ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁን በተመለከተ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የሚዘዋወረው ዘገባ ከእውነት የራቀ ነው።

 

ሰሞኑን በአንዳንድ ማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህርዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስን በማስመልከት የሚሰራጩት ዜናዎች ፍጹም ከእውነት የራቁና ሕዝበ ክርስቲያኑን ለማደናገር የሚነዙ ሐሰተኛ ዘገባዎች ናቸው።

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በመንፈስቅዱስ ፈቃድና በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተጣለባቸውን ከባድ ኃላፊነት በብቃት፣በትጋትና በውጤታማነት እየተወጡ የሚገኙ ሲሆን ወደፊትም የጀመሯቸውን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና አስተዳደራዊ ተግባራትን የበለጠ በማጠናከር ቅድስት ቤተክርስቲያን የገጠሟትን ፈተናዎች ሁሉ በጽናት በመቋቋም በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው ጸሎትና ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ኃላፊነታቸውን አጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን በማክበር እንገልጻለን።

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ቅድስት ቤተክርስቲያን የጣለችባቸውን ከባድ ኃላፊነት በመተው ከጠቅላይ ሥራ አስኪያጅነታቸው ሊለቁ እንደሆነ በአንዳንድ ማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች እየተገለጸ ያለው ዘገባም ፍጹም ሐሰት መሆኑን በድጋሚ እየገለጽን ምዕመናን በአንዳንድ ማኅበራዊ የመገናኛ አውታሮች የሚነዛው መረጃ የሐሰት መሆኑን በመረዳት ለብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሥራ ስኬት በጸሎትና በተለያዩ መንገዶች ስታደርጉ የቆያችሁትን ድጋፍ አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት

ግንቦት ፳፩ ቀን ፳፻ ፲ወ ፭ ዓ.ም
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ

በባህርዳር የተገነባው ባለ ፮ ወለል ሁለ ገብ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ተመረቀ።

የባሕር ዳር ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል ገዳም ያስገነባው ባለ ስድስት ወለል ሁለ ገብ ሕንፃ በብፁዕ አቡነ አብርሃም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዛሬ ግግቦት ፳ ቀን ፳ ፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ተመርቋል።

የግንቦት ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የርክበ ካህናት ጉባኤ ባለ ፲ ነጥብ መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ።

ቅዱስ ሲኖዶስ ከግንቦት ፩ ቀን ፳፻ ፲ወ ፭ዓ.ም አስከ ግንቦት ፲፭ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ድርስ በ ፲፰ አጀንዳዎች ዙሪያ የርክበ ካህናት ጉባኤውን ሲያካሒድ ከቆየ በኋላ ዛሬ ግንቦት ፲፮ ቀን ፳፻ ፲ወ ፭ዓ.ም ፲ ነጦቦችን የያዘ መግለጫ በማውጣት ጉባኤውን አጠናቋል።

ቅዱስ ሲኖዶስ በ፯ኛ ቀን ውሎው በአራት አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ አሳለፈ።

ቅዱስ ሲኖዶስ ግንቦት ፱ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ባካሄደው ውይይት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ትምህርቷን ለትውልዱ የታስተምርበት ተቋማት አንዱ መንፈሳዊ ኮሌጆች መሆነቸውን አውስቷል፡፡ እነዚህ ኮሌጆች ወጥ የሆነ ሕግ ሳይኖራቸው የቆየ ሲሆን በቅርቡም በሐዋሳ እና በወልቂጤ የተቋቋሙት ኮሌጆች ባቀረቡት መተዳደሪያ ደንብ መሠረት፤ ቅዱስ ሲኖዶስ ውይይት አድርጎ ለሁሉም መንፈሳዊ ኮሌጆች የሚያገለግል ወጥ የሚሆን ሕግ አዘጋጅቶ ማጽደቁን ብፁዕነታቸው ገልጸዋል፡፡

የ2015 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት የሁለተኛው ቀን ውሎን አስመልክቶ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባባቢዋ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ማብራሪያ ሰጡ።

ቅዱስ ሲኖዶስ በ2ኛ ቀን ውሎው የተከፋፈለ ሲኖዶስ እንደሌለ እና ከዚህ ሐሳብ ውጪ የሆነ አካል ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕግና ሥርዓት ውጪ የሆነ መሆኑን በመግለጽ መንግሥትን የሚያነጋግሩ ልዑካን ሰይሟል። በቅዱስ ሲኖዶስ በትግራይ ያሉ አባቶችና አባላቱን በአካል የሚያነጋግሩ ብፁዓን አባቶች ተመርጠው ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል።

የቅዱስ ፓትርያርኩ የግንቦት ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ርክበ ካህናት ጉባኤ መክፈቻ ንግግር ሙሉ ቃል

የሰላም አለቃ፣የምሕረት አባት የሆነው ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅድስት የሆነችውን በዓለ ትንሣኤውን አክብረን ይህንን የረክበ ካህናት ቀኖናዊና ሲኖዶሳዊ ጉባኤ እንድናካሂድ ስለሰበሰበን ክብርና ምስጋና፣ አምልኮና ውዳሴ ለእሱ በማቅረብ፣እንኳን ደኅና መጣችሁ ለማለት እንወዳለን፡፡

በጠቅላይ ቤተክህነት እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ ሁለገብ አዳራሽ የግንባታ ሥራው ፹፯ ፐርሰንት መድረሱ ተገለጸ።

በሥልጠናው መዝጊያ ላይ የተገኙት ብጹዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በህዝብ ግንኘነት አስፈላጊነትና ለቤተክርስቲያን ያለውን ፋይዳ በዝርዝር ገልጸው ቤተክርስቲያን በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን በህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ዘመኑን የዋጀና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ሥራ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

ቅዱስ ፓትርያርኩ የመድኃኔዓለም በዓልን በምስካየ ኀዙናን መድኃኔዓለም ገዳም አከበሩ

በሥልጠናው መዝጊያ ላይ የተገኙት ብጹዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በህዝብ ግንኘነት አስፈላጊነትና ለቤተክርስቲያን ያለውን ፋይዳ በዝርዝር ገልጸው ቤተክርስቲያን በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን በህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ዘመኑን የዋጀና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ሥራ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

ለሁለት ቀናት ሲሰጥ የነበረው የህዝብ ግንኙነት የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተጠናቀቀ።

በሥልጠናው መዝጊያ ላይ የተገኙት ብጹዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በህዝብ ግንኘነት አስፈላጊነትና ለቤተክርስቲያን ያለውን ፋይዳ በዝርዝር ገልጸው ቤተክርስቲያን በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን በህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ዘመኑን የዋጀና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ሥራ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዓለ ንግስ ቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በታላቅ መንፈሳዊ ሥነሥርዓት ተከብሮ  ዋለ።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖትና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዓለ ንግሥ በአዲስ አበባ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ዛሬ ሚያዝያ ፳፫ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ,ም በከፍተኛ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ተከበረ ።