የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም የጥምቀት በዓል ጥንታዊ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ ሁኔታ ሰላማዊና ደማቅ በሆነ መልኩ እንዲከበር ሁሉም ወገን በኃላፊነት መንፈስ እንዲሠራ ብፁዕ አቡነ አብርሃም አሳሰቡ።

January 13, 2024

ጥር ፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
———————-
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
“””””””””””””””””””””

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም የጌታችን የአምላካችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓልን በማስመልከት “ከክፉ ሽሽ መልካምንም አድርግ ሰላምን እሻ ተከተላትም” (መዝሙር ፴፬፥፲፫) የሚለውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ኀይለ ቃል መነሻ በማድረግ ባስተላለፉት መልዕክት የጥምቀት በዓል ጥንታዊና ሃይማኖታዊ መሰረቱን በጠበቀ መልኩ ሰላማዊ በሆነና በደማቅ ሥነ ሥርዓት ተከብሮ መዋል ይችል ዘንድ ሕዝበ ክርስቲያኑ በኃላፊነት መንፈስ ሊንቀሳቀስ እንደሚገባው ገልጸዋል።

በዓሉ የቤተክርስቲያን ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበ የአገራችን ብሎም የዓለማችን ታላቅ በዓል መሆኑን የገለጹት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በዓሉን በምናከብርበት ጊዜ ሕግን ባከበረ፣ ፍጹም ሃይማኖታዊ ሥርዓትን በጠበቀ፣ በኦርቶዶክሳዊ አለባበስ በተዋበ ሥርዓት በዓለ ጥምቀትን  በማክበር መንፈሳዊ ኃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል።

በዓለ ጥምቀቱ ዓለም አቀፋዊ እውቅና የተሰጠው በመሆኑን አበክረው የገለጹት ብፁዕነታቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልጆች ብቻ ሳትሆኑ በሰው ልጆች እኩልነት የምታምኑ   የተለያዩ እምነት ተከታዮች የሆናችሁ ኢትዮጵያን ወገኖች እንደ ሁል ጊዜው እምነታችሁ ባይሆንም “በዓሉ በዓላችን ነው።” እያላችሁ በተለያዩ ጊዜያት አብራችሁን የምታከብሩ፣ ድጋፍ የምታደርጉ ወገኖች በዓሉን ራሳችሁ አክባሪዎች፣ ራሳችሁ የጸጥታው አስተናጋጆች  የሰላም መሪዎች ናችሁ ቅድስት ቤተክርስቲያን በምታስተላልፈው መልዕክት መሰረት በዓሉ በሞቀና በደመቀ መልኩ እንዲከበር የተለመደውን ጥረት ታደርጉ ዘንድ በቅድስት ቤተክርስቲያን ስም ጥሬዬን አስተላልፋለሁ ብለዋል።

የጸጥታ አካላትን በተመለከተ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ባስተላለፉት መልዕክት የጸጥታው አካላት የሀገራችንን ሰላም ባስጠበቀ መንገድ በዓሉን ማክበራችን የሀገራችንን መልካም ነጽታ ማሳየት ይቻል ዘንድ ከማንኛውም ቅሬታ ነፃ በሆነ መንገድ ይህን ካላደረጋችሁ ይህን አናደርግም ከሚል አስተሳሰብ በመራቅ  ሕግን  የማስከበር ሥራችሁን ታከናውኑ ዘንድ  ቤተክርስቲያን መልዕክቷን ታስተላልፋለች ብለዋል።

በሌላ በኩል ጸብ አጫሪዎችን በተመለከተ ባስተላለፉት መልዕክት አሁን አሁን ቅድስት ቤተክርስቲያን እየተጎዳች ያለችው አማኞች ሳይሆኑ ነጠላ የሚለብሱ፣ አማኞች ሳይሆኑ ማተም የሚያደርጉ፣ የቤተክርስቲያን ልጆች መስለው በመካከል ገብተው ችግር ፈጥረው ቤተክርስቲያን ችግር እንደፈጠረች የሚያስመስሉ ስላሉ ተናባችሁ፣ ተዋውቃችሁ፣ በሥነ ሥርዓቱ በዓሉን በልዩ መንገድ እንድናስከብር ቅድስት ቤተክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች ብለዋል።

ብፁዕነታቸው አክለውም የጥምቀት በዓልን እንዲመራ በጠቅላይ ቤተክህነት  የተሰየመው ዓቢይ ኮሚቴ ከከተማችን አስተዳደርና ከሚመለከታቸው የፀጥታ ኃላፊዎች ጋር  በትላንትናው ዕለት ውይይት ያደረገ መሆኑን ገልፀው በውይይቱ በአንዳንድ አባቶች የተነገሩ ንግግሮችን  ቤተክርስቲያኗ ማውገዝ ይኖርባታል። ይህ ካልሆነ ግን እኛም በትብብር ለመሥራት እንቸገራለን በማለት የገለጹት ሀሳብ  ከጥምቀት በዓል አከባበር ጋር ተያይዞ መነሣቱ አግባብነት የለውም ካሉ በኋላ በተለያዩ ቦታዎች በአባቶች  የሚሰጡትን አስተያየቶች ቤተ ክርስቲያን ለምን በዝምታ አለፈችው የሚል ቅሬታ ቀደም ሲልም  እንዳለ አስታውሰው ቋሚ ሲኖዶስ  በጉዳዩ  ዙሪያ በስፋት ተወያይቶና የሚለውን ብሎ ጉዳዩ በቅዱስ ሲኖዶስ  ምልዓተ ጉባኤ ደረጃ  እንዲታይ  ወደዚያው አስተላልፎታል ብለዋል።

ቤተክርስቲያን ሞትን አታውጅም ትንሣኤን ነው የምታውጀው። ወደ ንስሐ ትጣራለች እንጂ ሞትን አታውጅም  ያሉት ብፁዕነታቸው ጉዳዩን በሰማሁ ጊዜ በጣም ነው ያዘንኩት መግለጫ በግሌ ለመስጠትም ተዘጋጅቼ ነበር ካሉ በኋላ መንገዱን ስናየው ግን መጠላለፊያ እንጂ የጽድቅ ስላልሆነ ነው ዝም ያልነው ብለዋል።

የብፁዕ አቡነ ጴጥሮስን የአሜሪካ ጉዞን በተመለከተም በሀገረ ስብከታቸው የጥምቀት በዓልን ለማክበር በሀገረ ስብከታቸው ቅዳሴ ቤቱ የሚከበረውን  ቤተክርስቲያን ለመባረክ ታቦት ይዘው ሕጋዊ ደብዳቤ ተጽፎላቸው በህጋዊ መንገድ የተጓዙ መሆኑን ገልጸው የሄዱበትን ሐዋርያዊ ጉዞ አጠናቀው ወደ አገር ቤት በመመለስ መደበኛ ሥራቸውን እንደሚያከናውኑ  አስታውቀዋል።

በመጨረሻም በዓሉ የሰላም፣የደስታ፣የጤናና የበረከት እንዲሆንልን በመመኘት መልዕክታቸውን አጠቃለዋል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የብፁእ አቡነ ጴጥሮስ ሐዋርያዊ ጉዞ በቤተ ክርስቲያን ሕግ እና ሥርዓት መሠረት የተፈቀደ ነው። Link to: የብፁእ አቡነ ጴጥሮስ ሐዋርያዊ ጉዞ በቤተ ክርስቲያን ሕግ እና ሥርዓት መሠረት የተፈቀደ ነው። የብፁእ አቡነ ጴጥሮስ ሐዋርያዊ ጉዞ በቤተ ክርስቲያን... Link to: ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡብ እና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይ፣ የቤተ መጻሕፍት ወመዘክርና የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ አላማጣ ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው። Link to: ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡብ እና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይ፣ የቤተ መጻሕፍት ወመዘክርና የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ አላማጣ ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው። ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡብ እና የደቡብ ምሥራቅ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top