የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡብ እና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይ፣ የቤተ መጻሕፍት ወመዘክርና የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ አላማጣ ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው።

January 13, 2024

ጥር ፬ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
****
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
——————-

ከሦስት ዓመታት በፊት የቋሚ ሲኖዶስ ተረኛ መሆናቸውን ተከትሎ ወደ ጠቅላይ ቤተክህነት የመጡት ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ በሰሜኑ የአገራችን ክፍል በተቀሰቀሰው ጦርነት ምክንያት በአዲስ አበባ ለመቆየት በመገደዳቸው ወደ ሀገረ ስብከታቸው ሳይሔዱ መቆየታቸው ይታወሳል።

የሰላም ስምምነቱ ከተፈረመ በኋላም በአካባቢው ያለው ችግር ከመሰረቱ ባለመፈታቱ ምክንያት በራያና አካባቢው የሚገኙ ኦርቶዶክሳዊያን ምዕመናን የሚባርካቸው፣ የሚያስተምራቸውና የሚያጽናናቸው አባት ማጣታቸውን ተከትሎ ለቅዱስ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ በአባትነት ተመድበው እንዲመጡላቸው ያቀረቡትን ጥያቄ መነሻ በማድረግ በጊዜያዊነት የራያና አካባቢው  ስድስቱ ወረዳዎች ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ተቋቁሞ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ እንዲመሩት የሰጠውን ውሳኔ ተከትሎ ጽሕፈት ቤቱ ተቋቁሞ ሥራ መጀመሩና በ42ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ሪፖርት ማቅረቡም ይታወቃል።

ይህን ተከትሎ ጽሕፈት ቤቱን በማቋቋም፣ በማደራጀትና ሰራተኞችን በመመደብ በርካታ ሥራዎችን ሲያከናውኑ የቆዩት ብፁዕነታቸው ጥር 3 ቀን 2016 ዓ/ም. የጥምቀት በዓልን ለማክበር፤ በጦርነትና በድርቅ የተጎዳውን ሕዝበ ክርስቲያንም ለማጽናናት  አላማጣ ከተማ ገብተዋል።

ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ  አላማጣ ከተማ ከመግባታቸው በፊት በቅርበት በምትገኘው ቆቦ ከተማ በብዙ መቶ ሺህ የሚቆጠሩ ካህናት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፣ ምዕመናንና ምዕመናት በአይሱዙ መኪናዎች፣ በቤት መከናዎች፣ በባጃጃጅና በእግር በማጀብ ደማቅ፣ ናፍቆት የተሞላበት፣ ጥልቅ የአባት ፍቅር የታየበትና በዓይነቱ ልዩና ደማቅ አቀባበል። አድርገውላቸዋል።

በአላማጣ ከተማ በሚገኘው ጥንታዊውና ታሪካዊው አላማጣ ደብረ መድኃኒት መድኀኔዓለም ካቴድራል በተደረገላቸው ደማቅ የአቀባበል ሥነ ሥርዓት ላይ በአላማጣና አካባቢው የስድስቱ ወረዳ ቤተክህነት አስተባባሪ ጽሕፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ሥዩማን ሀብቱ አየነው የእንኳን ደህና መጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በአቀባበል ሥነ ሥርዓቱ ላይ ለተገኙ በብዙ መቶ ሺህ ለሚቆጠሩ ካህናት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፣ ምዕመናንና ምዕመናት “እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋም።” በሚል ርዕስ  ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ልዑል እግዚአብሔር እንኳን በሰላምና በጤና አገናኘን ካሉ በኋላ ከሦስት ዓመታት በፊት ለቋሚ ሲኖዶስ አገልግሎት ወደ ጠቅላይ ቤተክህነት በተጓዝኩበት ወቅት በሰሜኑ የአገራችን ክፍል በተቀሰቀሰው ጦርነት ምክንያት መንገድ በመዘጋቱ አገልግሎቴን አጠናቅቄ ወደ አገሬ መመለስ ባለመቻሌ በዚያው ለመቆየት ተገድጃለሁ ብለዋል። ልጆቼ ስትራቡ፣ ስትጠሙ፣ ስትታረዙ፣ ስትሰቃዩና ስትሰደዱ አብሬአችሁ ባለመሆኔ እጅጉን ሳዝን፣ ሳለቅስና ወደ ፈጣሪዬ ሳለቅስ ከርሜአለሁ። ያለፉትን ሦስት ዓመታትም በጾም፣ በጸሎትና በናፍቆት በመቆየት ዳግም የምንገናኝበትን ጊዜ ስናፍቅ ከርሜአለሁ ብለዋል።

በአላማጣና አካባቢው በአጠቃላይም በሰሜኑ የአገራችን ክፍል በተቀሰቀሰው ጦርነት ምክንያት በሞተ ሥጋ የተለዩንን አባቶችካህናት፣ ዲያቆናት፣ ወንድሞችና እህቶችን ልዑል እግዚአብሔር ነፍሳቸውን ከደጋጎቹ አባቶቻችን ጎን ያኑርልን ካሉ በኋላ ላደረጋችሁልኝ ታሪካዊና ደማቅ አቀባበል ልባዊ ምስጋናዬን እያቀረብኩ ለወደፊቱ በእምነታችሁ ጸንታችሁ፣ አንድነታችሁን አጽንታችሁ እንድትኖሩ አባታዊ መልዕክቴን አስተላልፋለሁ፤ በማለት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጥተው የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል።

በብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የአቀባበል ሥነሥርዓት ዙሪያ ዝርዝር መረጃዎችን ለማድረስ በአካባቢው ኢንተርኔት ባለመኖሩ ምክንያት በፎቶግራፍ የተደገፈ መረጃ ለማድረስ ባንችልም ለወደፊቱ የተጠናከረ መረጃ ስናገኝ መረጃውን የምናደርስ መሆኑን ከወዲሁ እንገልጻለን።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/photo_2024-01-13_12-43-09-cover.jpg 445 350 tc https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg tc2024-01-13 16:36:352024-01-13 16:36:35ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡብ እና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይ፣ የቤተ መጻሕፍት ወመዘክርና የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ አላማጣ ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው።
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም የጥምቀት በዓል ጥንታዊ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ ሁኔታ ሰላማዊና ደማቅ በሆነ መልኩ እንዲከበር ሁሉም ወገን በኃላፊነት መንፈስ እንዲሠራ ብፁዕ አቡነ  አብርሃም አሳሰቡ። Link to: የ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም የጥምቀት በዓል ጥንታዊ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ ሁኔታ ሰላማዊና ደማቅ በሆነ መልኩ እንዲከበር ሁሉም ወገን በኃላፊነት መንፈስ እንዲሠራ ብፁዕ አቡነ  አብርሃም አሳሰቡ። የ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም የጥምቀት በዓል ጥንታዊ ሃይማኖታዊ... Link to: የደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል በ22 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው የእንጀራ ማምረቻ በቅዱስ ፓትርያርኩ ተመረቀ። Link to: የደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል በ22 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው የእንጀራ ማምረቻ በቅዱስ ፓትርያርኩ ተመረቀ። የደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top