የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት ላለፉት ሁለት ዓመታት ያሰተማራቸውን ደቀ መዛሙርት አስመረቀ !!!

September 6, 2026
ጷጉሜን 01 ቀን 2018 ዓ/ም
የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት ላለፉት ሁለት ዓመታት ያሰተማራቸውን ደቀ መዛሙርት በዛሬው ዕለት አስመረቀ
በመርሐ ግብሩም ላይ መጋቤ ኅሩያን አባ ኤልያስ በልሁ የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም አስተዳዳሪ ፣ መልዓከ ብርሃናት ዶ/ር አባ ጴጥሮስ ሰለሞን የገዳሙ ስብከተ ወንጌል እና የአስተዳደር ቦርድ ፀሐፊ ፣የገዳሙ አበው መነኮሳት ፣ የተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት ነባር አባላት እና የሥራ አስፈጻሚዎች ፣ ተመራቂ ደቀ መዛሙርት እና የተመራቂ ደቀ መዛሙርት ቤተሰቦች በተገኙበት ተከናውኗል ።
በዕለቱም በመምህር አባ ገብርኤል አያሌው የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ስብከተ ወንጌል አገልጋይ “ተዘከሩ መኳንንቲክሙ ዘነገሩክሙ ቃለ እግዚአብሔር” የእግዚአብሔርን ቃል የነገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ ዕብራውያን 13፣8 ። በሚል ኃይለ ቃል መነሻ በማድረግ የሚያረጋጋና የሚያጸና ትምህርተ ወንጌል ተሰጥቷል ።
ተማራቂ ደቀ መዛሙርት መሠረታዊ የሃይማኖት ትምህርቱ በማዕከላውያን ክፍል ፣ መስማት በተሳናቸው ክፍል ፣ በቅዳሜ እና እሑድ ፣ በእሑድ ብቻ ፣ ሰኞ እና ረቡዕ በማታ መርሐ ግብር ፣ ሰኞ እስከ ሐሙስ በምሳ ሰዓት እንዲሁም በርቀት በአጠቃላይ ከ219 በላይ ትምህርታቸውን ለ12ወራት እንዲሁም ለሁለት ዓመታት የተከታተሉ መሆኑ ተገልጿል ።
ተመራቂዎች በለፉት ዓመታት
፩• ሀልዎተ እግዚአብሔር እና ሥነ ፍጥረት
፪• ኦርቶዶክሳዊ የስብከት ዘዴ
፫• አምሥቱ አእማደ ምሥጢራት
፬ • የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት
፭ • ነገረ መንፈስ ቅዱስ ፣ ነገረ ማርያም ፣ነገረ ቅዱሳን ነገረ ሃይማኖት ፣ነገረ ድኅነት
፮• ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር
፯ • ዕቅበተ ዕምነት
፰ • ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን
፱• የቤተ ክርስቲያን ታሪክ በኢትዮጵያ እና በዓለም መድረክ
፲•ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ትምህርቶችን ተምረው አጠናቀዋል ።
የገዳሙ ተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት እጅግ አንጋፋ እና ስመጥር ከመሆኑም በላይ ብዙ የቤተ ክርስቲያን እና የሀገር ባለውለታውችን ያፈራ፣ ወንጌልን ለሁሉም ይደርስ ዘንድ መስማት ለተሳናቸው ወገኖች በምልክት ቋንቋ የሚያስተምር እንዲሁም በአርድዕት ጉባኤ የነገ የቤተ ክርስቲያን ተረካቢ ሕጻናትን የአብነት ትምህርት በማስተማር ዋነኛ ዓላማ አድርጎ እየሠራ ያለ ባለታሪክ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው።
ባለፉት ዓመታት በሰንበት ትምህርት ቤቱ ያሳለፍናቸው ግዚያት ያካበትነው እውቀት ለነገው ህይወታችን ትልቅ መሠረት ነው ለዚህ ቀን ያበቃን ፈጣሪ ይመስገን ሲሉ ተመራቂ ተማሪዎች ተናግረዋል ።
በመርሐ ግብሩ ላይ በተመራቂ ተማሪዎች የወረብ ዝማሬና ስነፅሁፍ ያቀረቡ ሲሆን ለመምህራን፣ለደረጃ ተማሪዎች የምስክር ወረቀትና ሽልማት ተሰጥቷል።
የገዳማችን አስተዳዳሪ መጋቤ ኅሩያን አባ ኤልያስ በልሁ እንኳን ደስ ያላችሁ በማለት መልዕክት ያስተላለፍ ሲሆን የተመራቂዎች የመመረቅ ዋና ዓላማ የራቁትን ለመሰብሰብና ያልፀኑትን ለማፅናት እንደሆነ በመግለፅ በአገልግሎት እንዲተጉ እና እንዲጠነክሩ አሳስበው በጸሎት የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል ።©ምስካየኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም
Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/pr000091.jpeg 324 448 eotceth https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg eotceth2026-09-06 20:23:162026-09-06 20:23:16የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት ላለፉት ሁለት ዓመታት ያሰተማራቸውን ደቀ መዛሙርት አስመረቀ !!!
Search Search

Recent Posts

  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት መጪውን በዓል ምክንያት በማድረግ ለቤተ ክርስቲያኗ ከፍተኛ መሪዎች «የእንኳን አደረሳችሁ» ስጦታ አበረከተ።
  • የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት ላለፉት ሁለት ዓመታት ያሰተማራቸውን ደቀ መዛሙርት አስመረቀ !!!
  • ጳጉሜ የሚለው ስያሜ ‹‹ኤፓጉሜኔ›› ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ‹‹ጭማሪ›› ማለት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭)
  • የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ሠራተኞች ለተባባሪ ፕሮፌሰር ለብፁዕ አቡነ ፊልጶስ(ዶ/ር) የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በመመረቃቸው ልዩ የደስታና የምስጋና መርሐ ግብር አካሄዱ።
  • “መስከረም በአታ የሃያ ሺህ ሰዎች ምሥረታ” በሚል የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም የአብነት ትምህርት ቤት ሕንጻ ግንባታ ድጋፍ ማስጀመሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ በተገኙበት ተሰጠ።

Archives

  • September 2026
  • August 2026
  • July 2026
  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church
  • Link to Facebook
Link to: ጳጉሜ የሚለው ስያሜ ‹‹ኤፓጉሜኔ›› ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ‹‹ጭማሪ›› ማለት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) Link to: ጳጉሜ የሚለው ስያሜ ‹‹ኤፓጉሜኔ›› ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ‹‹ጭማሪ›› ማለት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭) ጳጉሜ የሚለው ስያሜ ‹‹ኤፓጉሜኔ›› ከሚለው የግሪክ... Link to: የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት መጪውን በዓል ምክንያት በማድረግ ለቤተ ክርስቲያኗ ከፍተኛ መሪዎች «የእንኳን አደረሳችሁ» ስጦታ አበረከተ። Link to: የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት መጪውን በዓል ምክንያት በማድረግ ለቤተ ክርስቲያኗ ከፍተኛ መሪዎች «የእንኳን አደረሳችሁ» ስጦታ አበረከተ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top