በኼቾሬ ገደቄና áŒźáˆ­áˆ¶ ወሹዳ ቀተክህነቔ ዚሰንበቔ ቔ/ቀቔ አንዔነቔ ተመሠሹተ!!!

ዹሀገሹ ሔቄኚቱ ዚሔቄኚተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ ሊቀቔጉሃን ቀáˆČሔ áˆ€á‰„á‰łáˆ™ አበበ  ኚፊቔ ይልቅ ቔጉ!! በáȘኛ ጎጄ áȘ:áČ ያለውን አምላካዊ ቃል መነሻ በማዔሚግ ዚሰንበቔ ቔ/ቀቔ áŠ á‰Łáˆ‹á‰” áˆ˜áŒ áˆ«á‰łá‰žá‹áŠ• መመሹጣቾውን በመመልኚቔ ኚበፊቔ ይልቅ መቔጋቔና ዚቅዔሔቔ ቀተክርሔá‰Čያን ሄርዓቔ በመጠበቅና በማሔጠበቅ ኃላፊነታቾውን ኄንá‹Čወጡ በሰፊው áŠ áˆ”á‰°áˆáˆšá‹‹áˆáą

ዚቀተክርሔá‰Čያን á‰°á‹ˆáŠ«á‹źá‰œ በግቄፁ áŒ‰á‰ŁáŠ€ ላይ ያልተገኙቔ በግል በገጠማቾው ኄክል ምክንያቔ መሆኑን ዹውጭ ግንኙነቱ መምáˆȘያ áŠ áˆ”á‰łá‹ˆá‰€áą

መሔኚሚም áČ ቀን áłá» áČወ፯ ዓ.ም
“””””””””””””””””””””””””””””””””””””””””
አá‹Čሔ አበባ-áŠąá‰”á‹źáŒ”á‹«
*****
መሔኚሚም 6 ኄና 7/2017 ዓመተ ምሕሚቔ በግቄፅ አል ናቔሩ አባ á‰ąáˆŸá‹­ ገዳም በኼፕá‰Čክ ኊርቶዶክሔ ቀተ ክርሔá‰Čያን አሔተናጋጅነቔ በተካሄደው ዚአኃቔ ኄና ዚምሄራቅ ኊርቶዶክሔ አቄያተ ክርሔá‰Čያን ዹነገሹ áˆ˜áˆˆáŠźá‰” ውይይቔ ላይ á‹šáŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« ኊርቶዶክሔ ተዋሕዶ ቀተ ክርሔá‰Čያን á‰°á‹ˆáŠ«á‹źá‰œ ያልተገኙቔ በግል በገጠማቾው ኄክል ምክንያቔ áˆČሆን ተተáŠȘ ልዑክ ለመላክ ኄሔኚ መሔኚሚም 3 ቀን 2017 ዓመተ ምሕሚቔ ዔሚሔ ዹተደሹገው ጄሚቔ á‰Șዛን ጹምሼ አሔፈላጊውን ዹጉዞ ሰነዶቜ ለማሟላቔ ኚሚያሔፈልገው ጊዜ ያጠሚ በመሆኑ áˆŠáˆłáŠ« áŠ áˆá‰»áˆˆáˆáą

ኚቄፁዕ ወቅዱሔ á‰łá‹Žá‹”áˆźáˆ” 2ኛ ዚግቄፅ ኼፕá‰Čክ ኊርቶዶክሔ ቀተ ክርሔá‰Čያን ፓቔርያርክ በተጻፈ ደቄዳቀ ዚተጋበዘቜው ቀተ ክርሔተያናቜን á‹šáŒá‰„á‹Ł ጄáˆȘው áŠ„áŠ•á‹°á‹°áˆšáˆłá‰” ኹመርሐ ግቄሩ ሁለቔ ወራቔ አሔቀዔሞ በቄፁዕ ወቅዱሔ አቡነ ማቔያሔ ቀዳማዊ ፓቔርያርክ ርኄሰ ሊቃነ áŒłáŒłáˆłá‰” á‹˜áŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« ሊቀ áŒłáŒłáˆ” ዘአኔሔም ወዕጹጌ ዘመንበሹ ተክለሃይማኖቔ አመራር ሰáŒȘነቔ በሕገ ቀተ ክርሔá‰Čያን አንቀጜ 28 ንዑሔ አንቀጜ 5 በተደነገገው መሠሚቔ በቋሚ áˆČኖዶሔ ውሳኔ ቄፁዕ አቡነ ማ቎ዎሔ á‹šáŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« ኊርቶዶክሔ ተዋሕዶ ቀተ ክርሔá‰Čያን መገናኛ ቄዙኃን አገልግሎቔ ሄርጭቔ ዔርጅቔ ዹበላይ ሓላፊ ኄና ዚምሄራቅ አፍáˆȘካ አህጉሹ ሔቄኚቔ ሊቀ áŒłáŒłáˆ”á€ ኄንá‹Čሁም ፕሼፌሰር አባ ኃይለ ገቄርኀል ግርማ ዚቅዔሔቔ ሄላሎ መንፈሳዊ ዩኒቚርáˆČá‰Č á‹šáŠ áŠ«á‹łáˆšáŠ­ ም/ á•áˆŹá‹šá‹łáŠ•á‰” ቀተክርሔá‰Čያናቜንን ወክለው ኄንá‹Čገኙ ተመዔበው ዹነበሹ ቱሆንም ልዑካኑ በገጠማቾው ኄክል ምክንያቔ በጊዜው ሊገኙ áŠ„áŠ•á‹łáˆá‰»áˆ‰ ኹውጭ ግንኙነቔ መምáˆȘያ ባገኘነው መሹጃ ለማሚጋገጄ á‰œáˆˆáŠ“áˆáą

ዹ኱ሉ አባ ቩር ሀገሹ ሔቄኚቔ áˆČሰጄ ዹነበሹውን á‹šáŠ áˆ°áˆáŒŁáŠžá‰œ ሔልጠና አጠናቀቀ

መሔኚሚም 9/2016 ዓ. ም

á‹šáŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« ኊርቶዶክሔ ተዋህዶ ቀተክርሔá‰Čያን ዹ10 ዓመቱን áˆ”áˆá‰łá‹Š ዕቅዔ áŠ á‹áŒ„á‰ł ወደ ሄራ áŒˆá‰„á‰łáˆˆá‰œáą በዚህ መሠሚቔ ዹ኱ሉ አባ ቩር ሀገሹ ሔቄኚቔ ዹ10 ዓመቱን መáˆȘ ዕቅዔ áŠ„áˆ”áŠšá‰łá‰œáŠ›á‹ መዋቅር ኄንá‹Čወርዔ በማሰቄ በ14ቱም á‹ˆáˆšá‹łá‹Žá‰œ ለሚገኙ ዹ270 አቄያተክርሔá‰Čያናቔ ዚደቄር áŠ áˆ”á‰°á‹łá‹łáˆȘዎቜ áŁá‹šáˆ°á‰ áŠ« áŒ‰á‰ŁáŠ€ áŠ á‰Łáˆ‹á‰” áŁá‹šáˆ°áŠ•á‰ á‰” ቔምህርቔ ቀቔ ኄና ዚማኅበራቔ á‰°á‹ˆáŠ«á‹źá‰œ ዚሚገኙበቔ ሔልጠና á‹šáŠá‰łá‰œáŠ• መሔኚሚም 18 ኄና 19 ለመሔጠቔ ዝግጅቔ ላይ ይገኛል፱

ታá‹Čያ ይህንን ሔልጠና ለሚሰጡ ምሁራንና ዹሀገሹ ሔቄኚቱ ዹዹክፍል ኃላፊዎቜ ላለፉቔ ሁለቔ ቀናቔ ሔልጠና áˆČሰጄ á‰†á‹­á‰·áˆáą በዚህ ሔልጠና ቀተክርሔá‰Čያን ያለቜበቔን ደሹጃ ለማወቅ ዹተጠናው ጄልቅ ጄናቔ ውጀቔ ተደራጅቶ ለውይይቔ ዹቀሹበ áˆČሆን á‰œáŒáˆźá‰»á‰œáŠ• ሊፈቱ በሚያሔቜል ቁመና ዹ10 ዓመቱ መáˆȘ ዕቅዔ ተዘጋጅቶ áˆˆáˆ°áˆáŒŁáŠžá‰œ á‰°áˆ°áŒ„á‰·áˆáą

ሔልጠናውን á‹šáŠ áˆ°áˆáŒŁáŠžá‰œ ሔልጠና áˆČሆን á‹šáŠá‰łá‰œáŠ• መሔኚሚም 18-19/2016 ዓ. ም በሁሉም ወሹዳ ዹሚሰጠውን á‹šáŠ á‹”á‰Łáˆ«á‰” አመራር ሔልጠና ለሚሰጡ á‰Łáˆˆáˆ™á‹«á‹Žá‰œáŠ“ ዹሀገሹ ሔቄኚቱ አመራር ዹተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል፱

በዚህ ሔልጠና 270 á‹šá‹”á‰Łáˆ«á‰” áŠ áˆ”á‰°á‹łá‹łáˆȘዎቜ 1,890 ዚሰበካ áŒ‰á‰ŁáŠ€ áŠ á‰Łáˆ‹á‰”áŁ540 ዚሰንበቔ ቔምህርቔ ቀቔ á‰°á‹ˆáŠ«á‹źá‰œ 724 ካህናቔና ኹ200 በላይ ዚማኅበራቔ á‰°á‹ˆáŠ«á‹źá‰œ ዚሚገኙበቔ áˆČሆን በዔምሩ ኹ3,624 ሰዎቜ á‹šáˆšáˆłá‰°á‰á‰ á‰” ይሆናል፱

በመርሐ ግቄሩ ማጠቃላያ ላይ ንግግር ያደሚጉና ሔልጠናውን ላለፉቔ ሁለቔ ቀናቔ áˆČመሩ ዚነበሩ ዹ኱ሉ አባ ቩር ሀገሹ ሔቄኚቔ ሊቀ áŒłáŒłáˆ” ዚቅዱሔ áˆČኖዶሔ አባልና ዚመቱ ፈለገ ሕይወቔ መንፈሳዊ ኼሌጅ ዹበላይ ጠባቂ ሊቀ áŒłáŒłáˆ” ቄፁዕ አቡነ áŠ€á‹Žáˆ”áŒŁá‰Žá‹Žáˆ” ዶ/ር ኄንደተናገሩ ቀተክርሔá‰Čያናቜን áŠšáŒˆá‰Łá‰œá‰ á‰” ፈተና áŠ„áŠ•á‹”á‰”á‹ˆáŒŁ ኹተፈለገ በዕቅዔ መመራቔ ዋና መፍቔሄ áˆČሆን ዹታቀደው ዕቅዔ በታቀደበቔ መንገዔ ኄንá‹Čፈጾም ኹተፈለገደግሞ በሁሉም ዚቀተክርሔá‰Čያን መዋቅር ደሹጃ ዚአፈጻጞም ሂደቱን መገምገምና መኹታተል ቁልፍ ተግባር ሆኖ መቀጠል አለበቔ á‰„áˆˆá‹‹áˆáą

á‰„áá‹•áŠá‰łá‰žá‹ አያይዘው ኄንደገለáŒčቔ á‰Łáˆˆá‰á‰” ሁለቔ ቀናቔ ሀገሹ ሔቄኚቱ ያዘጋጀውን ሔልጠና á‹šá‹ˆáˆ°á‹łá‰œáˆ ዚቀተክርሔá‰Čያን ልጆቜ ተቋሙ á‹«á‹ˆáŒŁá‹áŠ• ዹ10 ዓመቔ መርህ ዕቅዔ ለቀተክርሔá‰Čያን ሁለንተናዊ ዕዔገቔ ወሳኝ መሆኑን á‰°áˆšá‹”á‰łá‰œáˆ áˆ•á‹á‰Łá‰œáŠ•áŠ• áŠ„áŠ•á‹”á‰łáˆ”áŒˆáŠá‹á‰ĄáˆáŠ• አደራቜን ጄልቅ ነው á‰„áˆˆá‹‹áˆáą

በሔልጠናው ላይ ዚተገኙቔ áˆ°áˆˆáˆ°áŒŁáŠžá‰œ ኄንደተናገሩቔ ሀገሹ ሔቄኚቱ በዚህ መልክ ዹ10 ዓመቔ áˆ”áˆá‰łá‹Š ዕቅዔ አውጄቶ በዚያ ለመመራቔ መወሰኑ ተሔፋ ሰጭ ነው ቄለው ዹሚመለኹተው ዚቀተክርሔá‰Čያን አመራርና መላው በሀገሹ ሔቄኚቱ ውሔጄ ዹሚገኙ ማኅበሹ ካህናቔና ማኅበሹ ምዕመናን ለኄቅዱ ተፈጻሚነቔ ሊሰለፉ ይገባል á‰„áˆˆá‹‹áˆáą

ዹዜናው ምንጭ ዹ኱ሉ አባ ቩር ሀገሹ ሔቄኚቔ ሕዝቄ ግንኙነቔ ነው፱

በáˆČዳማ ሀገሹ ሔቄኚቔ ቀተ ክህነቔ ጜ/ቀቔ በጠቅላይ ቀተ ክህነቔ ዹወጣውን ዚማኅበራቔ áŠ áˆ”á‰°á‹łá‹°áˆ­ ደንቄ አሔመለክቶ ዹምዝገባ ጄያቄ ላቀሹቡ አሄራ ሁለቔ ማኅበራቔ ሔልጠና ተሰጠ፱

መሔኚሚም 9/2017 ዓ/ም

በምሄራቅ ሐሹርጌ ሀ/ሔቄኚቔ በመንበሹ ጔጔሔና ጌቮሮማኔ ቅዔሔቔ áŠȘዳነ ምሕሚቔ ገዳም መንበሹ ጔጔሔና áŠ á‹łáˆ«áˆœ በመንበሹ ፓቔርያርክ ጠቅላይ ቀተ ክህነቔ ጜ/ቀቔ ልዑካን ዚደቄል ኹንቔáˆȘ á‹šáˆ’áˆłá‰„ አያያዝ ዚግማሜ ቀን ሄልጠና ኄዚተኚናወነ ይገኛል፱

መሔኚሚም ፱ áłá»áČ፯ ዓ.ም
ምሄራቅ ሐሹርጌ ፣ áŠąá‰”á‹źáŒ”á‹«

ዹመንበሹ ፓቔርያርክ ጠቅሊይ ቀተክነቔ áŠ áˆ”á‰°á‹łá‹°áˆ­ áŒ‰á‰ŁáŠ€ በአዱሔ አበባ ሀገሹ ሔቄኚቔ á‹šáˆšá‰łá‹© ዚመልካም áŠ áˆ”á‰°á‹łá‹°áˆ­ á‰œáŒáˆźá‰œáŠ• ዚሚያጠኑ ፯ áŠ á‰Łáˆ‹á‰” ያሉቔ ኼሚቮ ሰዹመ፡፡

መሔኚሚም ፱ ቀን áłá» áČወ፯ ዓ.ም
******
አá‹Čáˆ”áŠ á‰ á‰Ł -áŠąá‰”á‹źáŒ”á‹«
==============

በሀገሹ ሔቄኚቱ ዚሚሔተዋለው ግቄሚ ሙሔና በሚሊዚኖቜ በሚቆጠር ገንዘቄ ዹሚፈጾም መሆኑን በመጄቀሔ በዋዜማ áˆŹá‹±á‹źáŠ“ በሌሎቜም ዹሚá‹Čያ ተቋማቔ ዹተዘገበውን ዘገባ በተመለኹተ ዹሀገሹ ሔቄኚቱ ዚህዝቄ ግንኙነቔ ክፍልና ዚሄራ ኃላፊዎቜ ጋዜጣዊ መግለጫ በመሔጠቔ áˆˆáˆ›áˆ”á‰°á‰Łá‰ áˆ መሞኚራ቞ው ይታወሳል፡፡

ይሁንና በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ሀገሹ ሔቄኚቱ ኚቅጄርና ዝውውር ጋር በተያያዘ በሕግና በመመáˆȘያ ኹጠቅላይ ቀተ ክህነቔ ጋር በመናበቄ ኄዚሰራ መሆኑን በመግለጜ ያሔተላለፈው መግለጫ ፍáŒčም ሐሰቔ ኹመሆኑም በላይ በተደጋጋሚ በሀገሹ ሔቄኚቱ በኩል ዚሚሔተዋለው ዚመልካም አሔተá‹Čደር ቜግር በቅዱሔ áˆČኖዶሔ ጞዔቆ በተላለፈው መመáˆȘያ መሠሚቔ ኄንá‹Čፈታና ቅሬታ áˆˆáˆšá‹«á‰€áˆ­á‰Ą ወገኖቜም ይህን መሠሚቔ በማዔሚግ ፍቔሕ ኄንዱሰጄ በጠቅላይ ቀተክህነቔ áŠ áˆ”á‰°á‹łá‹°áˆ­ áŒ‰á‰ŁáŠ€ ተወሔኖ በተደጋጋሚ ዹተላለፈውን መመáˆȘያ አለመፈጾሙ áŒ‰á‰ŁáŠ€á‹áŠ• አሳዝኗል፱

ሔለሆነም በሀገሹ ሔቄኚቱ ዚሚሔተዋለው ዚመልካም áŠ áˆ”á‰°á‹łá‹°áˆ­ ቜግር በፍáŒčም ቆራጄነቔና ተጋዔሎ á‹šáˆšá‰łáˆšáˆá‰ á‰”áŠ“ ቀተክርá‰Čያንና አገልጋይ ካህናቔ áŠ„áŽá‹­á‰ł ዚሚያገኙበቔ ሁኔታ መፍጠር ይቻል ዘንዔ ቜግሩን በዝርዝር በማጄናቔ ኚመፍቔሔ áˆáˆłá‰„ ጭምር á‹šáˆšá‹«á‰€áˆ­á‰Ą ፯ (áˆ°á‰Łá‰”) áŠ á‰Łáˆ‹á‰” ያሉቔ ኼሚቮ ኄንዱሰዚሰሙ áŠ á‹”áˆ­áŒ“áˆáĄáĄ

ቜግሩን áˆˆáˆ˜áá‰łá‰” ዹሚደሹገው ኄልህ አሔጚራሜ ተጋዔሎም ፍáŒčም ቆራጄነቔን ዹሚጠይቅ በመሆኑ ቜግሩ ኚሔሩ ተፈቶ ዚቀተክርá‰Čያን ክቄር ተመልሶና ዚካህናቔ ኄንባ á‰łá‰„áˆ¶ á‰€áŒŁá‹­áŠá‰” ያለው በህግ ዚሚመራና ዚቀተክርሔá‰Čያናቜንን ቅዔሔና ዚሚመጄን አሠራር ተዘርግቶ መፈጾም ኄሔኚሚቜል ዔሚሔ በቆራጄነቔ ለመሄራቔ áŒ‰á‰ŁáŠ€á‹ በአንዔ ዔምጜ በመወሰን ዝርዝር ሁኔታውን በማጄናቔ ኚመፍቔሔ áˆáˆłá‰„ ጭምር ኄንá‹Čá‹«á‰€áˆ­á‰ĄáŠ

፩. መ/ሰ ቆሞሔ አባ ቃለጜዔቅ ሙሉጌታ(ዶ/ር) ኹጠቅላይ ቀተክህነቔፀ
áȘ.ሊቀ መዘምራን ሐሹገወይን ጫኔ ኹጠቅላይ ቀተክህነቔፀ
፫.ሊቀ ሔዩማን ኄሔክንዔር ገቄሚክርሔቶሔ ኹጠቅላይ ቀተ ክህነቔፀ
፬.á‹Č/ን ሙሉቀን ቔዕዛዙ(ኹምዕመናን)
፭.á‹Č/ን ዘለዓለም áˆČሳይ(ኹምዕመናን)
፼.á‹Č/ን ዘካርያሔ ወዳጆ(ኹህግ ቋሚ ኼሚቮ)
፯.á‹Č/ን áˆ”áŠ•á‰łá‹šáˆ ምሔጋናውን ኚሰንበቔ ቔምህርቔ
ቀቶቜ አንዔነቔ በመመደቄ ዚኄለቱን áˆ”á‰„áˆ°á‰Ł በጞሎቔ አጠናቋል፱

በአá‹Čሱ ዓመቔ ቅዔሔቔ ቀተክርሔá‰Čያን ቔኩሚቔ áˆ°áŒ„á‰ł መሄራቔ á‹«áˆˆá‰Łá‰”áŠ• áŒ‰á‹łá‹źá‰œ ቄፁዕ አቡነ ሩፋኀል áˆŠá‰€áŒłáŒłáˆ” áŠ áˆ”á‰łá‹ˆá‰áą

በአá‹Čሱ ዓመቔ ቅዔሔቔ ቀተክርሔá‰Čያን ቔኩሚቔ áˆ°áŒ„á‰ł መሄራቔ á‹«áˆˆá‰Łá‰”áŠ• áŒ‰á‹łá‹źá‰œ ቄፁዕ አቡነ ሩፋኀል áˆŠá‰€áŒłáŒłáˆ” áŠ áˆ”á‰łá‹ˆá‰áą
“””””””””””””
1. ሐዋርያው ቅዱሔ ያዕቆቄ በመልዕክቱ “ጌታ á‰ąáˆá‰…á‹” ቄንኖርም ይህን ወይም ያን ኄናደርጋለን ማለቔ á‹­áŒˆá‰Łá‰œáŠ‹áˆáąâ€ (ያዕ 4Ă·15) áŠ„áŠ•á‹łáˆˆá‹
ኹመንበሹ ፓቔርያርክ ጠቅላይ ቀተክህነቔን ጀምሼ በመላው ዓለም á‰Łáˆ‰á‰” አደሚጃጀቶቜ ዘንዔ ዘላቂነቔ ኄና ወጄነቔ ባለው መልኩ ዘመኑን ዹዋጀ ተቋማዊ አሠራር አገልግሎቱን áˆˆáˆ›áˆłáˆˆáŒ„ ኄንደ ኄግዚአቄሔር ፈቃዔ በሹጅም ኄና በአጭር ጊዜያቔ ዚሚተገበሩ ዚአገልግሎቔ áŠ á‰…áŒŁáŒ«á‹Žá‰œáŠ•áŁ አጠቃላይ ዹመáˆȘ ዕቅዔ ሔልቶቜን ኄና መርሐ áŒá‰„áˆźá‰œáŠ• በዹደሹጃው ያለው ዚቀተክርሔá‰Čያን መዋቅር መፈጾም á‹­áŒ á‰ á‰…á‰ á‰łáˆá€

2. ዚቅዔሔቔ ቀተክርሔá‰Čያን አንዔነቔ áŠ„á‹šá‰°áˆá‰łá‰°áŠ ያለ ክፍፍል በተለይም á‰ áŠŠáˆźáˆšá‹« ኄና በቔግራይ ዹታዹውን ወደ አንዔነቔ áˆ›áˆáŒŁá‰”áŠ“ በዕርቅፀ በሰላም ኄና በሔምምነቔ መፈጾም á‹­áŒˆá‰ŁáŠ“áˆá€ ይህንንም ለመፈጾም ዚፌዎራልም ሆነ ዹክልል áˆ˜áŠ•áŒáˆ”á‰łá‰” ኚቅዔሔቔ ቀተክርሔá‰Čያን ጎን ሆነው ሕግ ዚማሔኚበር ሄራ ኄንá‹Čሠሩ አበክሹን መሄራቔ ያሔፈልገናልፀ

3. በመንፈሳዊ ማኅበራቔ ዚሚሠሩ ሄራዎቜ ፀ በሰ/ቔ/ቀቔ áˆˆáŠ á‹łáŒŠá‹Žá‰œ ኄና áˆˆá‹ˆáŒŁá‰¶á‰œ ዹሚሰጧቾው ሁለገቄ አገልግሎቶቜ በዓለማቜን ላይ በዹጊዜው ዚሚኚሰተቱን መልካም ዕዔሎቜ ኄና ፈተናዎቜ ኄንá‹Čሁም በዹአህጉሹ ሔቄኚቱ ያለውን áŠá‰Łáˆ«á‹Š ሁኔታ ኚክርሔá‰Čያናዊ ዕሎቶቜ ጋር ባገናዘበ መልኩ ኄንá‹Čተገበሩ በመንፈሳዊ ጄበቄ ዹተቃኙ ቀልጣፋ ዚአፈጻጞም ሔልቶቜን በመኹተል መሄራቔ አለቄንፀ

4. ሕገ-ወጄ አጄማቂያንን ኄንá‹Čሁም በዹቩታው ያለቅዔሔቔ ቀተክርሔá‰Čያን ፈቃዔና ዕውቅና á‰ áˆ˜áŠ•á‰€áˆłá‰€áˆ” ዶግማዋን ቀኖናዋን ኄና ሄርዓቷን ዚሚጄሱ ግጭቔ ዚሚቀሰቅሱቔን ዚተደራጁ ኃይሎቜን ኄና ግለሰቊቜን ሄርዓቔ ማሔያዝፀ በተጹማáˆȘም በዓመቱ á‰ áˆ­áŠ«á‰ł á“áˆ”á‰°áˆźá‰œ ኄዚተጠመቁ áŠšá‰°áŠšá‰łá‹źá‰»á‰žá‹ ጋር ወደ ቅዔሔቔ ቀተክርሔá‰Čያን ሔለተመለሱ ማጜናቔና áˆ˜áŠ•áŠšá‰ŁáŠšá‰„ አለቄንፀ

5. ዹመáˆȘ ዕቅዱን አፈጻጞም ባለው ሂደቔ ውሔጄም በመላው ዓለም ኹመንበሹ ፓቔርያርክ ጀምሼ ኄሔኚ áŠ áŒ„á‰ąá‹« ሰ/ጉ/ቀቔ ዔሚሔ በተዘሹጋው á‹šáŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« ኊርቶዶክሔ ተዋሕዶ ቀተ ክርሔá‰Čያን መዋቅራዊ አደሚጃጀቔ ውሔጄ በአንá‹Čቔ ቀተ ክርሔá‰Čያን ጄላ ሄር á‰°áˆ°á‰Łáˆ”á‰ á‹ ለአንá‹Čቔ ቅዔሔቔ ቀተ ክርሔá‰Čያን ሐዋርያዊ á‰°áˆáŠ„áŠź ኄና ራኄይ áˆ˜áˆłáŠ«á‰” ሁለገቄ ኄና ጉልህ ሚና ዚሚጫወቱ áŠ áŒˆáˆáŒ‹á‹źá‰œáŠ• áˆ›á‰ áˆšá‰łá‰łá‰”áŠ“ ማሳደግ በአá‹Čሱ ዓመቔ ዚቅዔሔቔ ቀተክርሔá‰Čያን ዚቔኩሚቔ áŠ á‰…áŒŁáŒ« መሆን ይገባል ቄዏ አምናለሁ áˆČሉ á‰„áá‹•áŠá‰łá‰žá‹ ተናግሹዋል፱

መሔኚሚም 06 ቀን 2017 ዓ/ም
áŠ áˆ¶áˆłá€

ዚደብቄና ምዕራቄ አፍáˆȘካ ሀገሹ ሔቄኚቔ አጠቃላይ ዚሰበካ መንፈሳዊ áŒ‰á‰ŁáŠ€ ኄያካሔደ ይገኛል፱

መሔኚሚም 6 ቀን 2017 ዓ.ም

ዹáˆČዳማ ሀገሹ ሔቄኚቔ ቀተ ክህነቔ ጜ/ቀቔ ለቄፁዕ አቡነ ዼሮፍ ዹáˆČዳማ ሀገሹ ሔቄኚቔ ሊቀ áŒłáŒłáˆ”áŠ“ ዹታቩር ፍኖተ ጄበቄ መንፈሳዊ ኼሌጅ ሊቀ áŒłáŒłáˆ” ዚቅዱሔ áˆČኖዶሔ አባል ዚኄንኳን አደሹሰዎ መርሐ ግቄር áŠ áŠ«áˆ„á‹°áą

መሔኚሚም 5/2017 ዓ/ም

á‰ á‹”áˆŹá‹łá‹‹ ሀገሹ ሔቄኚቔ በቄፁዕ አቡነ በርተሎሜዎሔ ዹሀገሹ ሔቄኚቱ áˆŠá‰€áŒłáŒłáˆ” ዚቅዱሔ áˆČኖዶሔ አባል ዚተመራ ዚመሔቀልና ደመራን በዓል አሔመልክቶ ኹሚመለኹታቾው á‰Łáˆˆá‹”áˆ­áˆ» አካላቔ ጋር በመንበሹ ጔጔሔና áŠ á‹łáˆ«áˆœ áˆ”á‰„áˆ°á‰Ł á‰°áŠ«áˆ„á‹°áą

መሔኚሚም ፬/áłá» áČወ፯ ዓ.ም