አሥሩን ነጥቊቜ ያለመሞራሚፍ ለመተግበር እነ አቡነ ሳዊሮስ ተስማሙ።ወቅታዊ መግለጫ

******
ዚካቲት ፲፩ቀን፳፻ ፲ወ፭ዓ.ም
“””””””””””””””””””””””””””
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
******

ጥር ፰ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ክቡር ዚኢፌዎሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አህመድ በተገኙበት ኚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን ሊስት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና እነ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በተገኙበት በተደሹገው ውይይት ፲ ዚስምምነት ነጥቊቜ ተቀምጠው በነጥቊቹ ላይ ዚጋራ መግባባት ኹተደሹሰ በኋላ ዚጋራ መግለጫ በመስጠት ስምምነቱ መጜደቁ ይታወሳል።

ይህን ተኚትሎም ስምምነቱን ሙሉ ለማድሚግና ዕርቁን ተቋማዊ ለማድሚግ በማሰብ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ እነ አቡነ ሳዊሮስን በመያዝ ወደ መንበሹ ፓትርያርክ በማምጣት ኚቅዱስነታ቞ው ጋር እንዲገናኙ ማድሚጋ቞ው ይታወሳል።

ዛሬ ዚካቲት ፲፩ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያንን በመወኹል በስምምነቱ ላይ ዚተሳተፉት ብፁዓን አባቶቜና እነ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በመንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጜሕፈት ቀት ጜርሐ መንበሹ ፓትርያርክ ተገናኝተው ሰፊ ውይይት ካደሚጉ በኋላ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት ዹተደሹሰውን ስምምነት በምንም መልኩ መጣስ እንደሌለበት በመተማመን በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫውም “በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ዹተፈጠሹውን ቜግር ለመፍታት ክቡር ጠቅላይ ሚ/ር ዶ/ር አብይ አሕመድ በተገኙበት ዚካቲት ፰ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ/ም በተደሹገው ውይይት ዚተስማማንባ቞ውን (፲) ዐሥር ነጥቊቜ ያለመሞራሚፍ ለመፈጾም እንዲሁም ቀጣዩን ተግባር በተመለኹተ በቅዱስ ሲኖዶስ አማካኝነት ለማኹናወን ተስማምተናል። በማለት ይፋዊ መግለጫ ሰጥተዋል። ኚመግለጫው በኋላም ወደ ማሚፊያ ቀታ቞ው ገብተዋል።

ዹመንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጜሕፈት ቀትም ዚአባቶቜን መመለስ ተኚትሎ ዚጞጥታ ሥራው አስተማማኝ መሆን ይቜል ዘንድ ጠቅላይ ቀተ ክህነቱ በሕጋዊ መልኩ ጥበቃ ሊደሚግለት እንደሚገባ በማመንና ጞጥታውን አስተማማኝ ለማድሚግ እንዲሁም ዚጥበቃ ሥራውን ተቋማዊ በሆነ መልኩ ዚሚያኚናውኑ ዚፌደራል ፓሊስ አባላት እንዲመደቡለት ያቀሚበው ጥያቄ ተቀባይነት ስላገኘ ኚፌደራል ፓሊስ ኮሚሜን ዚፓሊስ አባላት ተመድበው ዹጠቅላይ ቀተ ክህነቱን ዚጥበቃ ሥራ እያኚናወኑ ይገኛሉ።

በአጠቃላይ በትላንትናው ዕለት ዹነበሹው ሁኔታ ኹፍ ሲል በተጠቀሰው አግባብ ዚተስተካኚለ መሆኑን እዚገለጜን ዹተጀመሹው ዹሰላም ሂደት ግቡን ይመታ ዘንድ ምዕመናንና ምዕመናት በወርሃ ጟሙ ወደ ልዑል እግዚአብሔር አጥብቀው በመጾለይ እንዲተጉ ቅድስት ኊርቶዶክሳዊት ቀተክርስቲያናቜን ጥሪዋን ታስተላልፋለቜ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን
ጠቅላይ ጜሕፈት ቀት ዚሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

በቀድሞ ስማ቞ው እነ አቡነ ሣዊሮስ ስምምነቱን ሳይሞራሚፍ እንደሚቀበሉና ተግባራዊ እንደሚያደርጉ በቅዱስ ሲኖዶስ በመገኘት ቃላቾውን ሰጥተው አሚጋግጠዋል።

በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ዹተፈጠሹውን ቜግር ለመፍታት ክቡር ጠቅላይ ሚ/ር ዶ/ር አብይ አሕመድ በተገኙበት ዚካቲት 8 ቀን 2015 ዓ/ም በተደሹገው ውይይት ዚተስማማንባ቞ውን (10) ዐሥር ነጥቊቜ ያለመሞራሚፍ ለመፈጾም እንዲሁም ቀጣዩን ተግባር በተመለኹተ በቅዱስ ሲኖዶስ አማካኝነት ለማኹናወን ተስማምተናል። ዚካቲት 11 ቀን 2015 ዓ/ም

በሾገር ሲቲ በፉሪ ክ/ኹተማ04 ፓሊስ ጣቢያ ታስሚው ኚነበሩ እስሚኞቜ መካኚል ኚአንድ መቶ በላይ ዚሚሆኑት መፈታታ቞ውን ብፁዕ አቡነ ጎጥሮስ ዶ/ር ገለጹ።

*******
ዚካቲት 10 ቀን 2015ዓ.ም
“”””””””””””””””””””””””
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ
******
ብፁዕ አቡነ ጎጥሮስ ዶ/ር በሾገር ሲቲ በ ፉሪ ኹ/ኹተማ 04 ፖሊስ ጣብያ ዹሚገኙ እስሚኞቜን ጠነቁ።ብፁነታ቞ው በፓሊስ ጣቢያው ዹሚገኙ ወጣት ዚሰንበት ትምህርት ቀት ተማሪዎቜን በእስር ቀቱ በመገኘት ኹጠዹቁና ካጜናኑ በኋላ ኚሚመለኚታ ቾው ዚአቃቀ ሕግና ዚፖሊስ ጣቢያው ኋላፊዎቜ ጋር ውይይት አድርገዋል ። ኚውይይቱ በኋላም ኚአንድ መቶ ሃምሳ በላይ እስሚኞቜ ተፈተዋል። ሲሉ ብፁዕነታ቞ው ገልጞውልናል።

ብፁዕነታ቞ው በጉብኝታ቞ው ወቅት ኚአቃቀ ሕጉና ኚፓሊስ ኃላፊዎቜ ለተደሹገላቾው ግሩም ዹሆነ መስተንግዶና አቀባበል ዹተሰማቾውን ደስታ በመግለጜ ምስጋና቞ውን በቅድስት ቀተክርስቲያን ስም አቅርበዋል።ዚቀሩትና በፓሊስ ጣቢያው ውስጥ ዹሚገኙ እስሚኞቜም በአጭር ቀናት ውስጥ እንደሚፈቱ ኚአቃቀ ህጉና ኚፓሊስ ኃላፊዎቹ ማሚጋገጫ እንደተሰጣ቞ው ብፁዕነታ቞ው ጹምሹው ገልጞዋል።

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ

 

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜንፀ

• በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ዚምትገኙ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ምእመናንና ምእመናት እንዲሁም ኢትዮጵውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ!
እንደ ስሑትና ደካማ ሰብአዊ ባሕርያቜን ሳይሆን እንደ አባታዊ ቞ርነቱ ሁል ጊዜ በምሕሚቱ ዹሚጐበኘን አምላካቜን እግዚአብሔር እንኳን ለጟመ ኢዚሱስ አደሚሰንፀ አደሚሳቜሁ!
• “ንጹም ጟመ፣ ወናፍቅር ቢጞነ፣ እስመ ኹማሁ አዘዘነ፡- ጟምን እንጹም፣ ባልንጀራቜንንም እንውደድ፣ እንዲህ አዞናልና” (ቅዱስ ያሬድ)
እግዚአብሔር በዚህ ዓለም ስንኖር፣ እንድናደርገው ያዘዘን ዓቢይ ነገር ቢኖር ፍቅር ነው፡፡ እግዚአብሔር ፍጥሚታትን ፈጥሮ እዚመገበ ዹሚገኘው በፍቅር ነው፡፡ እኛንም ኚፍዳ ኃጢአት ያዳነን በፍቅር ነው፡፡ ሕይወታቜንና ንብሚታቜን ተጠብቆ ዹሚኖሹው ፍቅር ሲኖር ነው፡፡
ግላዊና ማኅበራዊ ኑሮአቜን እንዲሁም ሃይማኖታዊ አምልኮአቜንና ዚተግባር እንቅስቃሎአቜን በሙሉ ውጀታማ ሊሆን ዚሚቜለው ፍቅር ሲኖር ነው፡፡
በፍቅር ውስጥ በሚኚት እንጂ ጉድለት ዚለምፀ በፍቅር ውስጥ ጀና እንጂ በሜታ ዚለምፀ በፍቅር ውስጥ ጜድቅ እንጂ ኃጢአት ዚለምፀ በፍቅር ውስጥ እግዚአብሔር እንጂ ዲያብሎስ ዚለም፡፡ ይህም በመሆኑ ቅዱስ መጾሐፍ ፍቅርን ‹‹ዚሁሉም ነገር ማሰሪያ ነቜ›› በማለት ይገልጻታል፡፡
ጌታቜን አምላካቜንና መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስም ኹሁሉም ዚምትበልጠው ታላቋ ትእዛዝ ‹‹ፍቅር›› እንደሆነቜ ኹመግለፁም በላይ ኊሪትና ነቢያት ሁሉ በእሷ እንደሚጠቃለሉ አስተምሮናል፡፡

ዚተወደዳቜሁ ዚመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቜን ምእመናንና ምእመናት!
ፍቅርን እንደ ዓይን ብሌን ስንጠብቃት በእጅጉ ዚምትጠቅመንን ያህል ጣል ጣል ስናደርጋት ደግሞ በእጅጉ ትጎዳናለቜ፡፡ በፍቅር እጊት ዹሚደርሰው ጉዳት በተወሰነ ነገር ብቻ ሳይሆን በነፍስም ሆነ በሥጋ፣ በምድርም ሆነ በሰማይ እጅግ በጣም ዹገዘፈና ዹሰፋ ነው፡፡ በሀገራቜን ዹሆነውና እዚሆነ ያለውም ይኾው ነው፡፡ ፍቅርን ባጣንባ቞ው ዓመታት ኚዚት ወዎት እንደደሚስን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዹሚገነዘበው ነው፡፡ ያተሚፍነው ነገርም ምን እንደሆነ ዹምናውቀው ነው፡፡  ይሁንና ዹፍቅር እጊት ምን ያህል እንደጎዳን ራሳቜን ተገንዝበን ወደ ሰላሙ መንገድ መመለሳቜን ዚተሻለ አማራጭ መሆኑን ሳንመሰክር አናልፍም፡፡ ዹተጀመሹው ዹፍቅርና ዹሰላም ጉዞም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ልባዊ ምኞታቜንና ጞሎታቜን ነው፡፡  ይህንን ሰላም እንዲመጣ ያደሚጉ ወገኖቜም ሁላቾውን ሳናመሰግን አናልፍም፡፡ ምክንያቱም በሰዎቜ መካኚል ፍቅርንና ሰላምን ዚሚያደርጉ ዚእግዚአብሔር ልጆቜ ይባላሉ ብሎ ጌታ እንደ አስተማሚን ብፅዕና ይገባ቞ዋልና ነው፡፡

ዚተወደዳቜሁ ዚመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቜን ምእመናንና ምእመናት!
ዚፍጹም ፍቅር መገኛ ዹሆነው ቅዱስ ወንጌል ዚሚያስተምሚው ፍቅር፣ ራስን ማፍቀር ወይም መውደድ ሳይሆን ራስን መጥላት ባልንጀራን ግን መውደድ ነው፡፡ ወንጌላዊ-ፍቅር ፍጹም ነው ዚሚያሰኘውም ቅሉ ይህ ነው፡፡ ለሁለት ሺሕ ዘመናት ያህል በቅዱስ ወንጌል አስተምህሮ ላይ ዚተገነባው ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ቅዱስ ባህልም ይህን ፍቅር ጠብቆ ዹሚጓዝ ነው፡፡ ይህም በመሆኑ ዚኢትዮጵያ አበው መነኮሳት ኚነበራ቞ው ፍቅርና ትሕትና ዚተነሣ፣ ዚሹመት ሜሚያ አያውቁም ነበር፡፡ ኹዚህ አንጻር ትልቁን ሥልጣን ይቅርና ዚአንድ ገዳም መሪ ለመሆንም በእግር ብሚት ታስሚው በግድ ካልሆነ በቀር እሺ ብለው በፈቃደኝነት ሹመትን አይቀበሉም ነበር፡፡ ራሱን በራሱ መሟም ወይም እኔን ሹሙኝ ብሎ መናገርና ዹሌላን ድጋፍ መጠዹቅ ለኢትዮጵያውያን መነኮሳት ጭራሜ ነውርና ጞያፍም ነበር፡፡ ያም በመሆኑ ነው ኹዘመነ ብሉይ ጀምሮ ለሊስት ሺሕ ዘመናት ዹዘለቀው ሃይማኖታቜን ምንም ዓይነት መለያዚት ሳያጋጥመው አንድ ሆኖ ሊዘልቅ ዚቻለው፡፡ ይህ ዚቀተ ክርስቲያናቜን ጠንካራ አንድነት ለሕዝቡም በመትሚፉ ዚሀገሪቱን አንድነትና ነጻነት አስጠብቆ እስኚ ዘመናቜን ሊደርስ ቜሎአል፡፡ በዚህም ቀተ ክርስቲያናቜን ዚሕዝብንና ዹሀገርን አንድነትና ነጻነት ለማስጠበቅ ያደሚገቜውና ዚምታደርገው ጥሚት ሊያስመሰግናት እንጂ ሊያስወቅሳት አይገባም፡፡

ዚተወደዳቜሁ ዚመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቜን ምእመናንና ምእመናት!
ኚቅርብ ቀናት ወዲህ በቀተ ክርስቲያናቜን ተኚሥስቶ ዹነበሹውን ሕጋዊ ያልሆነ ድርጊት ዚቀተ ክርስቲያናቜንን ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና ባሕላዊ መርሕን ዚናደ፣ እንደዚሁም በኢትዮጵያ ይቅርና በዓለም ታሪክ ተደርጎ ዚማያውቅ ድርጊት እንደሆነ ቀተ ክርስቲያናቜን በአጜንዖት ስትገልጜ ቆይታለቜ፡፡ ይህንን ዚቀተ ክርስቲያን ድምፅ በመስማትና በመቀበል ሕዝበ ክርስቲያንና ኢትዮጵያውያን ሁሉ ለእግዚአብሔር ባቀሚቡት ኃዘንና ጞሎት እንደዚሁም ባደሚጉት መጠነ ሰፊና ዙርያ መለስ ዹሆነ ዚድጋፍ ርብርብ ስሕተቱ ሊታሚም ቜሏል፡፡ ለተገኘው መንፈሳዊ ውጀትም ክቡር ጠቅላይ ሚንስትርና መንግሥታ቞ውን፣ ዚቀተ ክርስቲያን አንድነትና ሉዓላዊነት እንዲኚበር ኹፍተኛ መሥዋዕትነት ለኹፈለው መላው ሕዝበ ክርስቲያን እንዲሁም ይህ ስሕተት እንዲታሚም ኚቀተ ክርስቲያናቜን ጎን ተሰልፈው ድምፃ቞ውን ላሰሙ ኢትዮጵያውያንና ዹውጭ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ በቀተ ክርስቲያናቜን ስም ኹፍ ያለ ምስጋና እናቀርብላ቞ዋለን፡፡ በዚህ አጋጣሚ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ልጆቻቜን ግልፅ ማድሚግ ዹምንፈልገው ኚቀተ ክርስቲያናቜን ዶግማ፣ ቀኖና እና ሥርዓት መኹበር እንደዚሁም ኹሉዓላዊ አንድነቷ መጠበቅ በመለስ ያለው ጥያቄ ለማስናገድ ቀተ ክርስቲያናቜን ዝግጁ መሆኗን ነው፡፡ ቀተ ክርስቲያናቜን ሕዝቊቜ በቋንቋቾው ዚመማር፣ ዚማስተማርና ዹማምለክ እንዲሁም ዚመተዳደር መብትን ካሁን በፊትም፣ አሁንም፣ ካሁን በኋላም ዚምትነፍግበት መሠሚት እንደሌለም ሁሉም ሊያውቀው ይገባል፡፡ ይህም በመሆኑ በቋንቋ ዹመጠቀም መብት በሕገ ቀተ ክርስቲያናቜን ምዕራፍ 2 አንቀጜ 5 ኚቁጥር 1-3 ባለው አንቀጜ በሚገባ ተቀምጩ ይገኛል፡፡ ስለሆነም በቋንቋ ዹመጠቀም ጥያቄ በሕግ ደሹጃ ተመልሶ በተግባር እዚተሰራበት ዹሚገኝ መሆኑን ሁሉም ሊገነዘበው ይገባል፡፡

ዚተወዳቜሁ ዚመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቜን ምእመናንና ምእመናትፀ
ዛሬ ታላቁን ጟማቜን በፍቅር ሆነን ዚምንጟምበት ወቅት ነው፡፡ ሁላቜንም እንደምናውቀው ጟም ማለት ስጋዊ ፈቃድን በመግታት ኚእግዚአብሔር ጋር ጥብቅ ግንኙነት ለማድሚግ ዚሚካሄድ መንፈሳዊ ተጋድሎ ነው፡፡
በጌታቜን ጟም በተግባር እንዳዚነው ጟም ማለት ዲያብሎስ ዚሚሞነፍበት በአንጻሩ ደግሞ ዚእግዚአብሔር ሕዝብ አሞናፊዎቜ ዚሚሆኑበት ኃይል ነው፡፡
ስለሆነም ጟም ዚተጋድሎና ዚሙዓት ሜዳ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ዚምንታገለውም ልቡሰ ሥጋ ሰውን ሳይሆን ሹቂቅ ፍጡር ዹሆነው ሰይጣን በሰው አድሮ ዹሚነዛውን አጥፊ ሐሳቡንና ድርጊቱን ነው፡፡
ኹዚህም ጋር ሰውነታቜን ለዚህ ክፉ መንፈስ ታዛዥ እንዲሆን ዹሚገፋፉ ጥሉላት መባልዕትን መተውፀ ኃይለ ሥጋን መቈጣጠርፀ ኃይለ መንፈስን ደግሞ ማጎልበት ያስፈልጋል፡፡ በጟም ወቅት ዚተራቡትን ማጉሚስ ዚታሚዙትን ማልበስ ዚተበደሉትን መካስ፣ ፍትሕና ርትዕ በማኅበሹ ሰብ ውስጥ ማንገሥ ያስፈልጋል፡፡

በጟም ወቅት ኅሊናቜን ማሰላሰል ያለበት ሰው ምን አለ? ወይም ምን አደሹገ? በሚለው ሳይሆን እግዚአብሔር በፊቱ ምን ዓይነት ሰው እንድንሆንለት ይፈልጋል? በሚለው ላይ ነው፡፡
ስለዚህ ጟማቜን በዚህ መንፈስ ዹተቃኘ ፍቅሚ፣ እግዚአብሔርንና ፍቅሹ ቢጜን ማእኚል ያደሚገ፣ መጠራጠርንና አለመተመማንን ያስቀሚ፣ ዚተለያዩትን ያቀራሚበ፣ ዚተሳሳቱትን ያሚመ በአንጻሩ ደግሞ ሁላቜንን በሰላምና በፍቅር አንድ አድርጎ ያስተሳሰሚ ይሆን ዘንድ በዚህ መንፈስ ተነቃቅተን እንድንጟመው አባታዊ ጥሪያቜንን ለሕዝበ ክርስቲያኑ እናስተላልፋለን፡፡

በመጚሚሻምፀ
በሀገራቜን እዚታዚ ያለው ዹሰላም ጭላንጭልና ቜግሮቜን በውይይት ዚመፍታት ዝንባሌ በእጅጉ ጠቃሚና ለሁለንተና ልማታቜንና ለዕድገታቜን እንደዚሁም ለተሟላ አንድነታቜን ጠቃሚነቱ ዹጎላ ስለሆነ እግዚአብሔር ለዘለቄታው እንዲያሳካልን ኚልብ እንድናዝንና ወደ አምላካቜን በተመሥጊ እንድንጞልይ በአጜንዖት በማሳሰብ አባታዊ መልእክታቜንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡
መልካም ዚጟም ወራት ያድርግልን!
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቊቜዋን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር! አሜን

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስምወዕጚጌ ዘመንበሹ ተክለ ሃይማኖት
ዚካቲት ፲፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

ዹመንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጜሕፈት ቀት አስተዳደር ጉባኀ በወቅታዊ ጉዳዮቜ ዙሪያ ተወያይቶ ልዩ ልዩ ውሳኔዎቜን አስተላለፈ ።


**********
ዚካቲት ፱ቀን ፳ ፻ ፲ወ፭ ዓ.ም
“”””””””””””””””””””””””””
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ

በብፁዕ ኚቡነ አብርሃም ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና በባህር ዳር ሀገሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ ዚሚመራው ዹጠቅላይ ቀተክህነት አስተዳደር ጉባዔ በወቅታዊ ዚቀተክርስቲያን ጉዳዮቜ ዙሪያ ዛሬ ዚካቲት ፱ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ባደሚገው መደበኛ ስብሰባ ልዩልዩ ውሳኔዎቜን አስተላለፈ።

ጉባኀው በቀተክርስቲያናቜን ዹተደሹሰውን ስምምነት አስመልኚቶ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ዹተሰጠውን ሰፊና ጥልቅ ማብራሪያ ካዳመጠ በኋላ በጉዳዩ ዙሪያ ሰፊ ውይይት በማድሚግ ዚሚኚተሉትን ውሳኔዎቜ አስተላልፏል።

፩ኛ በትላንትናው ዕለት በቅዱስ ሲኖዶስና ተወግዘው በተለዩት አባቶቜ መካኚል ዹተደሹሰውን ስምምነት በማድነቅ ተቀብሎታል። ለአፈጻጞሙም ዚሚጠበቅበትን ሁሉ ለማበሚሰኚት ቃል ገብቷል።

፪ኛ እርቀ ሰላሙ በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ ኹፍተኛ አስተዋጜኊ ላበሚኚቱና ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያንን ወክለው ለተወያዩ ብፁዓን አባቶቜ፣ ተወግዘው ተለይተው ለነበሩ አባቶቜ ኹሁሉም በላይ ለቀተክርስቲያን አንድነት ቅድሚያ በመስጠት ለፈጞሙት ታሪካዊ ስምምነት አድናቆቱንና ምስጋናውን አቅርቧል።

፫ኛ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ቅዱስ ፓትርያርኩ ፣ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና ብፁዕ ዚቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጾሐፊው ዚቅድስት ቀተክርስቲያንን ሉአላዊ ክብርና ቀኖናዊ ሥርዓቱን ለማስጠበቅ ዚኚፈሉትን መስዋዕትነት በማድነቅ ስምምነቱ ዚቀተክርስቲያናቜንን መብት ባስኚበሚ መልኩኩ እንዲፈጞም በማድሚጋ቞ው ዹተሰማውን ልባዊ ደስታ ኚመግለጜ ጋር ስምምነቱን ተኚትሎ ለሚኹናወነው ተቋማዊ ዕድገት ዚበኩሉን አስተዋጜኊ ሁሉ በፍጺም ትጋት ለመፈጾም ዝግጁነቱን ገልጿል።።

፬ኛ ክቡር ዚኢፌዎሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አህመድ ኹዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን ሀገር ናት በማለት ዚሚገልጹትን ሀቅ በማጠናኹር እርቀ ሰላሙን ተኚትሎ “ሙሜራው ክርስቶስ እስኚሚመጣበት ድሚስ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን አንድነቷ ተጠብቆ ይኖራል።” በማለት እርቀ ሰላሙ ኚልብ እንዲኚናወን ያደሚጉትን ጥሚት በማድነቅ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ልባዊ ምስጋናውን አቅርቧል።

፭ኛ ዚቀተክርስቲያን ቀኖና አይጣስም አንድነቷ አይናጋም በማለት ቅድስት ኊርቶዶክሳዊት ቀተክርስቲያንን ለማስኚበር ክቡር መስዋዕትነት ለኚፈላቜሁ ዹዘመኑ ሰማዕታት፣ለዕስርና ለእንግልት ዚተዳሚጋቜሁ ኊርቶዶክሳዊያን፣ለግርፋትና ለአካል ጉዳት ዚተዳሚጉ ልጆቻቜን ሁሉ ክብርና ምስጋና ይገባ቞ዋል ያለው ጉባኀው ለሰማዕታት መንግስተ ሰማያትን እንዲያወርስልን፣ዚአካልና ዚሥነ አእምሮ ጉዳት ለደሚሰባ቞ው ምሕሚትን ለልዑል እግዚአብሔር ይስጥልን ወዳጅ ዘዶቻ቞ውንም ያጜናናልን፣ዚታሰሩትንም ያስታልን በማለት ዚታሰሩ ዚቀተክርስቲያን ልጆቜን ለማስፈታት በሚደሹገው ጥሚት ዚሚጠበቅበትን ሁሉ ለማበርኚት ቃል ገብቷል።

፮ኛ በዚህ ፈታኝ ወቅት ዚቀተክርስቲያንን ሉዓላዊነትና ቀኖናዊ አንዎነትን ለማስኚበር በተደሹገው ተጋድሎ ኚቅድስት ቀተክርስቲያን ጎን በጜናት ዚቆማቜሁ በዹደሹጃው ዚምትገኙ ዹአህጉሹ ስብኚት ሥራ አስኪያጆቜና ዚጜሕፈት ቀት ሰራተኞቜ፣ዚቀተክርስቲያን አገልጋዮቜ፣ ማኅበራት፣ወጣት ልጆቻቜን ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን ዹመገናኛ ብዙሃን ድርጅት፣ዚቀተክርስቲያናቜን ዚሕዝብ ግንኙት መምሪያ፣ዚማኅበሚ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት በሚዲያው ዘርፍ ለተሰማሩሩ ልዩልዩ ዚሚዲያ ተቋማት አክቲቪስቶቜና ጞሐፊያን ሁሉ ቀተክርስቲያናቜን ልባዊ ምስጋናዋን ታቀርባለቜ።

፯ኛ ዚቀተክርስቲያናቜን ጉዳት ጉዳታቜን ነው ኚቀተክርስቲያናቜን ጎን በጜናት እንቆማለን ፀቜግሩን ዚቀተክርስቲያንን መብትና ጥቅም በሚያስኚብር መልኩ በሰላማዊ መንገድ እንፈታዋለን በማለት ሊገለጜ ዚማይቜል ተጋድሎና እልህ አስጚራሜ ፈተናዎቜን በጜናት አልፋቜሁ ይህን ዕርቀ ሰላም እውን ያደሚጋቜሁ ዚመፍትሔ አፈላላጊና ዚሜምግልና ሥራ ዚሰራቜሁ ባለሀብቶቜና አትሌቶቜ ልፋታቜሁ እንኳን ፍሬ አፍርቶ ለማዚት በቃቜሁ እንኳንም ደስ አላቜሁ። በማለት ልባዊ ምስጋናቜን እናቀርብላቜኋለን።

፰ኛ በዚህ ፈተና ጊዜ ቀተክርስቲያንን አናስደፍርም፣ ዚቀተክርስቲያንን ጥሪ ተቀብለን ቀተክርስቲያንን እናስኚብራለን በማለት ውድ ሕይወታ቞ውን በመስዋዕትነት ላቀሚቡ ሰማዕታት ቀተሰቊቜ፣ዚአካልና ዚሥነ አእምሮ ጉዳት ዚደሚሰባ቞ውን ወገኖቜን ለመደገፍና ዚቀተክርስቲያን ተቋማትን መልሶ ለመገንባት ዓለም አቀፍ ዚርዳታ አሰባሳቢ ኮሚ቎ በአስ቞ኳይ እንዲቋቋም ወስኗል።

፱ኛ ዹሚቋቋመው ዓለም አቀፍ ዚርዳታ አሰባሳቢ ኮሚ቎ በተቋም ደሹጃ በማዕኹላዊ ዚቀተክርስቲያናቜን አስተዳደር ዹሚቋቋም ብቻ እንዲሆን ይደሚጋል።ኚዚህ ውጪ በማኅበር፣በግልና በቡድን ዹሚቋቋም ዚርዳታ አሰባሳቢ ኮሚ቎ ፍጹም ተቀባይነት ዹሌለው መሆኑ ታውቆ ድጋፍ ማድሚግ ዹሚፈልጉ ወገኖቜ ሁሉ ዚቀተክርስቲያያቜን ማዕኹላዊ አስተዳደር
በሚያሳውቀው ሕጋዊ አካል ብቻ ድጋፍ እንዲያደርጉና መላው ኊርቶዶክሳዊያን ይህን ዹተቀደሰ ዓላማ ለማሳካት ርብርብ እንዲያደርጉ ጥሪ እያቀሚብን ለዚሁ ዓላማ ዹሚውል ዚባንክ ሒሳብ በአገር ውስጥና በውጪ ሀገራት ዚሚኚፈት ይሆናል።

፲ኛ በቀተክርስቲያናቜን ታሪክም ሆነ በዓለም አቀፍ ደሹጃ ይህን ዹመሰለ ፈተና ገጥሞ በማያውቅበት ጊዜ ኚቀተክርስቲያናቜን ጎን በመቆም ለቀኖናና ለአንድነታቜን መኹበር በጜናት ዚቆማቜሁ ዚእስልምናና ዚኘሮ቎ስታንት ዕምነት ተኚታይ ወንድሞቻቜን ሁሉ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን ሀገር መሆኗን በተግባር በሚያሚጋግጥ ተጋድሎ በሀቅ ኚጎናቜን ስለቆማቜሁ ልባዊ ምስጋናቜንን በቅድስት ቀተክርስቲያናቜን ስም እናቀርብላቜኋለን።

፲ ፩ኛ በዚህ ፈታኝ ወቅት ጉዳት በደሚሰባ቞ው አካባቢዎቜ ዚስብኚተ ወንጌል ስምሪት ተደርጎ ተጎጂዎቜን ዚመጜናናት ፣ዚማስተማርና ዚመጎብኘት ሥራ በአስ቞ኳይ እንዲካሔድ ለዚሀህም አስፈላጊው ዚቅድመ ዝግጅት ሥራ እንዲኚናወን ወስኗል።

፲፪ኛ በዚህ ዚቀተክርስቲያንን መብትናጥቅም በማስኚበር ሒደት ውስጥ ዚመንግስትን ሥልጣን መኚታ በማድሚግ በህገ ወጥ መንገድ ግድያ ዚፈጞሙ፣ዚአካል ጉዳት ያደሚሱ፣ድብደባና ወኚባ ዹፈጾሙ አካላትን ለህግ ተጠያቂነት ማቅሚብ ለነገ ዚማይባል ተግባር በመሆኑ እነዚህን አካላት ለህግ ለማቅሚብ ዹሚደሹገውን ጥሚት በመደገፍ ምዕመናንና ምዕመናት እንዲሁም ወጣት ዚቀተክርስቲያያቜን ልጆቻቜን አስፈላጊውን ድጋፍ እንድተታደርጉ ጥሪአቜንን እያቀሚብን ዚቀተክርስቲያናቜን ዹሕግ አገልግሎት መምሪያና ጠበቆቻቜን ይህን ጉዳይ በልዩ ትኩሚት በመኚታተል ዹህግ ተጠያቂነትን ተግባራዊ እንዲያደርጉ ዚአስተዳደር ጉባኀው ዹወሰነ ሲሆን ውሳኔውም ለቋሚ ሲኖዶስ በመሾኛ እንዲላክ ብሏል።

፲፫ኛ ዹተጀመሹው ዹሰላም ሂደት ፍሬ አፍርቶ ተጚባጭ ውጀት እስኚሚገኝና ሁሉም ነገር ወደ ቊታው እስኚሚመለስ ድሚስ ኊርቶዶክሳዊያን ልቻቜን ሁሉ አስኚ ሁን ድሚስ ስተታደርጉት እንደቆያቜሁት ሁሉ ቀተክርስቲያናቜሁን በጜናት እንድትጠብቁ ጉባኀው አደራ ብሏል።

በመጚሚሻም ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጃቜን በዚህ ክፉ ወቅት በፍፁም ትጋት፣ብቃትን በተተተግባር ባመላኚተው ዚአመራር ቜሎታ቞ው በጥብአት ዚፈጞሙት ተጋድሎን ኚልብ ዹምናደንቅ ሲሆን ለቀጣይ ሥራ቞ው መሳካት ኚብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጃቜን ጎን በመቆም ሌት ተቀን ለመስራት ፍጹም ዝግጁ መሆናቜንን ስናሚጋግጥ በፍጹም ደስታና ትህትና መሆኑን እንገልጻለን በማለት ዚዕለቱን ስብሰባ በጞሎት አጠናቋል።

በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያንና ተወግዘው በተለዩት አባቶቜ መካኚል በሜማግሌዎቜ አማካኝነት ዹተደሹገው ስምምነት ሰነድ።

ኹዚህ በሚት ያልሆኑ ሌሎቜ በጎቜ አሉኝ። እነርሱንም ማምጣት አለብኝ። እነርሱም ድምፄን ይሰማሉ። አንድ መንጋም ይሆናሉ። እሚኛውም አንድ ፀ ዚዮሐንስ ወንጌል 10፣ 16

በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ በተክርስቲያን ተፈጥሮ ዹነበሹው ቜግር ብፁዓን አበው ዚቀተክርስቲያናቜንን ቀኖና መሠሚት አድርገው ባደሚጉት ውይይት ተፈታ።

ምሕሚትና እውነት ተገናኙ ጜቅድቅና ሰላም ተስማሙ – መዝ 855፣10

Odduu Ammee

Warreen Seera Alaan Muudam Ephis Qophoosummaa “muudaman” jedhaman Keessaa tokko kan turan Abbaa Niwaye Sillaasee Akliiluu
Mana Kiristaanaafi Qulqulluu Sinoodoosii dhiifama gaafachuun Deebi’anii jiru.

Breaking News

Aba NewayeSelassie Aklilu, one of the the monks who are said ordinated by the law breaker group returned back to his mother Church.

(ትግርኛ) ሰበር ዜና

. . . በዚ ሎሚ ዕለት ቅዱስ ሲኖዶስ ብዝሠዚሞ አቀራራቢን ናይ ይቅርታ ኮሚ቎ አማካኝነት ብቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ብዝኞፈቶ ናይ ይቅርታን ናይ ምሕሚትን አፍደገ መሠሚት፣ ናብ አደይ ቀተክርስቲያነይን ናይ መንፈስ ቅዱስ አቊታተይን ኚምኡ ውን ናብ ምእመናን ንይቅርታ ዝቀሚብኩ ስለዝኟነ ብመሠሚት ናይ ቋሚ ሲኖዶስን ምልዓተ ጉባኀን ውሳነ ነዚ ይቅርታይ ብአቊነት መንፈስ ንክቅበለኒ ብዓብይ ትሕትና ይሓትት።