የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

‹‹ብዙዎች በጉጉት ሲጠብቋት የነበረች ይህች ዕለት እግዚአብሔር የመረጣት ታላቅ ቀን ናት›› ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በወለቴ ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የምረቃ በዓል

July 14, 2025

‹‹ብዙዎች በጉጉት ሲጠብቋት የነበረች ይህች
ዕለት እግዚአብሔር የመረጣት ታላቅ ቀን ናት››
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በወለቴ ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የምረቃ በዓል

ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም

በቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል፤ የወለቴ ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ቤቱ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል ። ሕንጻ ቤተክርስቲያኑ በ1000 ሺ ካሬ መሬት ያረፈና በአዲስ መልክ የተገነባ ግዙፍና ዘመናዊ ሕንጻ ነው።

በበዓሉ ላይ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የተሰማቸውን ታላቅ ደስታና ምሥጋና ገልጸዋል፡፡ ብፁዕነታቸው ‹‹ብዙዎች በጉጉት ሲጠብቆት የነበረች ይህቺ እግዚአብሔር የመረጣት ቀን ናት›› ሲሉ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል ።

ብፁዕ አቡነ እንጦንስ የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ በበኩላቸው ‹‹ቃሉ እንደሚያዘን የእግዚአብሔር ማደሪያ ለመሆን ክርስቲያናዊ ምግባር በመተግበር ከየትኛውም እኩይ ተግባር፣ ኃጢአትና በደል ተጠብቀን በቅድስና ሕይወት መኖር ይጠበቅብናል›› ሲሉ አስተምረዋል ። አያይዘውም ሐምሌ 7 ቀን የሚከበረውን ሥሉስ ቅዱስ ወደ አብርሃም ቤት የገቡበትን ቀን የሚያስታውስ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል።

በክብረ በዓሉ ላይ የቤተ መድቅሱን ሕንጻ አሠራርና አፈጻጸም የሚያሳይ አጠቃላይ ሪፖርት በኢንጅነር ሳሙኤል ሀብቴ ቀርቧል። በሪፖርቱ ላይ የካቲት 01 ቀን 2005 ዓ.ም በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመሠረት ድጓጋይ መቀመጡና፣ በወቅቱ ብፁዕነታቸው ሦስት ዘመናዊ የሕንጻ ዲዛይኖችን ከውጪ ሀገር አስመጥተው ለውሳኔ ቀርቦ፣ አሁን በተሰራው ዲዛይን ላይ ነጭ ርግብ መጥታ እንዳረፈችበት በመጥቀስ የአመሠራጥ ሂደቱ በዝርዝር ተገልጿል ።

በማስከተልም በሕንጻ ቤተክርስቲያኑ ግንባታ በገንዘብ፣ በዕውቀትና በጉልበት በማገዝ ሰፊ ድርሻ ለነበራቸው የኮሚቴ አባላትና ምዕመናን የምስጋና ሥጦታ ተበርክቶላቸዋል ።

በመጨረሻም :- ብፁዕ አቡነ መልከጼድቅ በሰንሰለታማ ተራራሮች ላይ ተከቦ የሚገኘው የወለቴ ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ለአከባቢው ግርማ ሞገስ ሁኖ የሚታይ ነው ሲሉ ደስታቸውን ገልጸው፤ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጥተው መርሐግብሩ ተጠናቋል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: “ዝክረ ወንጌል ወዝክረ ሊቃውንት”በሚል መሪ ቃል በስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ከትምህርትና ማሰልጠኛ መምሪያ ጋር በመሆን ያዘጋጀው የሁለት ቀናት የምክክር ጉባኤ የአቋም መግለጫ አውጥቷል የአቋም መግለጫው ሙሉ ቃል Link to: “ዝክረ ወንጌል ወዝክረ ሊቃውንት”በሚል መሪ ቃል በስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ከትምህርትና ማሰልጠኛ መምሪያ ጋር በመሆን ያዘጋጀው የሁለት ቀናት የምክክር ጉባኤ የአቋም መግለጫ አውጥቷል የአቋም መግለጫው ሙሉ ቃል “ዝክረ ወንጌል ወዝክረ ሊቃውንት”በሚል መሪ... Link to: የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት የሚገኘውን ቤተ መጻሕፍት ወመዘክርን ገበኙ። Link to: የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት የሚገኘውን ቤተ መጻሕፍት ወመዘክርን ገበኙ። የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top