ቅዱስ ፓትርያርኩ አልሾምም ወደ ትግራይም ፤ አልሔድም አላሉም

ሰኔ ፳፱ ቀን ፳፻ ፲ ወ፭ ዓ.ም
“”””””””””””””””””””””””””
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ
******

በአንዳንድ ማኅበራዊ ሜዲያዎች ቅዱስ ፓትርያርኩ በቅዱስ ሲኖዶስ “የተመረጡትን መነኮሳት አልሾምም፤ ወደ ትግራይም አልሔድም”ብለዋል ተብሎ የተሰርጭው ዜና ፍጹም ሐሰት ነው። የተመረጡትን አባቶችንም አልሾምም አላሉም። በተያዘው መርሐ ግብር መሠረትም ወደ ትግራይ ይጓዛሉ።

እንዲህ ዓይነቱ ሆን ተብሎ የሚሰራጭ የሐሰት ዘገባ ፤ የእርቅ ሂደቱን የማደናቀፍ እና የቅዱስ ፓትርያርኩን ስም በሐስት የማጠልሽት የተለመደና ቀጣይ የሐሰተኞችና ስም አጥፊዎች ዘመቻ አካል መሆኑን እየገለጽን ይህን አይነቱን የሐሰትና የፈጠራ ወሬ በቅድስት እርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን ላይ የሚነዙ አካላትም ከዚህ ደርጊታቸው እንዲታቀቡ ቅድስት ቤተክርስቲያን በጥብቅ ታሳስባለች።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ