የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የወሊሶ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ቡኡራ ቦሩ አጸደ ሕፃናት ትምህርት ቤት በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ተመረቀ።

September 5, 2026
ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም
በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኘው የወሊሶ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን አማካኝነት የተገነባው የቡኡራ ቦሩ አጸደ ሕፃናት ትምህርት ቤት በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ በጸሎተ ተባርኮ በይፋ ተመረቀ።
የቡኡራ ቦሩ አጸደ ሕፃናት ትምህርት ቤት ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም. የተመረቀ ሲሆን፣ በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ፣ የሸገር ከተማ እና የምስካየ ሕዙናን አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ እንዲሁም መልአከ ኃይል አባ አፈወርቅ ዮሐንስ፣ የለገጣፎ ለገዳዲ፣ የኩራ ጂዳ፣ የቡራዩ ገፈርሳ እና የጉጄ መልካ ኖኖ ክፍላተ ከተማዎች ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ በተጨማሪም የወሊሶ ከተማ ከንቲባ አቶ ገመቺስ አረዳ፣ የአካባቢው የጸጥታ አካላት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎችና በርካታ ምዕመናን ተገኝተዋል።
ብፁዕነታቸውንና ተጋባዦችን መርሐ ግብሩ በሚካሔድበት ሥፍራ ሲደርሱ የወሊሶ ከተማ ከንቲባ አቶ ገመቺስ አረዳ፣ የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ገነት ፍቅረ ሥላሴ እንዲሁም የአካባቢው የጸጥታ ኃይሎች በጋራ በመሆን ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ለአገልግሎት ክፍት የሆነው ይህ አዲስ የትምህርት ቤት ሕንፃ ከሀገር ውጭና በወሊሶ ከተማ በሚገኙ ምዕመናን አማካኝነት ግንባታው መካሄዱ ተገልጿል። ሕንፃው ሰባት የመማሪያ ክፍሎች ያሉት ሲሆን፣ ለሕፃናት የትምህርት እና የእውቀት መስፋፊያ እንዲሁም ለቀጣዩ ትውልድ መልካም መሠረት ለመጣል የሚያገለግል መሆኑ ተገልጿል።
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በምረቃው ሥነ ሥርዓት ላይ ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት፣ “ሕፃናት በዚህ ትምህርት ቤት ተምረው ቤተ ክርስቲያናቸውንና አገራቸውን ማገልገል እንዲችሉ የተሠራው ሥራ እጅግ መልካም ነው” ብለዋል።
ብፁዕነታቸው አክለውም፣ ቤተ ክርስቲያን ከጥንት ጀምሮ የትምህርት ሚኒስቴር፣ የሕክምና ተቋም፣ የማኅበረሰብ አስታራቂ ሽማግሌዎችና ካህናት መገኛ መሆኗን አስታውሰው፣ ለነገዋ አገር ተረካቢ የሆነ ትውልድ ማግኘት እንዲቻል እንዲህ ያሉ የትምህርትና የልማት ሥራዎች ሊበረታቱ እንደሚገባ ገልጸዋል።
“ትምህርት ቤት የሁሉም ሰው መገልገያ በመሆኑ ይህ የልማት ሥራ ተጠናክሮ ሊቀጥልና ሊስፋፋ ይገባል፤ የታሪክ አሻራችሁም መልካም ነው” ሲሉ ለተሳተፉትና ለዚህ ሥራ መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ምስጋና አቅርበዋል።
የወሊሶ ከተማ ከንቲባ አቶ ገመቺስ አረዳ በበኩላቸው ባደረጉት ንግግር፣ “ቤተ ክርስቲያን ሁልጊዜም የሰላምና የፍቅር ምንጭ ናት” ካሉ በኋላ፣ በተለይም ማኅበራዊ ኃላፊነቷን በመወጣትና እንዲህ ያሉ የልማት ሥራዎችን በመገንባት ረገድ የምታበረክተው ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸው የከተማ አስተዳደሩም ለትምህርት ቤቱና ለተያያዙ የልማት ሥራዎች ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በመጨረሻም ​በትምህርት ቤቱ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱት አካላት እውቅና የተሰጠ ሲሆን በሥራ አፈጻጸማቸው የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ የሥራ ኃላፊዎችም የማዕረግ ስም ተሰጥቷቸዋል።ሲል የሀገረ ስብከቱ ሚዲያ ክፍል በላከልን ዘገባ ገልጿል።
Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/pr000086.jpeg 298 448 eotceth https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg eotceth2026-09-05 18:12:572026-09-05 18:12:57የወሊሶ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ቡኡራ ቦሩ አጸደ ሕፃናት ትምህርት ቤት በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ተመረቀ።
Search Search

Recent Posts

  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት መጪውን በዓል ምክንያት በማድረግ ለቤተ ክርስቲያኗ ከፍተኛ መሪዎች «የእንኳን አደረሳችሁ» ስጦታ አበረከተ።
  • የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት ላለፉት ሁለት ዓመታት ያሰተማራቸውን ደቀ መዛሙርት አስመረቀ !!!
  • ጳጉሜ የሚለው ስያሜ ‹‹ኤፓጉሜኔ›› ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ‹‹ጭማሪ›› ማለት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭)
  • የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ሠራተኞች ለተባባሪ ፕሮፌሰር ለብፁዕ አቡነ ፊልጶስ(ዶ/ር) የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በመመረቃቸው ልዩ የደስታና የምስጋና መርሐ ግብር አካሄዱ።
  • “መስከረም በአታ የሃያ ሺህ ሰዎች ምሥረታ” በሚል የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም የአብነት ትምህርት ቤት ሕንጻ ግንባታ ድጋፍ ማስጀመሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ በተገኙበት ተሰጠ።

Archives

  • September 2026
  • August 2026
  • July 2026
  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church
  • Link to Facebook
Link to: የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 18ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የ2018 ዓ.ም የበጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ። Link to: የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 18ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የ2018 ዓ.ም የበጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ። የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 18ኛ መደበኛ... Link to: በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት አዘጋጅነት ሲካሄድ የነበረው «ቅድሚያ ለወንጌል» ሥልጠና የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ። Link to: በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት አዘጋጅነት ሲካሄድ የነበረው «ቅድሚያ ለወንጌል» ሥልጠና የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ። በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት አዘጋጅነት...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top