የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ቅዱስ ሲኖዶስ ለውጭ አሁጉረ ስብከት ወጥ የሆነ መመሪያ እንዲያወጣ ብፁዕ አቡነ ሙሴ ጠየቁ።

October 20, 2023

ጥቅምት ፱ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
“””””””””””””””””””””””””””””
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
***

ብፁዕ አቡነ ሙሴ የምዕራብ አውስትራሊያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በ፵፪ኛው ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ የሀገረ ስብከታቸውን ሪፖርት አቅርበዋል።

ብፁዕነታቸው በሪፖርታቸው ባለፉት ሦስት ዓመታት በኮረና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ባለመቻላቸው በቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤዎች ሳይሳተፉ መቅረታቸውን ገልጸው በቅርቡ ደግሞ ቋንቋና ፖለቲካን ምክንያት በማድረግ በሀገረ ስብከታችን በተፈጠረውን ችግር ምክንያት ምዕመናን እንዳይለያዩ በቅርበት ለመቆጣጠርና ምክር ለመስጠት በዚያ ለመቆየት ተገድጃለሁ ብለዋል።

በግንቦት 2015 ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ ለስብሰባ መምጣታቸውን የገለጹት ብፁዕነታቸው በትግራይ ክልል በተፈጠረው ችግር ምክንያት በሀገረ ስብከታችን ስር በቆዩ ሦስት አብያተ ክርስቲያናትና በቅርቡ በእኛ ሥር የቆየን አንድ ቤተክርስቲያን ጨምረው በህገ ወጥ መንገድ ተሹመናል የሚሉ መነኮሳት ቋንቋና ፖለቲካን ምክንያት በማድረግ ወስደዋቸዋል ብለዋል።

አሁን የተወሰዱት አብያተ ክርስቲያናት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥር ይተዳደሩ የነበሩ መሆናቸውን የገለጹት ብፁዕነታቸው ቅዱስ ሲኖዶስ መተዳደሪያ ወይም መመሪያ በማዘጋጀት ተቋማዊ ሕልውናቸው እንዲረጋገጥ ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል።

በሀገረ ስብከታቸው በርካታ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደነበር የገለጹት ብፁዕ አቡነ ሙሴ በዚያው አገር ተወልደው ያደጉ 45ዲያቆናትና 4 ቀሳውስትን ለማዕረገ ክህነት ማብቃታቸውን ገልጸዋል።

በአሁኑ ጊዜ በሀገረ ስብከታቸው ሥር የሚገኙ ምዕመናን ለሁለት ተከፍለው እንደሚገኙ በሪፖርታቸው የገለጹት ብፁዕነታቸው ግማሾቹ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እና ከቅዱስ ሲንዶስ ጋር መሆናቸውን በመግለጽ ላይ የሚገኙ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ ተለይተናል በማለት ከህገ ወጥ ተሿሚዎቹ ጋር ወግነዋል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት በውጭ በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ችግር እየተፈጠረ ስለሆነ ቅዱስ ሲኖዶስ ወጥ የሆነ መመሪያ በማጣትና አህጉረ ስብከቱ ለሚገኙባቸው መንግሥታት በማሳወቅ ችግሩን ከመሰረቱ ሊፈታው ይገባል በማለትም ሪፖርታቸውን አጠቃለዋል።

በመጨረሻም ብፁዕነታቸው በአውስትራሊያ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥር የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት በየ ዓመቱ እንደሚደረገው ሁሉ ለሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ ገቢ የሚደረግ ገንዘብ እንዲልኩልኝ በተደጋጋሚ ያቀረብከት ጥያቄ ምላሽ ሊያገኝ ባለመቻሉ ከግል ገንዘቤ ለበረከት የሚሆን ሁለት ሺህ የአሜሪካ ዶላር ገቢ አድርጌያለሁ ብለዋል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙሃን ሥርዓት ድርጅት(EOTC TV) ለሥራ አፈጻጸሙ የሚያግዙትን ቁሳቁስ በማማላት ላይ ነው። Link to: የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙሃን ሥርዓት ድርጅት(EOTC TV) ለሥራ አፈጻጸሙ የሚያግዙትን ቁሳቁስ በማማላት ላይ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን... Link to: የ፵፪ ኛው አጠቃላይ ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የተለያዩ የአቋም መግለጫ ነጥቦችን በማውጣት ተጠናቋል። Link to: የ፵፪ ኛው አጠቃላይ ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የተለያዩ የአቋም መግለጫ ነጥቦችን በማውጣት ተጠናቋል። የ፵፪ ኛው አጠቃላይ ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top