የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልጅ ያሬድ በተባለው ግለሰብ እና ተባባሪዎቹ ላይ ክስ እንዲመሠረት ለፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ ጥያቄ አቀረበች።

ነሐሴ ፳፱ ቀን ፲ወ፭ ዓ.ም
“”””””””””””””””””””””””
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
******

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልጅ ያሬድ በተባለውን ግለሰብ እና በተባባሪዎቹ ላይ ክስ እንዲመሠረት ለፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ በላከችው ደብዳቤ ጠይቃለች።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ባቀረበችው አቤቱታ ከዚህ ቀደም በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተምሮ ፣ በሃይማኖት አባቶቿ ፣ በምዕመናኗ እና የአምልኮ ቦታዎቿን ባንቋሸሹ እንዲሁም የሐሰተኛ ንግግር ባስተላለፉት በነፓስተር ዮናታን አክሊሉ ፣ በነቢይ ኢዩ ጩፋ ፣ በአዲስ ኪዳን ካህናት ቤተ ክርስቲያን እና በክራይስት አርሚ ኢንተርናሽናል ቤተ ክርስቲያን ላይ ላቀረበችው አቤቱታ ውጤት በመጠባበቅ ላይ ሳለች ይን የመሰለ ድፍረት የተሞላበት ድርጊት እንደገጠማት ገልጻለች።

በዚህ በግለሰቡ እና ተባባሪዎቹ ድፍረት የተሞላበት ድርጊት በበርካታ ኦርቶዶክሳዊያንና ኢትዮጵያውያን ላይ ከፍተኛ ቁጣን በመቀስቀሱን እና ከፍትህ አደባባይ ፍርድን ለማግኘት ይቻል ዘንድ ይሔን አቤቱታ ማቅረቧን በጻፈችው ደብዳቤ ገልጻለች።

የተከሳሹ ድርጊት በዋናነት የቤተ ክርስቲያኗን መልካም ስም የሚያጎድፍ ድርጊት ከመሆኑም በላይለቤተ ክርስቲያን ያለውን ጥላቻ በድፍረት በመግለጽ ሰዎችን ለአመጽ እና ብጥብጥ የሚያነሳሳ በመሆኑ ፤ የቤተክርስቲያንን የአምልኮ ቦታ ያራከሰ በመሆኑ ፤ የምዕመናኑን ስሜት የሚነካ ፣ በሚያዋርድ መልኩ የተፈጸመ በመሆኑ በግለሰቡ እና በተባባሪዎቹም ላይ ጭምር ፖሊስ ተገቢውን ምርመራ በማድረግ ክስ በመመስረት ለአቃቤ ሕግም እንዲልክ ጠይቃለች።