የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የመስቀል ደመራ በዓል የቅድመ ዝግጅት ሥራ በአምስት ማዕከላት በመከናወን ላይ ይገኛል።

September 19, 2023

መስከረም ፰ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
“””””””””””””””””””””””””””””””
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ
******
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል የቅድመ ዝግጅት ሥራውን እያከናወነ ነው።

መምሪያው በዛሬው ዕለት በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም የምሥራቅ ክፍለ ከተማ የመዝሙር ጥናቱን ያካሔደ ሲሆን በጥናት መርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስና የመምሪያው ዋና ኃላፊ መ/ብ ቆሞስ አባ ተክለያሬድ ዘጎርጎሬዎስ ተገኝተዋል።

የጥናት መርሐ ግብሩም ከታዕካ ነገሥት ቷዓታ ለማርያም ቤተክርስቲያን በተጨማሪ በከሰዓት በኋላ መርሐ ግብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የሰሜን ክፍለ ከተማ የወጣቶች የመዝሙር ጥናት መርሐ ግብር በመካሔድ ላይ ይገኛል።

በአጠቃላይ አሁኑ ጊዜ በ5 የጥናት ማዕከላት በዚህ መልኩ የጥናት መርሐ ግብሩ እየተካሔደ የሚገኝ ሲሆን የመዝሙርና የመንፈሳዊ ትርዒቱ በሚጀመርበት ጊዜ ሁሉ በየቀኑ የጸሎትና የትምህርት መርሐ ግብር ይከናወናል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ሰብሳቢነት በሚመራው ዐቢይ ኮሚቴ አማካኝነት የበዓሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራ በሚገባ እየተመራና አፈጻጸሙ በየጊዜው እነተገመገመ ሲሆን በቀናት በፊትም የሁሉም ንዑሳን ኮሚቴዎች የዕቅድ አፈጻጸም ተገምግሞ በቀሪ ቀናት የሚከናወኑ ሥራዎች አቅጣጫ የተሰጠባቸው መሆኑ ይታወሳል።

በዚህም መሰረት በዓሉ ፍጹም ሃይማኖታዊና ታሪካዊ በዓል መሆኑን ታሳቢ ባደረገ አግባብ ሕግና ሥርዓት ተከብሮ እንዲሰራ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ መመሪያ መሰጠቱ ይተወሳል።በተለይም ደግሞ የዘንድሮ የመስቀል ደመራ በዓል ሙስሊም ወገኖቻችን የመውሊድን በዓልን ከሚያከብሩበት ወቅት ጋር የተገጣጠመ በመሆኑ በመተሳሰብና በመተጋገዝ ፍጹም ክርስቲያናዊ ሥነምግባርን በተላበሰ አግባብ በዓላችንን እንድናከብር ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አደራ ማለታቸው ይታወሳል።

Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: በዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የደረሰውን ዝርፊያ በተመለከተ አሰፈላጊው ክትትል እየተደረገ ነው። Link to: በዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የደረሰውን ዝርፊያ በተመለከተ አሰፈላጊው ክትትል እየተደረገ ነው። በዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የደረሰውን... Link to: በውጭ አገር ለምትገኙ አህጉረ ስብከት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተላለፈ መልዕክት Link to: በውጭ አገር ለምትገኙ አህጉረ ስብከት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተላለፈ መልዕክት በውጭ አገር ለምትገኙ አህጉረ ስብከት ከኢትዮጵያ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top