የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይቶ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን አስተላለፈ ።

February 16, 2023


**********
የካቲት ፱ቀን ፳ ፻ ፲ወ፭ ዓ.ም
“”””””””””””””””””””””””””
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ

በብፁዕ ከቡነ አብርሃም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና በባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሚመራው የጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር ጉባዔ በወቅታዊ የቤተክርስቲያን ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ የካቲት ፱ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ልዩልዩ ውሳኔዎችን አስተላለፈ።

ጉባኤው በቤተክርስቲያናችን የተደረሰውን ስምምነት አስመልከቶ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የተሰጠውን ሰፊና ጥልቅ ማብራሪያ ካዳመጠ በኋላ በጉዳዩ ዙሪያ ሰፊ ውይይት በማድረግ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል።

፩ኛ በትላንትናው ዕለት በቅዱስ ሲኖዶስና ተወግዘው በተለዩት አባቶች መካከል የተደረሰውን ስምምነት በማድነቅ ተቀብሎታል። ለአፈጻጸሙም የሚጠበቅበትን ሁሉ ለማበረሰከት ቃል ገብቷል።

፪ኛ እርቀ ሰላሙ በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ወክለው ለተወያዩ ብፁዓን አባቶች፣ ተወግዘው ተለይተው ለነበሩ አባቶች ከሁሉም በላይ ለቤተክርስቲያን አንድነት ቅድሚያ በመስጠት ለፈጸሙት ታሪካዊ ስምምነት አድናቆቱንና ምስጋናውን አቅርቧል።

፫ኛ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ቅዱስ ፓትርያርኩ ፣ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የቅድስት ቤተክርስቲያንን ሉአላዊ ክብርና ቀኖናዊ ሥርዓቱን ለማስጠበቅ የከፈሉትን መስዋዕትነት በማድነቅ ስምምነቱ የቤተክርስቲያናችንን መብት ባስከበረ መልኩኩ እንዲፈጸም በማድረጋቸው የተሰማውን ልባዊ ደስታ ከመግለጽ ጋር ስምምነቱን ተከትሎ ለሚከናወነው ተቋማዊ ዕድገት የበኩሉን አስተዋጽኦ ሁሉ በፍጺም ትጋት ለመፈጸም ዝግጁነቱን ገልጿል።።

፬ኛ ክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አህመድ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሀገር ናት በማለት የሚገልጹትን ሀቅ በማጠናከር እርቀ ሰላሙን ተከትሎ “ሙሽራው ክርስቶስ እስከሚመጣበት ድረስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አንድነቷ ተጠብቆ ይኖራል።” በማለት እርቀ ሰላሙ ከልብ እንዲከናወን ያደረጉትን ጥረት በማድነቅ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ልባዊ ምስጋናውን አቅርቧል።

፭ኛ የቤተክርስቲያን ቀኖና አይጣስም አንድነቷ አይናጋም በማለት ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያንን ለማስከበር ክቡር መስዋዕትነት ለከፈላችሁ የዘመኑ ሰማዕታት፣ለዕስርና ለእንግልት የተዳረጋችሁ ኦርቶዶክሳዊያን፣ለግርፋትና ለአካል ጉዳት የተዳረጉ ልጆቻችን ሁሉ ክብርና ምስጋና ይገባቸዋል ያለው ጉባኤው ለሰማዕታት መንግስተ ሰማያትን እንዲያወርስልን፣የአካልና የሥነ አእምሮ ጉዳት ለደረሰባቸው ምሕረትን ለልዑል እግዚአብሔር ይስጥልን ወዳጅ ዘዶቻቸውንም ያጽናናልን፣የታሰሩትንም ያስታልን በማለት የታሰሩ የቤተክርስቲያን ልጆችን ለማስፈታት በሚደረገው ጥረት የሚጠበቅበትን ሁሉ ለማበርከት ቃል ገብቷል።

፮ኛ በዚህ ፈታኝ ወቅት የቤተክርስቲያንን ሉዓላዊነትና ቀኖናዊ አንዴነትን ለማስከበር በተደረገው ተጋድሎ ከቅድስት ቤተክርስቲያን ጎን በጽናት የቆማችሁ በየደረጃው የምትገኙ የአህጉረ ስብከት ሥራ አስኪያጆችና የጽሕፈት ቤት ሰራተኞች፣የቤተክርስቲያን አገልጋዮች፣ ማኅበራት፣ወጣት ልጆቻችን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙሃን ድርጅት፣የቤተክርስቲያናችን የሕዝብ ግንኙት መምሪያ፣የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት በሚዲያው ዘርፍ ለተሰማሩሩ ልዩልዩ የሚዲያ ተቋማት አክቲቪስቶችና ጸሐፊያን ሁሉ ቤተክርስቲያናችን ልባዊ ምስጋናዋን ታቀርባለች።

፯ኛ የቤተክርስቲያናችን ጉዳት ጉዳታችን ነው ከቤተክርስቲያናችን ጎን በጽናት እንቆማለን ፤ችግሩን የቤተክርስቲያንን መብትና ጥቅም በሚያስከብር መልኩ በሰላማዊ መንገድ እንፈታዋለን በማለት ሊገለጽ የማይችል ተጋድሎና እልህ አስጨራሽ ፈተናዎችን በጽናት አልፋችሁ ይህን ዕርቀ ሰላም እውን ያደረጋችሁ የመፍትሔ አፈላላጊና የሽምግልና ሥራ የሰራችሁ ባለሀብቶችና አትሌቶች ልፋታችሁ እንኳን ፍሬ አፍርቶ ለማየት በቃችሁ እንኳንም ደስ አላችሁ። በማለት ልባዊ ምስጋናችን እናቀርብላችኋለን።

፰ኛ በዚህ ፈተና ጊዜ ቤተክርስቲያንን አናስደፍርም፣ የቤተክርስቲያንን ጥሪ ተቀብለን ቤተክርስቲያንን እናስከብራለን በማለት ውድ ሕይወታቸውን በመስዋዕትነት ላቀረቡ ሰማዕታት ቤተሰቦች፣የአካልና የሥነ አእምሮ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖችን ለመደገፍና የቤተክርስቲያን ተቋማትን መልሶ ለመገንባት ዓለም አቀፍ የርዳታ አሰባሳቢ ኮሚቴ በአስቸኳይ እንዲቋቋም ወስኗል።

፱ኛ የሚቋቋመው ዓለም አቀፍ የርዳታ አሰባሳቢ ኮሚቴ በተቋም ደረጃ በማዕከላዊ የቤተክርስቲያናችን አስተዳደር የሚቋቋም ብቻ እንዲሆን ይደረጋል።ከዚህ ውጪ በማኅበር፣በግልና በቡድን የሚቋቋም የርዳታ አሰባሳቢ ኮሚቴ ፍጹም ተቀባይነት የሌለው መሆኑ ታውቆ ድጋፍ ማድረግ የሚፈልጉ ወገኖች ሁሉ የቤተክርስቲያያችን ማዕከላዊ አስተዳደር
በሚያሳውቀው ሕጋዊ አካል ብቻ ድጋፍ እንዲያደርጉና መላው ኦርቶዶክሳዊያን ይህን የተቀደሰ ዓላማ ለማሳካት ርብርብ እንዲያደርጉ ጥሪ እያቀረብን ለዚሁ ዓላማ የሚውል የባንክ ሒሳብ በአገር ውስጥና በውጪ ሀገራት የሚከፈት ይሆናል።

፲ኛ በቤተክርስቲያናችን ታሪክም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ይህን የመሰለ ፈተና ገጥሞ በማያውቅበት ጊዜ ከቤተክርስቲያናችን ጎን በመቆም ለቀኖናና ለአንድነታችን መከበር በጽናት የቆማችሁ የእስልምናና የኘሮቴስታንት ዕምነት ተከታይ ወንድሞቻችን ሁሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሀገር መሆኗን በተግባር በሚያረጋግጥ ተጋድሎ በሀቅ ከጎናችን ስለቆማችሁ ልባዊ ምስጋናችንን በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ስም እናቀርብላችኋለን።

፲ ፩ኛ በዚህ ፈታኝ ወቅት ጉዳት በደረሰባቸው አካባቢዎች የስብከተ ወንጌል ስምሪት ተደርጎ ተጎጂዎችን የመጽናናት ፣የማስተማርና የመጎብኘት ሥራ በአስቸኳይ እንዲካሔድ ለዚሀህም አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ሥራ እንዲከናወን ወስኗል።

፲፪ኛ በዚህ የቤተክርስቲያንን መብትናጥቅም በማስከበር ሒደት ውስጥ የመንግስትን ሥልጣን መከታ በማድረግ በህገ ወጥ መንገድ ግድያ የፈጸሙ፣የአካል ጉዳት ያደረሱ፣ድብደባና ወከባ የፈጸሙ አካላትን ለህግ ተጠያቂነት ማቅረብ ለነገ የማይባል ተግባር በመሆኑ እነዚህን አካላት ለህግ ለማቅረብ የሚደረገውን ጥረት በመደገፍ ምዕመናንና ምዕመናት እንዲሁም ወጣት የቤተክርስቲያያችን ልጆቻችን አስፈላጊውን ድጋፍ እንድተታደርጉ ጥሪአችንን እያቀረብን የቤተክርስቲያናችን የሕግ አገልግሎት መምሪያና ጠበቆቻችን ይህን ጉዳይ በልዩ ትኩረት በመከታተል የህግ ተጠያቂነትን ተግባራዊ እንዲያደርጉ የአስተዳደር ጉባኤው የወሰነ ሲሆን ውሳኔውም ለቋሚ ሲኖዶስ በመሸኛ እንዲላክ ብሏል።

፲፫ኛ የተጀመረው የሰላም ሂደት ፍሬ አፍርቶ ተጨባጭ ውጤት እስከሚገኝና ሁሉም ነገር ወደ ቦታው እስከሚመለስ ድረስ ኦርቶዶክሳዊያን ልቻችን ሁሉ አስከ ሁን ድረስ ስተታደርጉት እንደቆያችሁት ሁሉ ቤተክርስቲያናችሁን በጽናት እንድትጠብቁ ጉባኤው አደራ ብሏል።

በመጨረሻም ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጃችን በዚህ ክፉ ወቅት በፍፁም ትጋት፣ብቃትን በተተተግባር ባመላከተው የአመራር ችሎታቸው በጥብአት የፈጸሙት ተጋድሎን ከልብ የምናደንቅ ሲሆን ለቀጣይ ሥራቸው መሳካት ከብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጃችን ጎን በመቆም ሌት ተቀን ለመስራት ፍጹም ዝግጁ መሆናችንን ስናረጋግጥ በፍጹም ደስታና ትህትና መሆኑን እንገልጻለን በማለት የዕለቱን ስብሰባ በጸሎት አጠናቋል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/favicon.png 169 151 tc https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg tc2023-02-16 12:00:482023-02-16 12:14:08የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይቶ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን አስተላለፈ ።
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንና ተወግዘው በተለዩት አባቶች መካከል በሽማግሌዎች አማካኝነት የተደረገው ስምምነት ሰነድ። Link to: በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንና ተወግዘው በተለዩት አባቶች መካከል በሽማግሌዎች አማካኝነት የተደረገው ስምምነት ሰነድ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንና... Link to: መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ Link to: መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
Scroll to top Scroll to top Scroll to top