ዚተዛባ መሹጃ ለህዝብ በማድሚስ ዚሚፈታ ዚመልካም አስተዳደር ቜግር ዚለም።

በዛሬው ዕለት ዹጠቅላይ ቀተክህነትና ዚአዲስ አበባ ሀገሹ ስብኚት አስተዳደር ጉባኀ በጋራ ባደሚጉት ስብሰባ በርካታ ጉዳዮቜ ተነስተው ሰፊ ውይይት ተደርጎባ቞ዋል።

፵፪ኛው ዚሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኀ በማዕኹላዊ ጎንደር ሀገሹ ስብኚት ተካሔደ።

ዹማዕኹላዊ ጎንደር ሀገሹ ስብኚት ፵፪ኛውን አጠቃላይ ዚሰበካ መንፈሳዊ ጉባኀውን አካሔደ።ዚሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባዔው ኚመካሔዱ አንድ ቀን ቀደም ብሎም በሀገሹ ስብኚቱ መሰብሰቢያ አዳራሜ ታላቅ ጉባኀ መካሔዱን ኹሀገሹ ስብኚቱ ዹደሹሰን ዘገባ ያመለክታል።

ዚአዲስ አበባ ሀገሹ ስብኚት ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ቀተክህነት መሆኑን በመገንዘብ ሕግና መመሪያን አክብሮ እውነትና እውነተኝነትን መርሁ አድርጎ እንዲሰራ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አሳሰቡ።

በአዲስ አበባ ሀገሹ ስብኚት ዚሚታዩ ዚመልካም አስተዳደር ቜግሮቜን በጋራ ለመፍታትና መሰሚታዊ ለውጥ ለማምጣት ዹጠቅላይ ቀተክህነትና ዚአዲስ አበባ ሀገሹ ስብኚት ዚአስተዳደር ጉባኀ አባላት በዛሬው እለት ባደሚጉት ዚጋራ ጉባኀ ተስማሙ።

ዹጠቅላይ ቀተክህነትና ዚአዲስአበባ ሀገሹ ስብኚት አስተዳደር ጉባዔ አባላት በጜርሐ ተዋሕዶ አዳራሜ ዚጋራ ጉባዔ በማድሚግ ላይ ና቞ው።

ኅዳር ፲፰ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
=================
አዲስ አበባ -ኢትዮጵያ
“””””””””””””””””””””

ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን አስተዳደር ጉባኀ ኚአዲስ አበባ ሀገሹ ስብኚት ዚአስተዳደር ጉባኀ አባላት ጋር በሁለትዮሜ ዚአሰራር ሒደት፣በመልካም አስተዳደር፣በሕግ ፣ደንቊቜና መመሪያዎቜ አኚባበር በአጠቃላይ ሥራዎቜን በተቋማዊ አሰራር ሒደት በማኹናወን ዙሪያ ዚጋራ መድሚክ ተዘጋጅቶ ውይይት እንዲደሚግ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን ጠቅላይ ቀተክህነት አስተዳደር ጉባኀ ያስተላለፈውን ውሳኔ ተኚትሎ ዛሬ ኅዳር ፲፰ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም በጜርሐ ተዋሕዶ አዳራሜ ዚጋራ ጉባኀ በማካሔድ ላይ ና቞ው።

በጉባኀው መክፈቻ ሥነሥርዓት ላይ ዚተገኙት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጚጌ ዘመንበሹ ተክለሃይማኖት ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት፣ቃለ በሚኚትና ቡራኬ በቀተክርስቲያናቜን ያለውን ዚመልካም አስተዳደር ቜግር ሁላቜንም እናውቀዋለን።ማስተካኚልም እንቜላለን ብለዋል።

እኛ በቀተክርስቲያናቜን ዚሚስተዋለውን ቜግር ለማስተካኚል ዹምንቾገሹው ልባቜን ስላልተስተካኚለ ነው።ያሉት ቅዱስ ፓትርያርኩ ራሳቜንን ሳናስተካክል ሌላውን ማስተካኚል ስለማንቜል ቅድሚያ ራሳቜንን ለማስተካኚል ቆርጠን መነሳት ይኖርብናል ብለዋል።

አያይዘውም ሁላቜንም ዹቆምነው ለቀተክርስቲያናቜን እንጂ ለሌላ ዓላማ አይደለም።ያሉት ቅዱስነታ቞ው ቜግሮቻቜንን ለመፍታት መወያዚት ተገቢ ነው።”ኚልብ ካለቀሱ እንባ አይገድም” እንደሚባለው ሁሉ ቜግሮቻቜንን ለመፍታት ኚልብ ኚተነሳን ዚሚያስ቞ግር ነገር ይኖራል ብለን እናምናለን ካሉ በኋላ ኚተጠያቂነትና ኚተወቃሜነት ለመዳን፣ቀታቜንን ለማቅናትና ለማስተካኚል ዹሚጎለን ምንድነው ?ያሉት ቅዱስነታ቞ው ይህን ለማድሚግና ቀተክርስቲያናቜንን ለመጠበቅ ሙሉ ሥልጣንና ኃላፊነት እያለን መ቞ገራቜን ያስገርማል ብለዋል።

ዘወትር ሁላቜንም ራሳቜንን መመርመር አለብን ዚት ነው ያለነው፣ምንድነው ዚምንሰራው፣ወዎት ነው ዹምንሔደው ብለን ራሳቜንን በመጠዹቅ ያለፈውን ጊዜ ቜግሮቜ ማሰብና በተሰጠን መንፈሳዊ ኃላፊነት ልክ በመስራት ቀተክርስቲያንን መጠበቅና ምዕመናንን ዚሚያሚካ ተግባር መፈጾም ይኖርብናል ያሉት ቅዱስነታ቞ው ሁላቜንም ራሳቜንን በአግባቡ በመመርመር ራሳቜንን እናስተካክል ካሉ በኃላ በአንድነትና በጜናት ለቀተክርስቲያናቜን እንቁም።በመመካኚር አንድ ሆነን በመቆም ለቀተክርስቲያን ህልውና በጋራ እንስራ እኛ ተመካሪዎቜ አይደለንም መካሪዎቜ እንጂ ስለዚህ መመካኚር ቜግሮቜን ለመቅሹፍ ዹሚጠቅም ስለሆነ ተመካክሚን እንስራ ቜግሮቜንም በግልጜ በማውጣት ለቜግሮቻቜን መፍትሔ በማበጀት ለውጀት ልናበቃው ይገባል በማለት አባታዊ መልእክታ቞ውን በማጠናቀቅ ጉባኀውን በይፋ ኚፍተዋል።

ብፁዕ አቡነ አብርሃም ዹጠቅላይ ቀተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና ዚባህርዳር ሀገሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ በበኩላ቞ው ባስተላለፉት መልዕክትፊ መልካም አስተዳደርን ለማምጣትና ቜግሮቜን ለመፍታት ውይይት ወሳኝ ነው።ቅዱስነትዎም በቀተክርስቲያናቜን መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን ዚዘወትር ምኞትዎና ጞሎትዎ እንደሆነ ይታወቃል።

በዚህ ጊዜ ዚሚታዚውን ዚመልካም አስተዳደር ቜግሮቜን በጋራ ተወያይተን መፍታትና ዚቁጥጥር ሥርዓታቜንን በማጥበቅ ቜግሮቜን በአግባቡ መፍታት አለብን ብለዋል አያይዘውም ህገወጥ ቅጥርና ዝውውርን በተመለኹተ እዚተኚናወነ ዹሚገኘውን ህገ ወጥ ቅጥርና ዝውውር በማሹም በቅዱስ ሲኖዶስ ጞድቆ በቀሹበው መተዳደሪያ ደንብ መሰሚት መስራት ይኖርበታል ብለዋል።

ሀገሹ ስብኚቱና ጠቅላይ ቀተክህነቱ ተናበውና ተግባብተው መስራት በሚገባ቞ው ጉዳዩቜ ላይም ሕግንና ሕግን መሰሚት አድርገን መስራት ስለሚገባ቞ው ይህን መድሚክ ለማዘጋጀት ተገደናል ያሉት ብፁዕነታ቞ው ዹዚህ መድሚክ ዓላማ ለመወነጃጀል ለመነቃቀፍና ለመተቻ቞ት ሳይሆን በመወያዚትና በመግባባት በሀገሹ ስብኚቱ ዚሚታዩትን ቜግሮቜ ለመፍታት ነው በማለት ዚመክፈቻ ንግግራ቞ውን አጠቃለዋል።

ጉባኀው በዛሬው እለት በሚያካሒደው ጥልቅ ውይይት ሕግ፣መመሪያ፣ደንቊቜና ተቋማዊ አሰራሮቜን በጠበቀ መልኩ ሥራዎቜን በማኹናወን ማዕኚላዊነትን ባለማክበር ዙሪያ ዚሚታዩ ክፍተቶቜን በመሙላት ተቋማዊና ሕጋዊ አሰራሮቜን በመተግበር በሀገሹ ስብኚቱና በጠቅላይ ቀተክህነት መካኚል መዋቅራዊ ግንኙነቶቜን ማጠናኹር ዚሚያስቜሉ ልዩልዩ ውሳኔዎቜን ያስተላልፋል ተብሎ ይጠበቃል።

ብፁዕ አቡነ ጎጥሮስ (ዶ/ር) በዓለም አብያተ ክርስቲያናት ስብሰባ እዚተካፈሉ ይገኛሉፀ

ኅዳር ፲፰ቀን ፳፻ ፲ወ፮ዓ.ም
“”””””””””””””””””””””””””
ብፁዕ አቡነ ጎጥሮስ (ዶ/ር) ዚቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጾሐፊ ዚኒውዮርክና አካባቢው ሀገሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስፀ ዹዓለም አብያተ ክርስቲያናት ስብሰባን ለመካፈል ቅድስት ቀተ ክርስቲያንን ወክለው ዹተጓዙ ሲሆን ስብሰባው በጄናቫ ቩሮ ዹቮዎሎጅ ትምህርት ቀት ቅጥር ግቢ እዚተካሄደ ይገኛል፡፡

ዹዓለም አብያተ ክርስቲያናት ጉባኀ በዹጊዜው በሚያደርጋ቞ው ኹፍተኛ ጉባኀዎቜ ላይ ቀተ ክርስቲያን በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በሚመራ ልዑክ ዚምትሳተፍ ሲሆን በዚሁ መሠሚት ኚኅዳር 17-20 ቀን 2016 ዓ/ም በሚደሹገው ጉባኀ ለመገኘት ኹመንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቀተ ክህነትና ኚልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኊ ኮሚሜን ዹተወኹሉ ልዑካንን በመምራት በጉባኀው እዚተሳተፉ መሆኑ ታውቋል፡፡

ብፁዕነታ቞ው በቅርቡ በቅዱስ ሲኖዶስ ዚታወጀውም ዚጞሎትና ምኅላ መርሐ ግብር ላይ በመጀመሪያዎቹ ሊስት ቀናት በመንበሹ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ቀተ ክርስቲያን ኚብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩና ኚብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጋር ሲሳተፉ ዚቆዩ ሲሆን ኚጉዳዩ አስፈላጊነት አንፃር ወደ ዓለም አቀፍ ስብሰባ ቢጓዙም በዚያው ባሉበት ቅድስት ቀተ ክርስቲያናቜን ያወጀቜውን ጟምና ጾሎተ ምኅላ ዚተሚዱ ዚጉባኀው ተሳታፊዎቜ እነሱም ኚኢትዮጵያውያን ጋር ያላ቞ውን አጋርነት በመግለጜ አብሚው መሆናቾውን በጉባኀው ላይ ገልጞዋል፡፡

ብፁዕነታ቞ውም ዚቀተ ክርስቲያንን ተልእኮ ለመፈጾም ባሉበት ኚልኡካና቞ውና ጋር ሥርዓቱን እያካሄዱ መሆኑ ታውቋል፡፡

ሀገራዊ ሰላምን፣ መሚጋጋትንና አንድነት ማስፈንን አስመልክቶ በጥቅምቱ ዚቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ በተላለፈው ውሳኔ መሠሚት ኹቋሚ ሲኖዶስ ዹተሰጠ መግለጫፀ

“ሰላምዹ አኀድግ ለክሙ ወሰላመ አቡዚ እሁበክሙ፡- ሰላሜን እተውላቜኋለሁ፥ ዚአባ቎ ሰላምም እሰጣቜኋለሁ” (ዮሐ.14፡27)

ዚምሥራቅ ሾዋ ሀገሹ ስብኚት 42ኛው ጠቅላላ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኀ በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ዹሀገሹ ስብኚቱ ሊቀ ጳጳስ ጾሎተ ቡራኬ በይፋ ተጀመሚ።

በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ዹ 42ኛው ዚምሥራቅ ሾዋ ሀገሹ ስብኚት ጠቅላላ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኀ በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ዚምሥራቅ ሾዋ ሀገሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ ዹዝዋይ ሐመሚ ብርሃን ቅዱስ ገብርኀል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ ዹበላይ ኃላፊ ዚኢትዮጵያ ሃይማኖቶቜ ተቋማት ጉባኀ ዚቊርድ ሰብሳቢ ጾሎተ ቡራኬ ፡ ዹጠቅላይ ቀተ ክህነት ልዑካን ፡ክቡር መልአኹ ምሕሚት ቆሞስ አባ ገብሚ መድኅን ንጉሀ ዹሀገሹ ስብኚቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ፡ ዹሀገሹ ስብኚቱ ዹዹክፍል ኃላፊዎቜ ፡ ዚዚወሚዳ ቀተ ክህነቱ ሊቃነ ካህናትና ሠራተኞቜ ፡ ዚአድባራት አስተዳዳሪዎቜ ፡ ዚጜ/ቀት ሠራተኞቜ ፡ ዹሰ/ት/ቀቶቜ አንድነት ተወካዮቜ፡ ጥሪ ዹተደሹገላቾው እንግዶቜ በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል፡፡

ዚአሶሳ እንዚ መካነ ገነት መድኃኔአለም ካ቎ዎራል ዹህንፃ ግንባታ ኮሚ቎ ዹመንበሹ ጵጵስና ገዳማትና አድባራት ዚማጠናቀቂያ ዚገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርጉለት ጠዚቀፀ

ሀ/ስብኚቱ ዚአሠሪ ኮሚ቎ውና ዚካ቎ዎራሉ ሰበካ ጉባኀ ያቀሚበውን ጥያቄ መሠሚት በማድሚግ ኹመንበሹ ጵጵስና ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎቜና ዚሰበካ ጉባኀ አባላት ጋር ውይይት አድርጓል።

ውይይቱን ዚመሩት ዚሀገሚስብኚቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአኹ ፀሐይ ቆሞስ አባ ዘካርያስ ፀጋ እንደገለጹት ዹህንፃ ግንባታውን ምርቃት በተመለኹተ ዚካ቎ዎራሉ ሰበካ ጉባኀ እና ዹሀ/ስብኚቱ ጜ/ቀት ኃላፊነት ወስደው ዐብይ ኮሚ቎ በማቋቋም ወደ ሥራ እንደሚገባ ገልጾው ዹመንበሹ ጵጵስ ገዳማትና አድባራትን በመያዝ ካህናትን ሰብስቊ ግንዛቀ መፍጠር እንደሚገባ ገልጾው ግንዛቀ

ዹተፈጠሹላቾውን ካህናት በማሠማራት ዚማጠናቀቂያ ዚገቢ ማሰባሰብ ሥራ በመሥራት እስኚ መጋቢት 27 ቀን 2016 ዓ/ም ሥራው ተጠናቆ በዘመነ ትንሣኀ ለማስመሚቅ ቅድመ ዝግጅት ማድሚግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ዚሀገሚስብኚቱ ዋና ፀሐፊ ሊቀልሳናት ትህትና አበበ በበኩላ቞ው ዹመንበሹ ጵጵስና ገዳማትና አድባራት አጥቢያ አቢያተክርስቲያናት ዚሰበካ ጉባኀ ካህናትና ምዕመናን በህንፃ ግንባታው ማስፈጞሚያ ዚገቢ አሰባሰብ ንቅናቄ ሥራ ላይ ዹነቃ ተሳትፎ ማድሚግ እንደሚገባ቞ው ተናግሹው ይህም ዚቀተክርስቲያን አንድነት መገለጫ ነው ብለዋል። ምንግዜም ቢሆን ዚቀተክርስቲያን አንድነት በሥራ መገለጜ እንዳለበት በሰፊው ያብራሩት ዋና ፀሐፊው በዹደሹጃው ያለን ዚቀተክርስቲያን አገልጋዮቜ ፍቅርን እና አንድነትን በመያዝ ዚትብብርን መንፈስ ማዳበር አለብን ብለዋል።

ዚአሶሳ እንዚ መካነ ገነት መድኃኔአለም ካ቎ዎራል ዋና አስተዳዳሪ ሊቀ-አዕላፍ አባ ገ/መስቀል ምንዳ እንደተናገሩት አሁን ሥራውን አጠናቆ ለማስመሚቅ አራት ሚልዮን ብር እንደ ሚያስፈልግ ገልጾው ብሩን ለማሰባሰብ ዹመንበሹ ጵጵስና ገዳማትና አድባራት ዚሚቜሉትን ተኹፋፍለው ቃል እንዲገቡ ካህናት ግንባር ቀደም ተሳታፊዎቜ እንዲሆኑ ለማስቻል በሀ/ስብኚቱ በኩል ጥሪ ተደርጎ ምክክር ማድሚግ አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን አስታውሰዋል።

ዹህንፃ ግንባታ ኮሚ቎ው ዋና ሰብሳቢ አቶ ይሁን ጉዎታ እንደገለጹት ምዕመናን በዓይነት ድጋፍ እንዲያደርጉ በመድኃኔዓለም ስም ጠይቀው ዚሙሌት ሥራ ለመሥራት አሥር ቢያጆ ሀርድ ኮር ድንጋይ”ፀ አምስት ቢያጆ አሞዋፀ ሁለት መቶ ሃምሳ ኩንታል ስሚንቶፀ ዚኳርቲዝ ቀለም በዋናነት እንደሚያስፈልግ ተናግሚዋል።

ዹመንበሹ ጵጵስና ገዳማትና አድባራት አጥቢያ አቢያተክርስቲያናት አስተዳዳሪዎቜና ዚሰበካ ጉባኀ አባላትም ዚሚቜሉትን ሁሉ ዮጋፍ ለማድሚግ ቃል ገብተዋል።

በቅርቡም ዚገቢ ማሰባሰብ ንቅናቄውን ለመጀመር ኚካህናትና ኚዲያቆናት ጋር ምክክር እንደሚደሚግ ውሳኔ ላይ ተደርሷል።

ዘገባው ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን ዚቀኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ሀገሹ ስብኚት ህዝብ ግንኙነት ክፍል ነው።
ኅዳር 08 ቀን 2016 ዓ/ም
አሶሳፀ

ለሊስት ቀናት ዹቆዹው ዚምዕራብ ሐሹርጌ ሀገሹ ስብኚት 22ኛው መደበኛ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኀ በሰላም ተጠናቀቀ።

ለሊስት ቀናት ዹቆዹው ዚምዕራብ ሐሹርጌ ሀገሹ ስብኚት 22ኛው መደበኛ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኀ በሰላም ተጠናቀቀ።

“ደን(ዕጜዋት )ለምድራቜን ዹደም ሥርና ልብሷ ነው።ስለሆነም ምድራቜን ስሯ ተቆርጩ ሕይወቷን እንዳታጣ ዹመጠቅና ዚመንኚባኚብ ኃላፊነት ዹሰው ልጆቜ በመሆኑ ደኖቻቜንን በመንኚባኚብ ኃላፊነታቜንን እንወጣ።”

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ኚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዹተሰጠ መግለጫ፡፡