የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ባዘጋጀው የሥልጠናና የምክክር መርሐ ግብር ላይ ያስተላለፉት መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል፦

July 17, 2026
ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱሶ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
ሊቀ ሥዩማን እስክንድር ገብረክርስቶስ የቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅትና የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ፤
ክቡራን የጠቅላይ ቤተክሆነት ኃላፊዎች፤
የዚህ ታሪካዊ ሥልጠና ተሳታፊዎች፤
ክቡራንና ክቡራት፤
መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ። ማቴ 5:16
ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ለዘመናት የዕውቀት ምንጭ፣ የፍቅር ማኅደር፣ የሰላም ማዕከልና የታሪክ መዛግብት ሆና ኖራለች። ይሁን እንጂ ይህንን ታላቅና መልካም ሥራዋን፣ እንዲሁም በጨለማው ዓለም ውስጥ የምታበራውን መለኮታዊ ብርሃን ለዓለም ተደራሽ በሆነ መንገድ ማሳወቅና ማስመስከር የአሁኑ ዘመን ትውልድና በተለይም የእናንተ የሕዝብ ግንኙነት መሪዎች ዋነኛ የሐዋርያነት ኃላፊነት ነው።
​የምንኖርበት ዘመን የመረጃ ፍሰቱ እጅግ የፈጠነ፣ ነገር ግን እውነትና ሐሰት ተደባልቀው የሚቀርቡበት ውስብስብ ዘመን ነው። ዛሬ ላይ መረጃ እንደ ዋነኛ መሣሪያ እየተቆጠረ ባለበት ሰዓት፣ ቤተ ክርስቲያናችንም ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚሰነዘሩባትን የተዛቡ ትረካዎችና ስም ማጥፋቶች የምትጋፈጠው በዋናነት በዚህ በሕዝብ ግንኙነት መድረክ ላይ ነው። ለዘመናት ቤተ ክርስቲያን የሠራችው ታላቅ የልማት፣ የዕርቅ፣ የጥበብና የሀገርን አንድነት የማጽናት ሥራ በሚገባ ባለመነገሩና ባለመሰነዱ ምክንያት፣ ዓለም የእርሷን ባለውለታነት ዘንግቶ ፈተና ሊያደርስባት ሲሞክር ይስተዋላል። ይህ ክፍተት የተፈጠረው እኛ ብርሃናችንን በሰው ፊት በሚገባና በሚመጥን ቋንቋ ማብራት ባለመቻላችን ነው።
እስካሁን የነበረን የሕዝብ ግንኙነት አካሄድ በአብዛኛው ጥቃት ሲሰነዘርብን ምላሽ የመስጠት ወይም የመከላከል ባሕርይ የነበረው ነው። አሁን ግን ይህ አሠራር ሊቀየር ይገባል። እኛ አስቀድመን የቤተ ክርስቲያናችንን እውነት፣ መልካም ሥራና ሰላማዊ ማንነት ለሕዝብ በግልጽና በቅድሚያ ማሳየት አለብን።
የእኛ የሕዝብ ግንኙነት ሥራ ዓለማውያን እንደሚያደርጉት ውሸትን እውነት የማስመስከር ጥበብ አይደለም። የእኛ መሠረት እውነት እራሱ ክርስቶስ ነው። ስለዚህ እውነትን በሙያዊ ብቃት፣ በወቅታዊ ቴክኖሎጂና በሰከነ መንፈሳዊ ጥበብ ማቅረብ ይኖርብናል።
​ከስልጠናው የሚጠበቁ አበይት አቅጣጫዎች
​ይህ ከየአህጉረ ስብከቱ የተሰበሰባችሁበት ታላቅ መድረክ፣ ዕውቀትና ክህሎታችሁን ለማሳደግ ብቻ ሳይሆን በአንድነት ለመቆም የሚያስችል የአውታረ መረብ መሠረት ለመጣል የተዘጋጀ ነው። ከዚህ ስልጠና በኋላ ወደየአህጉረ ስብከታችሁ ስትመለሱ የሚከተሉትን አቅጣጫዎች በተግባር እንድትርጎሙ
ለማሳሰብ እንወዳለን።
​፩. የቅንጅትና የአንድነት አሠራርን መዘርጋት
​የጠቅላይ ቤተ ክህነት የሕዝብ ግንኙነት መዋቅርና የአህጉረ ስብከቱ መዋቅሮች ልክ እንደ አንድ አካል ተሳስረው መሥራት ይኖርባቸዋል። በአንድ አህጉረ ስብከት ላይ የሚፈጠር ፈተና ወይም የሚመዘገብ ስኬት የሁላችንም ነው። መረጃዎችን በፍጥነት በመለዋወጥና በአንድ ድምፅ በመናገር የቤተ ክርስቲያናችንን ጥንካሬና አንድነት ለዓለም ማሳየት ይኖርባችኋል።
​፪. ዘመናዊ የዲጂታል ሚዲያዎችን በአግባቡ መጠቀም
​የማኅበራዊ ሚዲያ መድረኮች የትውልዱ መገናኛና የሐሳብ መገበያያ ሆነዋል። እነዚህን መድረኮች በመልካም ሥነ ምግባር፣ በሳልና በጎ በሆነ ቋንቋ፣ እንዲሁም ማራኪ በሆኑ ዝግጅቶች በመጠቀም የቤተ ክርስቲያናችንን አስተምህሮና መልካም ሥራ ለዓለም ማሳወቅ አለባችሁ። ብዕራችሁ የሚገነባ እንጂ የሚያፈርስ መሆን የለበትም።
​፫. ለዕርቅና ለሰላም ቅድሚያ መስጠት
​የቤተ ክርስቲያን ድምፅ ምንጊዜም የሰላምና የዕርቅ ድምፅ ነው። በማኅበረሰቡ ውስጥ አለመግባባቶችና ግጭቶች ሲፈጠሩ የእናንተ መግለጫዎችና ዘገባዎች ቁስልን የሚፈውሱ፣ ወንድማማችነትን የሚያጸኑና ሰላምን የሚሰብኩ ሊሆኑ ይገባል።
​በመጨረሻም ይህ ስልጠና በቤተ ክርስቲያናችን የሕዝብ ግንኙነት ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት፣ ራሳችንን እንድንፈትሽና በአዲስ መንፈሳዊ ጉልበት እንድንነሳ የሚያደርግ እንደሚሆን ያለንን ሙሉ እምነት እየገለጽን በዚህ ስልጠና ወቅት የምታገኙትን ዕውቀት ወደ ተግባር በመለወጥ፣ የቤተ ክርስቲያናችንን ክብር ለመጠበቅና የወንጌልን ብርሃን ለማዳረስ በትጋት እንድትሠሩ አባታዊ አደራችንን እናስተላልፋለን። በየአህጉረ ስብከቱ የሚመሩ ብፁዓን አባቶች ሊቃነ ጳጳሳትም ለዚህ ሥራችሁ አስፈላጊውን ድጋፍና እገዛ እንዲያደርጉላችሁ ቀደም ሲል በቅዱስ ሲኖዶስ መመሪያ የተሰጠ ሲሆን፣ እኛም በጠቅላይ ቤተ ክህነት በኩል አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ እንደማናቋርጥ ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን።ይህንን ስልጠና በከፍተኛ ትጋት ላዘጋጁት የጠቅላይ ቤተ ክህነት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ እንዲሁም እውቀታቸውንና ተሞክሯቸውን ለማካፈል እዚህ ለተገኙት አሰልጣኞች በሙሉ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም ላቅ ያለ ምስጋናችንን እናቀርብላችኋለን።
ሐምሌ፱ቀን፳፻ ፲ወ፰ ዓ.ም
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ
አባ ሳዊሮስ
የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ
ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/pr000035.jpeg 434 336 eotceth https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg eotceth2026-07-17 03:47:432026-07-17 03:47:43ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ባዘጋጀው የሥልጠናና የምክክር መርሐ ግብር ላይ ያስተላለፉት መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል፦
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ወቅታዊ ጉዳዮች በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።
  • ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት የተሰሩ የልማት ሥራዎችን ተመለከቱ፤ በድሬዳዋ መልካ ጀብዱ መካነ ቅዱሳን አቡነ አረጋዊ ወአርሴማ ገዳም የሚገኙ እጓለማውታ ሕጻናትን ጎበኙ።
  • የድሬዳዋ ሳባ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ያስገኘባው ባለ ሦስት ወለል ሁለገብ ሕንጻ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና በብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጸሎተ ቡራኬ በዛሬው ዕለት ተመረቋል።
  • የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ሕንጻ ቤተክርስቲያን ዕድሳት ተጠናቆ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው ተባረከ።
  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ ወደ ቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ተጓዘ።

Archives

  • July 2026
  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: በአህጉረ ስብከትና በማዕከል መካከል የተናበበ የሕዝብ ግንኙነት መዋቅር ለመፍጠር የሚያስችል ስልጠና መሰጠት ጀመረ” Link to: በአህጉረ ስብከትና በማዕከል መካከል የተናበበ የሕዝብ ግንኙነት መዋቅር ለመፍጠር የሚያስችል ስልጠና መሰጠት ጀመረ” በአህጉረ ስብከትና በማዕከል መካከል የተናበበ... Link to: “እረኛ ከሌለ በጎቹ ለአራዊት ይዳረጋሉ፤ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች እውነትን ይዛችሁ ቤተ ክርስቲያንን ጠብቁ” ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ Link to: “እረኛ ከሌለ በጎቹ ለአራዊት ይዳረጋሉ፤ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች እውነትን ይዛችሁ ቤተ ክርስቲያንን ጠብቁ” ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ “እረኛ ከሌለ በጎቹ ለአራዊት ይዳረጋሉ፤ የሕዝብ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top