“አባ ” ንዋየ ሥላሴ የተባሉት በፈቃዳቸው ይቅርታ ጠየቁ እንጂ “ያፈነም” “ያስገደደም” አካል የለም ይህ የሐሰት ወሬ ነው ከዚህ ይልቅ በሕገወጥ መንገድ ያላችሁ አካላት በይቅርታ ወደ ቤታችሁ መመለሱ ይበጃል”

“አባ ” ንዋየ ሥላሴ የተባሉት በፈቃዳቸው ይቅርታ ጠየቁ እንጂ “ያፈነም” “ያስገደደም” አካል የለም ይህ የሐሰት ወሬ ነው ከዚህ ይልቅ በሕገወጥ መንገድ ያላችሁ አካላት በይቅርታ ወደ ቤታችሁ መመለሱ ይበጃል”
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አቀራራቢ ዐቢይ ኮሚቴ

በሕገ ወጥ “ሢመተ ኢጲስ ቆጶስ” ከተሳተፉ አካላት በይቅርታ የሚመለሱ አካላትን የሚያቀራርብ ዐቢይ ኮሚቴ በዛሬ ዕለት በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች መግለጫ ሰጥቷል።

በተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ሲያደርግ መቆየቱን የገለጸው ኮሚቴው እዚህ ደረጃ ለመድረሱ አስተዋጽኦ ላደረጉ የበጎ ሐሳብ ባለቤቶች ምስጋናውን አቅርቧል።

የአቀራራቢ ኮሚቴው በይቅርታ እንዲመለሱ ካደረጋቸው መካከል አባ ፀጋ ዘአብ አዱኛ ተጠቀሽ ሲሆኑ በሌላ በኩል በፈቃዳቸው ይቅርታ የተጠየቁትና በኋላ ግን “ተገድጄ ነው” ያሉት “አባ” ንዋየ ሥላሴ የተባሉ ግለሰብ የተናገሩት ያልተደረገና የሐሰት ሥራ መሆኑ ኮሚቴው ገልጿል።

ከዚህ በማያያዝ በሕገወጥ መንገድ እየተጓዙ ላሉ አካላትም አሁንም የአቀራራቢ ኮሚቴው የሚጠበቅበትን ሁሉ ለማድረግ እንደሚችል ጠቅሶ በይቅርታ ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንዲመለሱም ጥሪ አስተላልፏል።

በኢ/ኦ/ተ/ ቤተክርስቲያን በወቅታዊ ችግር ምክንያት የተደራጀው የሽምግልና ኮሚቴ እስከ አሁን የሰራቸውን ስራዎች ለዐቢይ ኮሚቴው ሪፖርት አደረጉ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ በተከሰተው የቀኖና፣የሃይማኖትና የአስተዳደር ጥሰትን ተከትሎ የተፈጠረውን ወቅታዊ ችግር ምክንያት ጉዳዩን በሽምግልና ለመፍታት የተደራጁት የሽምግልና ኮሚቴዎች (የሀገር ሽማግሌዎች) ችግሩ ከተፈጠረ ወዲህ በኮሚቴው የተሠሩ ሥራዎችን እና ወደፊት ሊሠሩ ስለሚገባቸው ጉዳዩች ለዐቢይ ኮሚቴ፣ለብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ለመንበረ ፓትርያርክ እና ለቅዱስ ሲኖዶስጽሕፈት ቤትዛሬ የካቲት ፲፰ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ዓ.ም ሪፖርቱን አቅርቧል።

ቤተክርስቲያን ያወጀችውን አዋጅ ተከትሎ ሃይማኖታዊ ተልእኳቸውን በመፈጸማቸው ከሥራ የተባረሩ፣የታሰሩና የተንገላቱ ኦርቶዶክሳዊያን ሪፖርት እንዲያደርጉ የተላለፈ ጥሪ፤

ቤተክርስቲያን ያወጀችውን አዋጅ ተከትሎ ሃይማኖታዊ
ተልእኳቸውን በመፈጸማቸው ከሥራ የተባረሩ፣የታሰሩና የተንገላቱ ኦርቶዶክሳዊያን ሪፖርት እንዲያደርጉ የተላለፈ ጥሪ፤
*********
የካቲት ፲፰ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም
“””””””””””””””””””””””””””
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
******

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅደስ አሐደ አምላክ
አሜን

በኢትዮጵያ ኦርቶድክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በተፈጸመው ሃይማኖታዊ፤ ቀኖናዊ እና አስተዳደራዊ ሕገ ወጥ የኤጴስ ቆጰሳት ሢመት ጋር በተያያዘ በተፈጠሩት ችግሮች እንዱሁም ችግሮቹን መነሻ በማድረግ ቅዱስ ሲኖድስ ጾመ ነነዌን ምክንያት በማድረግ በጾም እና በምህላ አዋጁ መነሻነት ምእመናን ሰማእትነትን ከፍለዋል፤ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ ያለአግባብም ታስረዋል፤ በሕገወጥ መንገድ ተንከራተዋል፤ ተገቢ ያልሆነ ዋጋ ከፍለዋል፤ እንዲሁም ከደመወዝ እና ከሥራ ገበታቸው ጭምር ታግደዋል፤ ተሰናብተዋልም፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ ቅደስ ሲኖዶስ በቤተ ክርስቲያናችን እና በምእመናን ላይ እየደረሱ ያሉ ጥቃቶች እና ጉዳቶች እንዱሁም ሕገ ወጥ ተግባራትን በመከታተል ተገቢውን ሕጋዊ ምላሽ መስጠት የሚችል የሕግ ባለሙያዎች አማካሪ እና ድጋፍ ሰጭ ኮሚቴ በማዋቀር ወደ ሥራ እንዲገባ ተደርጎ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን እያከናወነ ይገኛል፡፡

ስሆነም የደረሱትን እና እየደረሱ ያለትን ጉዳቶች በተመለከተ ተጨባጭ መረጃ እና ማስረጃ ማሰባሰቡ ለነገ የማይባል ተግባር በመሆኑ እና አሁንም የሕግ ክፍሉ በተለያየ መንገድ በሚደርሰው መረጃ ላይ ብቻ ተመስርቶ በውስንነት ድጋፍ እየሰጠ የሚገኝ ስለሆነ መረጃ እና ማስረጃ ያላቸው ማናቸውም ምእመናን እና ምእመናት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እጆቻችሁ ላይ ያሉ የሰነድ፤የድምጽ፤ እና የምስል ማስረጃዎቻችሁን በሙሉ ከዚህ በታች በተቀመጡት አማራጭ የመረጃ መንገዶች ታሳውቁ ዘንድ የሕግ ክፍሉ ያሳስባል፡፡
በመሆኑም ፦

፩. በማናቸውም የፌዳራል፤ የክልል እና የከተማ መስተዳደር ውስጥ ተቀጥራችሁ ስትሠሩ የነበራችሁ እና ከሃይማኖት ጋር በተያያዘ ከሥራ እና ከደመወዝ የታገዳችሁ እንዱሁም የተሰናበታችሁ በሙሉ ዝርዝር መረጃውን በመላክ እንድታሳውቁን፤

፪. በማናቸውም የፌዳራል፤ የክልል እና የከተማ መስተዳደር ከወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ በእስር ላይ የሚገኙ ካህናት፤ አገልጋዮች እና ምእመናን ሙለ መረጃ በመላክ እንድታሳውቁን፤

፫. በማናቸውም የፌዳራል፤ የክልል እና የከተማ መስተዳደር ከወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ የሞት እና የአካል ጉዳት የደረሰባቸውን ካህናት፤ አገልጋዮች እና ምእመናን ሙሉ መረጃ በመላክ እንድታሳውቁን፤ እያሳሰብን ያላችሁን ማናቸውም መረጃ እና ማስረጃዎች ይህ ማስታወቂያ ከተነገረበት ከዛሬ የካቲት ፲፰ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ጀምሮ በስልክ ቁጥር +251985585858 በዋትስአፕ፤ በቴሌግራም ወይም በኢሜይል አዴራሻችን፡-eotcer@gmail.com የሞቱትን፤ የተጎደትን፤ የታሠሩትን እና የተሰወሩትን ሰዎች ስም እና የድርጊቱን ውጤት የሚያሳይ ዝርዝር መረጃ ታጋሩን ዘንድ በቤተ ክርስቲያን ስም ጥሪያችንን እናስተላፋለን፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶድክስ ተዋሕዶ
ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ

መረጃ!

የካቲት 03 ቀን 2015 ዓ.ም ፍርድ ቤቱ በሕገ ወጥ መንገድ በተፈጸመው ሹመት ላይ የተሳተፉት ግለሰቦች ላይ ካስተላለፈው ዕግድ መካከል የተፈጸመውን ዕርቅ ተከትሎ የአባ ሳዊሮስ፣ የአባ ኤዎስጣቴዎስና የአባ ዜና ማርቆስ ዕግድ ተነስቷል።

ቀሪዎቹ 26 ግለሰቦች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅጽር ግቢ ውስጥ እንዳይገቡ የተጣለው ዕግድ እንዲቀጥል ፍርድ ቤቱ ወስኗል።

 

ብፁአን አባቶች በአዋሽ ሰባት የታሰሩ ወጣቶችን ሊጎበኙ ነው

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ወቅታዊ ችግር ምክንያት አዋሽ ሰባት በእስር ላይ የሚገኙ ወጣቶችን ሁኔታ ለመመልከት ብፁአን አባቶች የሚመሩት ልዑክ በማረሚያ ቤቱ ጉብኝት እንደሚያደርግ ቤተክርስትያኗ ያቋቋመችው ጊዜያዊ የሕግ ኮሚቴ ለአዲስ ማለዳ አስታውቋል።

ለኦርቶዶክሳውያን እና ለቤተክርስቲያን ክብር በመሟገታቸው ለእስር ተዳርገው የነበሩት ፓስተር ብንያም ሽታዬ ከእስር ተለቀቁ።

ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በተደጋጋሚ ጥብቅና በመቆም ሉዓለዊነቷንና መብቷን ማስጠበቅ እንደሚገባ በመሟገታቸው ሁካታና ብጥብጥ ፈጥረዋል በሚል ወቀሳ ታስረው የነበሩት ፓስተር ብንያም ሽታዬ ዛሬ የካቲት ፲፯፤ ፳፻፲፭ በአምስት ሽህ ብር ዋስ ተለቀዋል፡፡ ለዚህም ውሳኔ መሳካት ከፍተኛ ርብርብ ያደረጉት ፴፫ የሚሆኑ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ የሕግ ጥበቆች መሆናቸው ታውቋል፡፡

የዝዋይ ገዳም ኮሌጅ የተመሠረተው ለማን ነው ?

በመጋቤ ብሉይ ቆሞስ አባ አትናቴዎስ
የገዳሙ ርዕሰ መምህርና የኮሌጁ የቦርድ አባል

በውጪ ሀገራት የሚገኙ አህጉረ ስብከት መረጃዎችን ከማዕከል እንዲወስዱና በማዕከል እንዲያሰራጩ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠ/ቤ/ክ ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መመሪያ አስተላለፉ።

የአፍሪካ ሕብረት ልዩ መልዕክተኛ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የአፍሪካ ሕብረት ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴጎ ኦባሳንጆን ዛሬ በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው በአፍሪካ ቀንድ ሰላም ዙሪያ አነጋገሩ።ቅዱስነታቸው ኦሊሴንጎ በሰላም ዙሪያ እያደረጉት ያለውን ጥረት በማድነቅ ምስጋና አቅርበውላቸዋል፤

ማኅበረ ቅዱሳንና ሀገር አቀፍ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ያዘጋጁት የ2015 ዓ.ም የከፍተኛ ት/ተቋማት ገቢ ተማሪዎች ሽኝት መርሐ ግብር ተከናወነ።

ወደ ከፍተኛ ት/ተቋማት የሚገቡ ተማሪዎች ትምህርታቸውን በሚከታተሉባቸው ጊዜያት ኦርቶዶክሳዊነታቸውን በማጠንከር እና በመንፈሳዊነታቸው በመበርታት ተምስጋኝ መሆን እንደሚገባቸው ብፁእ አቡነ ፊሊጶስ የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ሊቀ ጳጳስ ገልጸዋል።”