሎታቸው ጎን ለጎን በሀገራዊ የሰላምና የልማት ጉዳዮች ላይ የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ የማቀድ፣ የማስተባበርና የማመቻቸት ሥራዎችን ሲሠራ መቆየቱን ገልጸዋል።
​አክለውም ከመንግሥታዊና መንግሥታዊ ካልሆኑ ሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የሰላምና የመከባበር የጋራ እሴቶች እንዲጠበቁ ሃይማኖታዊ አስተምህሮን መሠረት ያደረጉ የግንዛቤና የአብሮነት ሥራዎች በሀገር አቀፍ፣ በክልልና በከተማ አስተዳደሮች ደረጃ ሲከናወኑ መቆየታቸውንና አሁንም እየተሠሩ መሆኑን አብራርተዋል።
​የሰላም ሚኒስትር ክቡር አቶ መሐመድ ኢድሪስ ባስተላለፉት መልእክት፣ በ15 ዓመታት ውስጥ በየደረጃው የተካሄዱ መድረኮች የልዩ ልዩ ሃይማኖት ተከታይ የሆኑ ኢትዮጵያውያን የእርስ በእርስ አስተምህሮን እንዲረዱ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ገልጸዋል።
​ሚኒስትሩ አክለውም እንዲህ ዓይነቱ ጉባኤ የሃይማኖት ተቋማት የጋራ ፍላጎቶችንን የምናሰፍንበት፣ እምነትን በተግባር የምናጸናበትና የአብሮነትን ታላቅ ቁምነገር የምናሳይበት፣ ባለፉት 15 ዓመታት የሕዝባችንን የሞራልና የስነ-ምግባር እሴቶች ሲቀርጹ የነበሩ የዕድገት ምሳሌዎች መሆናቸውን በመጠቆም፣ በቀጣይም “ለሃይማኖትና ለሀገር የማይሆን ዜጋ እንዳንፈጥር በርትተን ከዘመኑ ጋር በመፍጠን ልንሠራ ይገባል” ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
​በመጨረሻም ለጉባኤው ስኬት የሙያዊና የፋይናንስ ድጋፍ ላደረጉ ተቋማትና ግለሰቦች በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ እና በሌሎች የሃይማኖት መሪዎች አማካይነት የዕውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
©የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/