የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የከተራ፣የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በአላማጣ በድምቀት ተከብሮ ዋለ።

January 23, 2024

ጥር ፲፬ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
————————-

የከተራ፣የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በራያ አላማጣና በስድስቱ ወረዳዎች በታላቅ መንፈሳዊ ሥነሥርዓት ተከብሮ መዋሉን የሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤት በላከልን ዘገባ ገለጸ።ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ተወልደው ባደጉበት ራያ አላማጣ ከተማ ከሦስት ዓመታት በኋላ በዓላቱን እንዳከበሩ የገለጸው የሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤት ሕዝበ ክርስቲያኑ በነቂስ በመውጣት በዓሉም ፍጹም ሰላማዊና ደማቅ በሆነ መልኩ ማክበሩን ገልጿል።

በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረው ጦርነት ካቆመ በኋላ በድምቀት በተከበረው በዓል ላይ የተገኙት ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ችግሮቹ ሁሉ ተወግደው ሰላማዊ በዓል ለማክበር ያበቃን ልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ይገባዋል ካሉ በኋላ ያገኘነውን ሰላም በመጠበቅና በመንከባከብ የተቸገሩ ወገኖቻችንን በመርዳትና በመደገፍ በዓሉን ልናከብረው ይገባል በማለት አታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ብፁዕነታቸው ከዚሁ ጎን ለጎን በአላማጣ ከተማ በዓይነቱና በስፋቱ ልዩ የሆነውን የአላማጣ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ለማሰራት የመሰረት ድንጋይ አኑረዋል፤አዲስ የሚሰራውን የአላማጣ ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያንን ሕንጻ ቤተክርስቲያን ጎብኝተው ለተሰበው ሕዝበ ክርስቲያንም የማጽናኛ ትምህርት፣ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጥተዋል።

በአላማጣ አካባቢ በሚገኘው የራያ ባላ ወረዳ ምሥራቀ ጸሐይ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያንና በአምስት የገጠር አብያተክርስቲያናት ሐዋርያዊ ጉዞ በማድረግም ሕዝበ ክርስቲያኑን በማጽናናትና በማስተማር አባታዊ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ የሰጡ ሲሆን የተሰሩ የልማት ሥራዎችንም በመጎብኘት አባታዊ የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።ብፁዕነታቸው ሐዋርያዊ ጉዞ ባደረጉበት ቦታ ሁሉ ሕዝበ ክርስቲያኑ በነቂስ በመውጣት ደማቅ አቀባበል አድርጎላቸዋል ሲል የሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤት በላከልን ዘገባ ገልጿል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም የጌታችን፣ የአምላካችን፣ የመድኀኒታችን፣ የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል ሰላማዊ በሆነ መልኩ ተከብሮ እንዲውል ላደረጋችሁ ሁሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምስጋናዋን ታቀርባለች፤ Link to: የ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም የጌታችን፣ የአምላካችን፣ የመድኀኒታችን፣ የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል ሰላማዊ በሆነ መልኩ ተከብሮ እንዲውል ላደረጋችሁ ሁሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምስጋናዋን ታቀርባለች፤ የ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም የጌታችን፣ የአምላካችን፣ የመድኀኒታችን፣... Link to: በጋምቤላ ሀገረ ስብከት በጋምቤላ ከተማ የመድኃኔ ዓለም እና የአቡነ አረጋዊ ታቦታተ ሕግ ወደመንበረ ክብራቸው በሰላም ገብተዋል። Link to: በጋምቤላ ሀገረ ስብከት በጋምቤላ ከተማ የመድኃኔ ዓለም እና የአቡነ አረጋዊ ታቦታተ ሕግ ወደመንበረ ክብራቸው በሰላም ገብተዋል። በጋምቤላ ሀገረ ስብከት በጋምቤላ ከተማ የመድኃኔ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top