የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

በመቅደላ ጦርነት ወቅት በእንግሊዝ ወታደሮች ከተዘረፉ የብራና መጻሕፍትና ልዩ ልዩ ንዋየ ቅድሳት መካከል እንደሆነ የሚገመት አንድ ጽላት እና የተለያዩ ቅርሶች በበጐ አድራጊዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ የርክክብ ሥነ ሥርዓት በታላቋ ብሪታንያ ለንደን ከተማ ተከናወነ።

September 22, 2023

መስከረም ፲፩ ቀን ፳፻ ፲ ፮ ዓም
“””””””””””””””””””””””””””””
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
******
በዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ለንደን (UCL) መምህር የሆኑትና ለረጅም ጊዜ በኢትዮጵያና በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤክርስቲያን ጉዳይ ላይ ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር ጃኮፖ ግኒስኪ በመቅደላ ጦርነት ዘመን ከአገር እንደወጣ የሚገመትና በእርሳቸው እጅ የነበረ ጽላት ወደ ሀገሩና ወደ መንበረ ክብሩ እንዲመለስ ከፍተኛውን አስተዋጽዖ እንዳበረከቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን በመወከል ጽላቱን የተረከቡት የልዑካን ቡድኑ ተወካይ ቀሲስ ዶ/ር አባተ ጐበና ምስጋናቸውን በልዑካኑ ስም ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በእንግሊዝ አገር በተለያዩ ተቋማትና ግለሰቦች እጅ የሚገኙ ንዋየ ቅድሳትን የማስመሡን ጉዳይ ትኩረት በመስጠት የማጣራቱንና የማስመለሱን ከተቋማቱና ከግለሰቦቹ ጋር በመነጋገር ሒደት እንዲከታተሉ ልዑካን ቡድን መመደቡ ታውቋል። የልዑካኑ ሰብሳቢ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የስዊድን፣ ስካንዲናቭያና ግሪክ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ምከትል ሰብሳቢው ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የጣልያንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ እንዲሁም ዋና ጸሐፊው ቀሲስ ዶ/ር አባተ ጐብና ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት፣ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት እና ከውጭ ጉዳይ መምሪያ ጋር በመነጋገር ጉዳዩን በቅርብ በመከታተል ለዚህ ፍጻሜ እንዲበቃ ያላሠለሰ ጥረት አድርገዋል።

ዶ/ር ጃኮፖ ግኒስኪ ጽላት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞች ዘንድ ያለውን የተለየ ክብር በመገንዘብ በቅዱስ ሲኖዶስ ከተመደቡላቸው ልዑካን ጋር በመመካከርና ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት በተከታታይ የተሰጠውን መመሪያ በመከተል ጽላቱ መንፈሳዊ ክብሩን በጠበቀ መንገድ ርክክቡ ተፈጽሞ ወደ ሀገሩ እንዲመለስ ማድረጋቸው እጅግ የሚደነቅ አርአያነት ያለ ተግባር መሆኑን የልዑካን ቡድኑ ፀሐፊ ቀሲስ ዶ/ር አባተ ጐበና ጨምረው ገልጸዋል።

በለንደን ከተማ ጥንታዊ ቅርሶችንና ሃይማኖታዊ ጥቅም ያላቸው ንዋያትን ለተገቢው ባለቤቶቻቸው የሚመልሱ ተቋማትንና ግለሰቦችን የሚያበረታታው “ሸሃራዛድ ፋውንዴሽን” (The Schaharazade Foundation) የተባለ ምግባረ ሠናይ ድርጅት ዶ/ር ጃኮፖ ግኒስኪ ጽላቱ ወደ ትክክለኛዋ ባለንብረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እንዲመለስ ለፈጸሙት አርአያነት ያለው መልካም ተግባር እውቅና በመስጠት የድርጅቱን ልዩ ሜዳልያና የምሥከር ወረቀት ሸልሟቸዋል።

የሸልማቱ ሥነ ሥርዓት መስከረም ፲ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም. በለንደን አቴናዩም መሰብሰቢያ አዳራሽ (The Atanaeum) የተካሄደ ሲሆን፣ በሽልማቱም ወቅት የፋውንዴሽኑ መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጣሂር ሻህ ዶ/ር ጃኮፖ ግኒስኪ ያደረጉትን ምሳሌነት ያለው ተግባር ሌሎችም ተቋማትና ግለሰቦች ሊከተሉት እንደሚገባ አሳስበው ይህንንም ለመደገፍ ድርጅታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ቅርሶች አስመላሽ ዓለም አቀፍ ኮሚቴን በመወከል በሥነ ሥርዓቱ ላይ የተካፈሉት የታሪክ ምሁሩና የኢትዮጵያ ባለውለታ የሆኑት የፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት ልጅ ዶ/ር አሉላ ፓንክረስት በበኩላቸው ጽላቱ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መመለሱ አጅግ ያስደሰታቸው መሆኑን ገልጸው፣ ከመቅደላ የተዘረፉ ሌሎችም ንዋየ ቅድሳት አንዲሁም ታሪካዊና ባህላዊ ቅርሶች ሁሉ እንዲመለሱ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

በብሪታንያ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ከቡር አምባሳደር ተፈሪ መለሰ በበኩላቸው ዶር ጃኮፖ ግኒስኪ ጽላቱን ክብሩን በጠበቀ መንገድ ለኢትዮጵያ አርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መመለሱ ፣ ሌሎችም የቤተመንግሥት የክብር መገልገያ የነበሩ የተለያዩ ቅርሶችም ያስደሰታቸው መሆኑን ገልጸው አሁን የኢትዮጵያን አዲስ ዓመት እየከበሮን ያለበት ሰሞን እንደመሆኑ እነዚህ ሁሉ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የአዲስ ዓመት ሥጦታ ሆነው እንደተሰጡ እንቆጥረዋለን በማለት ደስታቸውን ገልጸዋል።

ጽላቱ አስፈላጊው ቀኖናዊ ሥርዓት ከተፈጸመ ተፈጽሞ እሑድ
መስከረም ፲፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የስዊድን፣ስካንዲናቪያና ግሪክ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣ የልዑካ ሰብሳቢ, በተገኙበት በሚደረግ ሥርዓተ ማኅሌት፣ ጸሎተቅዳሴ እና ሥርዓተ ዑደት በካህናት፣ በምእመናንና በሰንበት ት/ቤት መዘምራን ልዩ የአቀባበልና የሽኝት ሥነ ሥርዓት ከተደረገለት በኋላ ወደ ሀገሩ ኢትዮጵያ ወደ መንበረ ክብሩእንደሚመለስ ቀሲስ ዶ/ ር አባተ ጐበና የልዑካኑ ጸሐፊ ጨምረው ገልጸዋል ሲል የውጪ ግንኙነት መምሪያ በላከልን ዘገባ ገልጿል።

Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል በዶምቢዶሎ ሎና በቄለም ወለጋ ልዩልዩ የልማት ሥራዎችን አከናወኑ ለችግረኛ ተማሪዎችም የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አየረጉ። Link to: ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል በዶምቢዶሎ ሎና በቄለም ወለጋ ልዩልዩ የልማት ሥራዎችን አከናወኑ ለችግረኛ ተማሪዎችም የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አየረጉ። ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል በዶምቢዶሎ ሎና በቄለም ወለጋ... Link to: ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመስቀል አደባባይ የሚከበረውን የደመራ በዓልን አስመልክቶ መልእክት አስተላለፉ። Link to: ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመስቀል አደባባይ የሚከበረውን የደመራ በዓልን አስመልክቶ መልእክት አስተላለፉ። ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top