የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

አሐዱ ባንክ ላደረገው ሁለተናዊ እገዛ በቋሚ ሲኖዶስ የእውቅናና የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበረከተለት።

July 23, 2026
ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ መመሪያ ሰጪነት በሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አዘጋጅነት ሐምሌ 9 እና 10 ቀናት 2018ዓ.ም ሲካሄድ የቆየው ሀገር አቀፍ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ኀላፊዎች የምክክርና የውይይት መርሐግብር ዘርፈ ብዙ ግንዛቤዎችን በማስጨበጥ የተጠናቀቀ ሲሆን ይህንን የሥልጠና መርሐ ግብር ሙሉ ወጪ በመሸፈን አስተዋጽኦ ላደረገው ለአሃዱ ባንክ አክሲዮን ማኅበር እና መምሪያውን በዘመናዊ መልኩ በማደራጀት ትብብር ላደረጉ አካላት እንዲሁም ባለፉት አራት ዓመታት በተለያዩ የሥልጠና መርሐ ግብሮች ላይ ለተሳተፉ ምሁራን የቤተክርስቲያን ልጆች በዛሬው እለት የምስጋና ምስክር ወረቀት ስጦታ ከቅዱስ ፓትርያርኩ እጅ ተበርክቶላቸዋል።
በመርሐ_ግብሩ የመግቢያ ንግግር ያደረጉት የመምሪያው ዋና ኀላፊ ሊቀ ሥዩማን እስክንድር ገብረክርስቶስ ቤተክርስቲያን
ቴክኖሎጂ የታጠቀ፣ሀቀኝነትን መሰረት ያደረገ፣ተቋም ተኮር የሆነ የሕዝብ ግንኙነት ሥራን ለመሥራት የሚያስችል ግንዛቤ ማስጨበጥን ዓላማው ያደረገው ሥልጠና በቅርቡ መሰጠቱን አስታውሰዎ የሥልጠናውን ወጪ እንዲሸፍን ለአሐዱ ባንክ የቀረበው ጥሪ ባንኩ አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ሥልጠናውን በስኬት እንድናከናውን ስላደረገን በቅዱስነትዎና በቋሚ ሲኖዶስ ፊት ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል።
በመቀጠልም ሕዝብ ግንኙነት ለአራት ተከታታይ ዓመታት በሚያደርጋቸው ስልጠናዎች እውቀታቸውንና ጊዜያቸውን ሳይሰስቱ የመምሪያው አጋር በመሆኑ ያገዙ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በዚሁ እለት እውቅና የምስክር ወረቀት እንዲሰጣቸው የተደረገው ቀጣዩን ሥራችንን ስኬታማ ለማድረግ ስለሆነ ላበረከታችሁልን አስተዋጽኦ ሁሉ ምስጋናችን ይድረሳችሁ ብለዋል።
በዚሁ ጊዜ ብፀዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት የሰማነው ሁሉ ለቤተክርስቲያን የሚጠቅም ሥራ ነው። ቤተክርስቲያን የሁላችንም ስለሆነች ቤተክርስቲያንን መርዳት የሁላችንም ግዴታ ነው ። በቤተክርስቲያን ላይ የሚነሱ አጸያፊ ስም ማጥፋቶችን ለመከላከልም ይሁን የቤተክርስቲያን ትክክለኛ አንደበት ለመሆን የተሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ እጅግ ደስ የሚል ነውና ለቤተክርስቲያን የሚጠቅም ስለሆነ ለሥልጠናው ስኬት ድጋፍ ላደረጋችሁ ሁሉ እግዚአብሔር ይስጥልን ብለዋል።
ከቅዱስነታቸው መልዕክት ቀደም ብሎ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ የመምሪያውን ዋና ኀላፊ በማመስገን ጀምረው በውይይቱ መርሐግብሩ ቤተክርስቲያን ሊያስከብር የሚችል ምክክር እንደተደረገ ምስክርነታቸውን ሰጥተው በቀጣይም በቤቶችና ሕንጻዎችም ይሁን በሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የሚታየው ለውጥ እንዲቀጥል አባታዊ መመሪያ ሰጥተዋል።
በመጨረሻም የአሐዱ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ “ከብዙኃን ለብዙኃን” በሚለው ሥራችን መሠረት ቤተክርስቲያን ለምታደርገው ማንኛውም ልማት እገዛ ማድረግ ተቀዳሚ ተግባራችን ነው ብለዋል።(ፎቶ Eotc tv)
Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/pr000048.jpeg 299 448 eotceth https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg eotceth2026-07-23 10:52:132026-07-23 10:52:13አሐዱ ባንክ ላደረገው ሁለተናዊ እገዛ በቋሚ ሲኖዶስ የእውቅናና የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበረከተለት።
Search Search

Recent Posts

  • የድሬዳዋ ሳባ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ያስገኘባው ባለ ሦስት ወለል ሁለገብ ሕንጻ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና በብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጸሎተ ቡራኬ በዛሬው ዕለት ተመረቋል።
  • የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ሕንጻ ቤተክርስቲያን ዕድሳት ተጠናቆ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው ተባረከ።
  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ ወደ ቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ተጓዘ።
  • አሐዱ ባንክ ላደረገው ሁለተናዊ እገዛ በቋሚ ሲኖዶስ የእውቅናና የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበረከተለት።
  • የመቱ ፈለገ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ የመጀመሪያውን ዙር እጩ መምህራን በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስመረቀ

Archives

  • July 2026
  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የመቱ ፈለገ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ የመጀመሪያውን ዙር እጩ መምህራን በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስመረቀ Link to: የመቱ ፈለገ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ የመጀመሪያውን ዙር እጩ መምህራን በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስመረቀ የመቱ ፈለገ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ የመጀመሪያውን... Link to: በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ ወደ ቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ተጓዘ። Link to: በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ ወደ ቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ተጓዘ። በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሚመራ የቤተክርስቲያናችን...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top