የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

በሲዳማ ሀገረ ስብከት በሀዋሳ ከተማ የመስቀል ደመራ በዓል በታላቅ ድምቀት ተከበረ።

September 27, 2024

መስከረም 16/2017 ዓ/ም
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በበዓሉ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ ሀገረ ስብከትና የታቦር ፍኖተ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል፣መጋቤ ሃይማኖት አባ አብርሃም የቅዱስ ሲኖዶስ ምክትል ጸሐፊ፣ ክቡር መኩሪያዬ መርሻዬ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ፣መጋቤ ጥበባት ቀሲስ ሞላልኝ መርጊያ የሲዳማ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣መጋቤ ሥርዓት ዳንኤል ጌታቸው የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሕዝብ ግንኙነት መመሪያ ዋና ጸሐፊ፣ከፍተኛ የመንግሥት ባለ ስልጣናት፣የሀገረ ስብከቱ የየመምሪያ ኃላፊዎች፣ላዕከ ወንጌል ደግፌ ባንቡራ የሀዋሳ ከተማና ዙሪያ ወረዳ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን፣ ምእመናንና ምእመናት የተገኙ ሲሆን ጸሎተ ወንጌል ከተደረሰ በኋላ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ያሬዳዊ ወረብ ቀርቦ በሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን ያሬዳዊ ወረብና መንፈሳዊ ትርኢትቀርቧል።

በመቀጠል የሀዋሳ ወረዳ ዋና ሥራ አስኪያጅ ላዕከ ወንጌል ደግፌ ባንቡራ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈው የሀገረ ስብከቱን ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ጥበባት ሞላልኝ መርጊያን ጋብዘዋል። የሲዳማ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ጥበባት ቀሲስ ሞላልኝ መርጊያ በዓሉን የምናከብርትን መሠረታዊ ምክንያት አንስተዋል በዚህም ውስጥ በክርስቶስ መስቀል ሰላም መደረጉን ደመራው ዕሌኒ መስቀሉን ለመፈለግ ያደረገችውን የሚያሳይ ነው የሚል መልእክት አስተላልፈው ብፁዕነታቸውን የዕለቱን ትምህርት እንዲያስተምሩና አባታዊ ቡራኬ እንዲሰጡ ጋብዘዋል።

ብፁዕ አባታችን አቡነ ዮሴፍ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈው መስቀሉ ተገኘ በሚል ተነስተው መስቀል ክርስቶስ ለሰው ልጆች የባሕርይ ፍቅሩን የገለጠበት ለሰው ልጆች ደሙን ያፈሰሰበት ጠላት ዲያብሎስን ድል የነሳበት ስለሆነ በካህናት እጅ ይያዛል በቤተ ክርስቲያን ምልክት ሆኖ ይቀመጣል በልብሳችን ከዚያም አልፎ በሰውነታችን ምልክት እናደርገዋለን። በሕይወት እያለን ብቻ አይደለም በመቃብራችንም ሳይቀር ምልክት ይደረጋል።ምክንያቱም እኛ ሕይወት ያገኘንበት ጠላት ዲያብሎስ የተሸነፈበት ስለሆነ።

ስለዚህ መስቀል ሰላም ያገኘንበት ስለሆነ መስቀል ላይ የዋለውን ክርስቶስን ስናይ የሰላም ሰዎች እንሆናለን።
ታዲያ ለምንድንነው የማንግባባው ካልን ከመስቀሉ ላይ ዓይናችንን ስናነሳና መስቀል ላይ የዋለውን ክርስቶስን ስንረሳ ነው።በጥቅሉ በክርስቶስ የፈረሰውን የጠብ ግድግዳ መልሰን መገንባት የለብንም የሚል ሰፊ ትምህርት አስተምረዋል። በመቀጠል የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈው በብፁዕነታቸው ጸሎት መርሐ ግብሩ ተጠናቋል።

መረጃው የሲዳማ ሀገረ ስብከት ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ነው።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: “ወወሀብኮሙ ትእምርተ ለእለ ይፈርሁከ ከመ ያምስጡ እምገጸ ቀስት – ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ ፥ ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው” Link to: “ወወሀብኮሙ ትእምርተ ለእለ ይፈርሁከ ከመ ያምስጡ እምገጸ ቀስት – ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ ፥ ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው” “ወወሀብኮሙ ትእምርተ ለእለ ይፈርሁከ ከመ ያምስጡ... Link to: ዘዕጣን አንፀረ ሰገደ ጢስ በጎልጎታ ዘደፈኑ አይሁድ ዮም ተረከበ እፀ መስቀል ክቡር፡፡ (በእጣን የተቃጠለው ጢስ ወደሰማይ ወጥቶ መስቀሉ ወደተቀበረበት ቦታ ሰገደ በዚህም አይሁድ የቀበሩት ዕፀ መስቀል ዛሬ ተገኘ)፡፡ Link to: ዘዕጣን አንፀረ ሰገደ ጢስ በጎልጎታ ዘደፈኑ አይሁድ ዮም ተረከበ እፀ መስቀል ክቡር፡፡ (በእጣን የተቃጠለው ጢስ ወደሰማይ ወጥቶ መስቀሉ ወደተቀበረበት ቦታ ሰገደ በዚህም አይሁድ የቀበሩት ዕፀ መስቀል ዛሬ ተገኘ)፡፡ ዘዕጣን አንፀረ ሰገደ ጢስ በጎልጎታ ዘደፈኑ አይሁድ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top