በኮቸሬ ገደብና ጮርሶ ወረዳ ቤተክህነት የሰንበት ት/ቤት አንድነት ተመሠረተ!!!

የሀገረ ስብከቱ የስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ ሊቀትጉሃን ቀሲስ ሀብታሙ አበበ  ከፊት ይልቅ ትጉ!! በ፪ኛ ጴጥ ፪:፲ ያለውን አምላካዊ ቃል መነሻ በማድረግ የሰንበት ት/ቤት አባላት መጠራታቸውን መመረጣቸውን በመመልከት ከበፊት ይልቅ መትጋትና የቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት በመጠበቅና በማስጠበቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ በሰፊው አስተምረዋል።

የቤተክርስቲያን ተወካዮች በግብፁ ጉባኤ ላይ ያልተገኙት በግል በገጠማቸው እክል ምክንያት መሆኑን የውጭ ግንኙነቱ መምሪያ አስታወቀ።

መስከረም ፲ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም
“””””””””””””””””””””””””””””””””””””””””
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ
*****
መስከረም 6 እና 7/2017 ዓመተ ምሕረት በግብፅ አል ናትሩ አባ ቢሾይ ገዳም በኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አስተናጋጅነት በተካሄደው የአኃት እና የምሥራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያን የነገረ መለኮት ውይይት ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተወካዮች ያልተገኙት በግል በገጠማቸው እክል ምክንያት ሲሆን ተተኪ ልዑክ ለመላክ እስከ መስከረም 3 ቀን 2017 ዓመተ ምሕረት ድረስ የተደረገው ጥረት ቪዛን ጨምሮ አስፈላጊውን የጉዞ ሰነዶች ለማሟላት ከሚያስፈልገው ጊዜ ያጠረ በመሆኑ ሊሳካ አልቻለም።

ከብፁዕ ወቅዱስ ታዎድሮስ 2ኛ የግብፅ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ በተጻፈ ደብዳቤ የተጋበዘችው ቤተ ክርስተያናችን የግብዣ ጥሪው እንደደረሳት ከመርሐ ግብሩ ሁለት ወራት አስቀድሞ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት አመራር ሰጪነት በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 28 ንዑስ አንቀጽ 5 በተደነገገው መሠረት በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት የበላይ ሓላፊ እና የምሥራቅ አፍሪካ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ እንዲሁም ፕሮፌሰር አባ ኃይለ ገብርኤል ግርማ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ም/ ፕሬዚዳንት ቤተክርስቲያናችንን ወክለው እንዲገኙ ተመድበው የነበረ ቢሆንም ልዑካኑ በገጠማቸው እክል ምክንያት በጊዜው ሊገኙ እንዳልቻሉ ከውጭ ግንኙነት መምሪያ ባገኘነው መረጃ ለማረጋገጥ ችለናል።

የኢሉ አባ ቦር ሀገረ ስብከት ሲሰጥ የነበረውን የአሰልጣኞች ስልጠና አጠናቀቀ

መስከረም 9/2016 ዓ. ም

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የ10 ዓመቱን ስልታዊ ዕቅድ አውጥታ ወደ ሥራ ገብታለች። በዚህ መሠረት የኢሉ አባ ቦር ሀገረ ስብከት የ10 ዓመቱን መሪ ዕቅድ እስከታችኛው መዋቅር እንዲወርድ በማሰብ በ14ቱም ወረዳዎች ለሚገኙ የ270 አብያተክርስቲያናት የደብር አስተዳዳሪዎች ፣የሰበካ ጉባኤ አባላት ፣የሰንበት ትምህርት ቤት እና የማኅበራት ተወካዮች የሚገኙበት ስልጠና የፊታችን መስከረም 18 እና 19 ለመስጠት ዝግጅት ላይ ይገኛል።

ታዲያ ይህንን ስልጠና ለሚሰጡ ምሁራንና የሀገረ ስብከቱ የየክፍል ኃላፊዎች ላለፉት ሁለት ቀናት ስልጠና ሲሰጥ ቆይቷል። በዚህ ስልጠና ቤተክርስቲያን ያለችበትን ደረጃ ለማወቅ የተጠናው ጥልቅ ጥናት ውጤት ተደራጅቶ ለውይይት የቀረበ ሲሆን ችግሮቻችን ሊፈቱ በሚያስችል ቁመና የ10 ዓመቱ መሪ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ለሰልጣኞች ተሰጥቷል።

ስልጠናውን የአሰልጣኞች ስልጠና ሲሆን የፊታችን መስከረም 18-19/2016 ዓ. ም በሁሉም ወረዳ የሚሰጠውን የአድባራት አመራር ስልጠና ለሚሰጡ ባለሙያዎችና የሀገረ ስብከቱ አመራር የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።

በዚህ ስልጠና 270 የድባራት አስተዳዳሪዎች 1,890 የሰበካ ጉባኤ አባላት፣540 የሰንበት ትምህርት ቤት ተወካዮች 724 ካህናትና ከ200 በላይ የማኅበራት ተወካዮች የሚገኙበት ሲሆን በድምሩ ከ3,624 ሰዎች የሚሳተፉበት ይሆናል።

በመርሐ ግብሩ ማጠቃላያ ላይ ንግግር ያደረጉና ስልጠናውን ላለፉት ሁለት ቀናት ሲመሩ የነበሩ የኢሉ አባ ቦር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባልና የመቱ ፈለገ ሕይወት መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ዶ/ር እንደተናገሩ ቤተክርስቲያናችን ከገባችበት ፈተና እንድትወጣ ከተፈለገ በዕቅድ መመራት ዋና መፍትሄ ሲሆን የታቀደው ዕቅድ በታቀደበት መንገድ እንዲፈጸም ከተፈለገደግሞ በሁሉም የቤተክርስቲያን መዋቅር ደረጃ የአፈጻጸም ሂደቱን መገምገምና መከታተል ቁልፍ ተግባር ሆኖ መቀጠል አለበት ብለዋል።

ብፁዕነታቸው አያይዘው እንደገለጹት ባለፉት ሁለት ቀናት ሀገረ ስብከቱ ያዘጋጀውን ስልጠና የወሰዳችሁ የቤተክርስቲያን ልጆች ተቋሙ ያወጣውን የ10 ዓመት መርህ ዕቅድ ለቤተክርስቲያን ሁለንተናዊ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን ተረድታችሁ ሕዝባችንን እንድታስገነዝቡልን አደራችን ጥልቅ ነው ብለዋል።

በስልጠናው ላይ የተገኙት ሰለሰጣኞች እንደተናገሩት ሀገረ ስብከቱ በዚህ መልክ የ10 ዓመት ስልታዊ ዕቅድ አውጥቶ በዚያ ለመመራት መወሰኑ ተስፋ ሰጭ ነው ብለው የሚመለከተው የቤተክርስቲያን አመራርና መላው በሀገረ ስብከቱ ውስጥ የሚገኙ ማኅበረ ካህናትና ማኅበረ ምዕመናን ለእቅዱ ተፈጻሚነት ሊሰለፉ ይገባል ብለዋል።

የዜናው ምንጭ የኢሉ አባ ቦር ሀገረ ስብከት ሕዝብ ግንኙነት ነው።

በሲዳማ ሀገረ ስብከት ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በጠቅላይ ቤተ ክህነት የወጣውን የማኅበራት አስተዳደር ደንብ አስመለክቶ የምዝገባ ጥያቄ ላቀረቡ አሥራ ሁለት ማኅበራት ስልጠና ተሰጠ።

መስከረም 9/2017 ዓ/ም

በምሥራቅ ሐረርጌ ሀ/ስብከት በመንበረ ጵጵስና ጌቴሴማኔ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም መንበረ ጵጵስና አዳራሽ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ልዑካን የደብል ኢንትሪ የሒሳብ አያያዝ የግማሽ ቀን ሥልጠና እየተከናወነ ይገኛል።

መስከረም ፱ ፳፻፲፯ ዓ.ም
ምሥራቅ ሐረርጌ ፣ ኢትዮጵያ

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅሊይ ቤተክነት አስተዳደር ጉባኤ በአዱስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን የሚያጠኑ ፯ አባላት ያሉት ኮሚቴ ሰየመ፡፡

መስከረም ፱ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም
******
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
==============

በሀገረ ስብከቱ የሚስተዋለው ግብረ ሙስና በሚሊየኖች በሚቆጠር ገንዘብ የሚፈጸም መሆኑን በመጥቀስ በዋዜማ ሬዱዮና በሌሎችም የሚዲያ ተቋማት የተዘገበውን ዘገባ በተመለከተ የሀገረ ስብከቱ የህዝብ ግንኙነት ክፍልና የሥራ ኃላፊዎች ጋዜጣዊ መግለጫ በመስጠት ለማስተባበል መሞከራቸው ይታወሳል፡፡

ይሁንና በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ሀገረ ስብከቱ ከቅጥርና ዝውውር ጋር በተያያዘ በሕግና በመመሪያ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጋር በመናበብ እየሰራ መሆኑን በመግለጽ ያስተላለፈው መግለጫ ፍጹም ሐሰት ከመሆኑም በላይ በተደጋጋሚ በሀገረ ስብከቱ በኩል የሚስተዋለው የመልካም አስተዲደር ችግር በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ በተላለፈው መመሪያ መሠረት እንዲፈታና ቅሬታ ለሚያቀርቡ ወገኖችም ይህን መሠረት በማድረግ ፍትሕ እንዱሰጥ በጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር ጉባኤ ተወስኖ በተደጋጋሚ የተላለፈውን መመሪያ አለመፈጸሙ ጉባኤውን አሳዝኗል።

ስለሆነም በሀገረ ስብከቱ የሚስተዋለው የመልካም አስተዳደር ችግር በፍጹም ቆራጥነትና ተጋድሎ የሚታረምበትና ቤተክርቲያንና አገልጋይ ካህናት እፎይታ የሚያገኙበት ሁኔታ መፍጠር ይቻል ዘንድ ችግሩን በዝርዝር በማጥናት ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር የሚያቀርቡ ፯ (ሰባት) አባላት ያሉት ኮሚቴ እንዱሰየሰሙ አድርጓል፡፡

ችግሩን ለመፍታት የሚደረገው እልህ አስጨራሽ ተጋድሎም ፍጹም ቆራጥነትን የሚጠይቅ በመሆኑ ችግሩ ከስሩ ተፈቶ የቤተክርቲያን ክብር ተመልሶና የካህናት እንባ ታብሶ ቀጣይነት ያለው በህግ የሚመራና የቤተክርስቲያናችንን ቅድስና የሚመጥን አሠራር ተዘርግቶ መፈጸም እስከሚችል ድረስ በቆራጥነት ለመሥራት ጉባኤው በአንድ ድምጽ በመወሰን ዝርዝር ሁኔታውን በማጥናት ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር እንዲያቀርቡ፦

፩. መ/ሰ ቆሞስ አባ ቃለጽድቅ ሙሉጌታ(ዶ/ር) ከጠቅላይ ቤተክህነት፤
፪.ሊቀ መዘምራን ሐረገወይን ጫኔ ከጠቅላይ ቤተክህነት፤
፫.ሊቀ ስዩማን እስክንድር ገብረክርስቶስ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት፤
፬.ዲ/ን ሙሉቀን ትዕዛዙ(ከምዕመናን)
፭.ዲ/ን ዘለዓለም ሲሳይ(ከምዕመናን)
፮.ዲ/ን ዘካርያስ ወዳጆ(ከህግ ቋሚ ኮሚቴ)
፯.ዲ/ን ስንታየሁ ምስጋናውን ከሰንበት ትምህርት
ቤቶች አንድነት በመመደብ የእለቱን ስብሰባ በጸሎት አጠናቋል።

በአዲሱ ዓመት ቅድስት ቤተክርስቲያን ትኩረት ሰጥታ መሥራት ያለባትን ጉዳዮች ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል ሊቀጳጳስ አስታወቁ።

በአዲሱ ዓመት ቅድስት ቤተክርስቲያን ትኩረት ሰጥታ መሥራት ያለባትን ጉዳዮች ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል ሊቀጳጳስ አስታወቁ።
“””””””””””””
1. ሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ በመልዕክቱ “ጌታ ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያን እናደርጋለን ማለት ይገባችኋል።” (ያዕ 4÷15) እንዳለው
ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነትን ጀምሮ በመላው ዓለም ባሉት አደረጃጀቶች ዘንድ ዘላቂነት እና ወጥነት ባለው መልኩ ዘመኑን የዋጀ ተቋማዊ አሠራር አገልግሎቱን ለማሳለጥ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በረጅም እና በአጭር ጊዜያት የሚተገበሩ የአገልግሎት አቅጣጫዎችን፣ አጠቃላይ የመሪ ዕቅድ ስልቶችን እና መርሐ ግብሮችን በየደረጃው ያለው የቤተክርስቲያን መዋቅር መፈጸም ይጠበቅበታል፤

2. የቅድስት ቤተክርስቲያን አንድነት እየተፈታተነ ያለ ክፍፍል በተለይም በኦሮሚያ እና በትግራይ የታየውን ወደ አንድነት ማምጣትና በዕርቅ፤ በሰላም እና በስምምነት መፈጸም ይገባናል፤ ይህንንም ለመፈጸም የፌዴራልም ሆነ የክልል መንግስታት ከቅድስት ቤተክርስቲያን ጎን ሆነው ሕግ የማስከበር ሥራ እንዲሠሩ አበክረን መሥራት ያስፈልገናል፤

3. በመንፈሳዊ ማኅበራት የሚሠሩ ሥራዎች ፤ በሰ/ት/ቤት ለአዳጊዎች እና ለወጣቶች የሚሰጧቸው ሁለገብ አገልግሎቶች በዓለማችን ላይ በየጊዜው የሚከሰተቱን መልካም ዕድሎች እና ፈተናዎች እንዲሁም በየአህጉረ ስብከቱ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ከክርስቲያናዊ ዕሴቶች ጋር ባገናዘበ መልኩ እንዲተገበሩ በመንፈሳዊ ጥበብ የተቃኙ ቀልጣፋ የአፈጻጸም ስልቶችን በመከተል መሥራት አለብን፤

4. ሕገ-ወጥ አጥማቂያንን እንዲሁም በየቦታው ያለቅድስት ቤተክርስቲያን ፈቃድና ዕውቅና በመንቀሳቀስ ዶግማዋን ቀኖናዋን እና ሥርዓቷን የሚጥሱ ግጭት የሚቀሰቅሱትን የተደራጁ ኃይሎችን እና ግለሰቦችን ሥርዓት ማስያዝ፤ በተጨማሪም በዓመቱ በርካታ ፓስተሮች እየተጠመቁ ከተከታዮቻቸው ጋር ወደ ቅድስት ቤተክርስቲያን ስለተመለሱ ማጽናትና መንከባከብ አለብን፤

5. የመሪ ዕቅዱን አፈጻጸም ባለው ሂደት ውስጥም በመላው ዓለም ከመንበረ ፓትርያርክ ጀምሮ እስከ አጥቢያ ሰ/ጉ/ቤት ድረስ በተዘረጋው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መዋቅራዊ አደረጃጀት ውስጥ በአንዲት ቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር ተሰባስበው ለአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ተልእኮ እና ራእይ መሳካት ሁለገብ እና ጉልህ ሚና የሚጫወቱ አገልጋዮችን ማበረታታትና ማሳደግ በአዲሱ ዓመት የቅድስት ቤተክርስቲያን የትኩረት አቅጣጫ መሆን ይገባል ብዬ አምናለሁ ሲሉ ብፁዕነታቸው ተናግረዋል።

መስከረም 06 ቀን 2017 ዓ/ም
አሶሳ፤

የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ እያካሔደ ይገኛል።

መስከረም 6 ቀን 2017 ዓ.ም

የሲዳማ ሀገረ ስብከት ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ለብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የታቦር ፍኖተ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የእንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር አካሄደ።

መስከረም 5/2017 ዓ/ም

በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት በብፁዕ አቡነ በርተሎሜዎስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የተመራ የመስቀልና ደመራን በዓል አስመልክቶ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመንበረ ጵጵስና አዳራሽ ስብሰባ ተካሄደ።

መስከረም ፬/፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም