የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አይሲቲና ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥራ ተጠናክሮ እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ።

September 2, 2026
ነሐሴ፳፯ ቀን፳፻ ፲ወ፰ ዓ.ም
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጥንታዊት፤ ብሔራዊት፤ ዓለም አቀፋዊት፤ሐዋርያዊት እና ሲኖዶሳዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆንዋ መጠን ዶግማዋን፣ ቀኖናዋን፤ትውፊቷንና ሥርዓቷን በጠበቀ መልኩ መንፈሳዊ እና ማኀበራዊ አገልግሎቷን ለማጠናከር እና ተደራሽ ለማድረግ ከምታከናውናቸው በርካታ ተግባራት መካከል ዘመኑ የደረሰበት የአይሲቲና የዲጂታል ሽግግር ሥራ ዋነኛው መሆኑ ይታወቃል::
ከዚሁ አንጻር የስብከተ ወንጌል አገልግሎትን በመላው ዓለም ለማስፋፋት፣ ታሪካዊ ቅርሶችን እና አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያን ሀብትና ንብረቷን ለመጠበቅ እንዲሁም አስተዳደራዊ ተግባራትን ለማሳለጥ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥራን በበላይነት የሚመራና የሚያስተባብር በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ እንዲሁም የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሽግግር አማካሪ ኮሚቴ ተቃቁሞ ወደ ሥራ መግባቱ ይታወሳል፡፡
በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና ሸገር አህጉረ ስብከተ ሊቀ ጳጳስ ስምና ፊርማ ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በተላከ ደብዳቤ፤ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ መቋቋሙን ገልጾ ቀደም ሲል እንደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ያሉ አይሲቲን በዋና ክፍል አደራጅተው እየሠሩ የሚገኙ አህጉረ ስብከት በተላከላቸው ዝርዝር የሥራ መመሪያ ቁጥር 3/3018 መሠረት እስከ አጥቢያ ቤተ ከርስቲያን ጽ/ቤት ድረስ ሥራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንዲደረግ በተሰጠው መመሪያ መነሻነት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤትም በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ከመቸውም ጊዜ በተሻለ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥራ ተጠናክሮ እየሠራ ይገኛል ሲሉ ዶ/ር ዘሩ ብርሃኔ(ቀሲስ) የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዋና ክፍል ኃላፊ ገልጸዋል፡፡
ዶ/ር ዘሩ ብርሃኔ(ቀሲስ) እንደገለጹት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሽግግር አማካሪ ኮሚቴ ሰበሳቢ ቀሲስ ዮሐንስ ተስፋዬ እና የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊ መጋቤ ጥበብ ሙሉዓለም አስራት በጋር በመሆን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ያለውን የጂታል ቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ያለበትን ወቅታዊ ሁኔታ በአካል ተገኝተው የተመለከቱ ሲሆን በእርሳቸው አማካይነት ቀደም ሲል ስለተሠሩ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ሥራዎች ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡
በገለጻቸውም አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሥሩ ብዙ ሠራተኞች እና ሀብት የሚያስተዳድር ሀገረ ስብከት እንደመሆኑ ዘመናዊ ዲጂታል ቴክኖሎጂ መጠቀም ዘመኑ የሚጠይቀው ሥራ ሆኖ በመገኘቱ ቀደም ሲል ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ ክፍሉን በማደራጀት የሀገረ ስብከቱ ኦፊሻል ድረ-ገጽ www.eotcaa.org እና ሙሉ የሀገረ ስብከቱ ሕንፃ በኔትዎርክ በማገናኘት ፈጣን የብሮድ ባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት መስጠት የቻለ ሲሆን፣ የባለ ጉዳይ መመዝገቢያና መከታተያ ሲስተም www.aadapp.org በማበልጸግ እንዲሁም ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ የመዝገብ ቤት እና ንብረት አስተዳዳር ሲስተም ተሰርተው የሀገረ ስብከቱ ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዋና ክፍል እያስተዳደራቸው እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
ከዚህ በማስከተልም በማዕከል ደረጃ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት አማካኝነት ስለተዘጋጁትና ተግባራዊ ስለተደረጉት ስትራቴጂ፣ ፖሊሲ እና መመሪያዎች እንዲሁም በለሙት የሰው ሀብት፤ የሰበካ ጉባኤ አስተዳዳር ሲስተም፣ ዌብ ፖርታል እና በመሳሰሉት የቴክኖሎጂ ሥራዎች በተመለከተ ከሀገረ ስብከታችን ዋና ሥራ አስከያጅ ከክቡር መልአከ ብርሃን ሰለሞን በቀለ ጋር በመገናኘት ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡
ቀደም ሲል የለሙት የሀገረ ስብከቱ መዝገብ ቤት እና ንብረት ሀብት አስተዳደር ሲስተሞች በክፍላተ ከተማ እና በገዳማትና አድባራት በማዕከል ደረጃ አገልግሎቱን ማግኘት ካለመቻላቸውም በላይ አሁን ላይ ቴክኖሎጂው ከደረሰበት አንፃር በእጅጉ ወደ ኋላ የቀሩ ሆነው በመገኘታቸው ሲስተሞቹ እንዲዘምኑ፤ እንዲሻሻሉ፣ ወቅታዊ እንዲሆኑ እና ጥቅም ላይ እንዲውሉ በመልአከ ብርሃን ሰሎምን በቀለ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስከያጅ አማካኝነት ሥራው ለሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች የሥራ መመሪያ መስጠታቸው እና የባለ ጉዳይ መመዝገቢያና መመከታቲያ ሲስተም www.aadapp.org በተመለከተም በቂ ሥልጠና ተሰጥቶ ከመስከረም 2019 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ ሥራው እንዲጀምር የሥራ መመሪያ መተላለፉን የሀገረ ስብከቱ የአይሲቲ ዋና ክፍል ኃላፊ ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም የአይሲቲ ዋና ክፍል ኃላፊው በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የለሙ/የበለጸጉ ሲስተሞችን ከሀገረ ስብከቱ ጀምሮ እስከ አጥቢያ ድረስ ሥራ ለማጀመር ሀገረ ስብከቱ ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቅቆ እየጠበቀ መሆኑን ጠቅሰው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ክፍሎችና የገዳማትና አድባራት የሥራ ኃላፊዎች ከወዲሁ በቂ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕውቀት ሽግግር፣ የሰውና የቴክኖሎጂ ግብአት ዝግጅት እንዲያደርጉ እና ማንኛውም ከቴክኖሎጂ መሠረተ ልማቶች ጋር የተያያዙ ጉዳዮች መዋቅሩን ጠብቆ ቅዱስ ሲኖዶስ ባወጣቸው የአይሲቲ ፖሊሲና መመሪያዎች መሠረት ብቻ መከናወን እንዳለባቸው አውቀው ከዚህ ቀደም የለሙ እና ወደፊትም የታቀዱትን ሲስተሞች፣ ድረ ገጾች እና ማኅበራዊ ሚዲያዎችን ዝርዝር ለዋና ክፍሉ በደብዳቤ እንዲያሳውቁ አሳስበዋል።
ድረ-ገጽ፡ www.eotcaa.org
የባለ ጉዳይ መከታቲያ፡ www.aadapp.org
Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/pr000085.jpg 365 336 eotceth https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg eotceth2026-09-02 17:54:142026-09-02 19:48:03በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አይሲቲና ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥራ ተጠናክሮ እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ።
Search Search

Recent Posts

  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት መጪውን በዓል ምክንያት በማድረግ ለቤተ ክርስቲያኗ ከፍተኛ መሪዎች «የእንኳን አደረሳችሁ» ስጦታ አበረከተ።
  • የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት ላለፉት ሁለት ዓመታት ያሰተማራቸውን ደቀ መዛሙርት አስመረቀ !!!
  • ጳጉሜ የሚለው ስያሜ ‹‹ኤፓጉሜኔ›› ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ‹‹ጭማሪ›› ማለት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭)
  • የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ሠራተኞች ለተባባሪ ፕሮፌሰር ለብፁዕ አቡነ ፊልጶስ(ዶ/ር) የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በመመረቃቸው ልዩ የደስታና የምስጋና መርሐ ግብር አካሄዱ።
  • “መስከረም በአታ የሃያ ሺህ ሰዎች ምሥረታ” በሚል የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም የአብነት ትምህርት ቤት ሕንጻ ግንባታ ድጋፍ ማስጀመሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ በተገኙበት ተሰጠ።

Archives

  • September 2026
  • August 2026
  • July 2026
  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church
  • Link to Facebook
Link to: የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 15ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል እና 18ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ:: Link to: የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 15ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል እና 18ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሄደ:: የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 15ኛ ዓመት... Link to: የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 18ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የ2018 ዓ.ም የበጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ። Link to: የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 18ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የ2018 ዓ.ም የበጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ። የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ 18ኛ መደበኛ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top