የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ሰንበት ት/ቤቶች ከመዘመር ባሻገር መሠረተ ሃይማኖት ላይ ትኩረት ሊያደርጉ ይገባል። (ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ)

September 14, 2024

መስከረም 2 ቀን 2017 ዓ.ም (ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት)
=============================

የወልድያ ከተማ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ትናንት መስከረም 1 ቀን የዘመን መለወጫ በዓልን በማስመልከት ለሀገረ ስብከቱ ብፁዓን አባቶች የእንኳን አደረሳችሁ መርሐ ግብር አካሂዷል። ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት በመርሐ ግብሩ ለተገኙ የሰንበት ት/ቤት አባላት አባታዊ መልእክትና የአገልግሎት መመሪያ አስተላልፈዋል። ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ የሰንበት ትምህርት ቤቶችን ለማጠናከር የደከሙት ድካም ከፍተኛ መሆኑን የጠቀሱት ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የብፁዕነታቸውን ህልም ለማሳካት ሀገረ ስብከቱ አቅዶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑንም አብራርተዋል።

መሪ እቅዱ ለይስሙላ ሳይኾን በትክክል ተግባራዊ እንዲሆን ሰንበት ትምህርት ቤቶችን የሚያጠናክር የሐዲሳት መጻሕፍት ትርጓሜ መምህር የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል ኀላፊ አድርጎ ከመመደብ ባሻገር 5 አሠልጣኝ መምህራን በጠቅላይ ቤተክህነት መሠልጠናቸውንና ሥርዐተ ትምህርቱን ለመተግበር ጥረት እየተደረገ መሆኑን ብፁዕነታቸው ተናግረዋል። የሀገረ ስብከቱና የወረዳዎች የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ተግባራዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ለሚስተዋሉ ክፍቶች የመፍትሒ አካል እንድሆኑና አባላቱም እንዲያግዟቸው አሳስበዋል። ትልቁ ሥራችን ሰው ማትረፍ ነውና ኹላችንም የጋራ ሥራ ሠርተን፥ የጋራ ውጤት ማምጣት አለብን ያሉት ብፁዕነታቸው በበዓላት ከመዘመር ባለፈ መሠረተ ሃይማኖት ላይ በማተኮር በእምነትም በምግባርም መጠንከርና ስለሚዘመረው ጉዳይም በቂ እውቀት ሊኖረን ይገባል ብለዋል።

ክርስትናችንን ማስፋት የምንችለው መሠረተ እምነቱን ማወቅ ስንችል ነው ያሉት ብፁዕነታቸው የጸሎተ ሃይማኖትን 12 ቱን አንቀጾች መያዝና ማብራራት መቻል፣ በትምህርተ ሃይማኖት፥ በነገረ ቅዱሳን፣ በምሥጢረ ሥላሴና በምሥጢረ ሥጋዌ ትውልድን ለመቅረጽ መዘጋጀት እንዳለባቸው አባታዊ መመሪያ አስተላልፈዋል። መረጃውን ያደረሰን የሀገረ ስብከቱ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ነው።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: በሲዳማ ሀገረ ስብከት በሀዋሳ ከተማ በደብረ ሰላም ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ  በዓል በታላቅ ድምቀት ተከበረ። Link to: በሲዳማ ሀገረ ስብከት በሀዋሳ ከተማ በደብረ ሰላም ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ  በዓል በታላቅ ድምቀት ተከበረ። በሲዳማ ሀገረ ስብከት በሀዋሳ ከተማ በደብረ ሰላም... Link to: በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት በብፁዕ አቡነ በርተሎሜዎስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የተመራ የመስቀልና ደመራን በዓል አስመልክቶ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመንበረ ጵጵስና አዳራሽ ስብሰባ ተካሄደ። Link to: በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት በብፁዕ አቡነ በርተሎሜዎስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የተመራ የመስቀልና ደመራን በዓል አስመልክቶ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመንበረ ጵጵስና አዳራሽ ስብሰባ ተካሄደ። በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት በብፁዕ አቡነ በርተሎሜዎስ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top