በዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የደረሰውን ዝርፊያ በተመለከተ አሰፈላጊው ክትትል እየተደረገ ነው።

መስከረም ፮ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም
*****
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ
“”””””””””””””””””””
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የሚገኘው የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም በትላንትናው እለት ማንነታቸው ባልታወቁ ዘራፊዎች የደረሰበትን ዝርፊያ በተመለከተ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስፈላጊውን ክትትልና ማጣራት በማድረግ ላይ የምትገኝ ሲሆን በጉዳዩ ዙሪያም ከሚመለከታቸው የመንግሥት የጸጥታ አካላት ጋር እየተነጋገረችበት ነው።

በገዳሙ በተካሔደው ዝርፊያም ከገዳሙ ጥንታዊያን ቅርሶች ጋር በተያያዘ የደረሰ ምንም ዓይነት ጉዳት የሌለ መሆኑን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤቱ ባደረገው ማጣራት አረጋግጧል።

በገዳሙ ከዝርፊያው ጋር በተያያዘ የደረሰውን ጉዳት በተመለከተ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤቱ ከገዳሙ፣ከሀገረ ስብከቱና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ተገቢውን ማጣራት እያደረገ ሲሆን ዝርዝር ሁኔታውን በተመለከተ በቅርቡ በመገናኛ ብዙሃን የምናሳውቅ መሆኑን እየገለጽን ሕዝበ ክርስቲያኑ ከቤተክርስቲያናችን ማዕከላዊ አስተዳደር የሚሰጠውን ማብራሪያ በትዕግስት እንዲጠባበቅ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ስም መልእክታችንን እናስተላልፋለን።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት