ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት አዲስ ለማሰራው ህንፃ ቤተ ክርስቲያን ባርከው የመሠረተ ደንጊያ አኖሩ።
ቅዱስነታቸው ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና ከድሬዳዋ ከንቲባ ከአቶ ከድር ጁሀር ጋር በመሆን በድሬዳዋ ከተማ እንዱስትሪ መንደር አዲስ ለሚሰራው የመካነ ሰማእት ቅዱስ እስጢፋኖስ፣ወልደታ ለማርያምና ወአቡነ ሳሙኤል ህንፃ ቤተ ክርስቲያን የመሠረተ ደንጊያ አኑረዋል፣
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ፤
ሐምሌ ፲፯ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም አዲስ አበባ
በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት የ፲ ዓመት ስልታዊ እቅድ ዙሪያ ለሁለት ቀናት የተካሄደው የምክክር ጉባኤ ተጠናቀቀ::
ከሐምሌ ፲፬-፲፭ ቀን ፳፻፲፭ ዓ ም ለሁለት ቀናት በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት የጉባኤ አዳራሽ በሀገረ ስብከትቦቱ የ፲ ዓመት ስልታዊ እቅድ ዙሪያ የተካሄደው የምክክር ጉባኤ መጠናቀቀ።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም ወቅታዊ የቤተክርስቲያንን ሁኔታ አስመልክቶ የሰላም ጥሪ አተስላለፉ።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወቅታዊ የቤተክርስቲያናችንን ሁኔታ አስመልክቶ ዛሬ ሐምሌ ፲፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም ከቀትር በኋላ በጽ/ቤታቸው ልዩ መግለጫ ተሰጥተዋል።
አዲስ ለሚሾሙት ኤጲስ ቆጶሳት የጸሎተ አስኬማ ሥነሥርዓት ተከናወነ።
በዛሬው ዕለት በተፈጸመው ጸሎተ አስኬማ ለሥርዓቱ የተሠራው ጸሎት በቅዱስነታቸው መሪነት ከደረሰ በኋላ ቡራኬ የተሰጠበትን ቅናተ ዮሐንስ ቅዱስነታቸው ለተሿሚ ቆሞሳት አስታጥቀዋል።
የኮሎራዶና አካባቢው ሀገረ ስብከት አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በዛሬው ዕለት መካሔድ ጀመረ።
በሰሜን አሜሪካን የኮሎራዶና አካባቢው ሀገረ ስብከት አምስተኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዛሬ ሐምሌ ፯ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም በኦምሐ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን መካሔድ ጀመረ።
ቅዱስ ሲኖዶስ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲያደርግ የነበረውን አስቸኳይ ጉባኤ በማጠናቀቅ መግለጫ ሰጠ።
በክልል ትግራይ በተካሄደው ጦርነት በቤተ ክርስቲያናችን የበላይ መዋቅርና በክልል ትግራይ አህጉረ ስብከት መካከል የነበረው አስተዳደራዊ መዋቅር ተቋርጦ መቆየቱን ተከትሎ የተፈጠረው አለመግባባት በውይይት ተፈቶ መዋቅራዊ አንድነታችን በድጋሚ ተጠናክሮ እንዲቀጠል ሀገራዊ የሰላም እርቁ ከተፈጸመበት ማግስት ጀምሮ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ፊርማ በተደጋጋሚ በደብዳቤ ሲጠየቅ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልአተ ጉባኤ ተጠራ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ እና በአዲስ አበባ አቅራቢያ ያሉ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ለዛሬ ሐምሌ ፭ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት በቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ ለአስቸኳይ የምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ እንዲገኙ ጥሪውን አስተላልፏል።
ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁን በተመለከተ በትግራይ ተፈናቃዮች የተደረገው መሰረተ ቢስ ውንጀላ ፍፁም ከእውነት የራቀ ነው።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም ወደ አሥመራ ተጉዘው ከፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ጋር የተገናኙት ሁሉም ኢትዮጵያዊ በኤርትራና በኢትዩጵያ ስምምነት በተደሰተበት ማግስት የተፈጠረውን ሰላምና ዕርቅ እውቅና ለመስጠት በተደረገ ሥነሥርዓት ላይ ለመገኘት የአማራ ክልል ልዑክ በመሆን መጓዛቸው በቀጥታም ህነ በተዘዋዋሪ ከትግራይ ጦርነት ጋር ግንኙነት የለውም።
ቅዱስነታቸው በትግራይ የሚገኙ አባቶች ችግሩን በጠረጴዛ ዙሪያ በሚደረግ ውይይት እንዲፈቱ ጥሪ አቀረቡ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በክልል ትግራይ በጦርነቱ ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች ርዳታ ለመስጠትና በትግራይ ከሚገኙ አባቶች ጋር የተፈጠረው ችግር በውይይት ለመፍታት ዛሬ ፣ ሐምሌ ፫ቀን ፳፻ ፲ወ፭ዓ.ም ማለዳ መቐለ ከተማ ገብተዋል።