ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች

በባህርዳር የተገነባው ባለ ፮ ወለል ሁለ ገብ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ተመረቀ።

የባሕር ዳር ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል ገዳም ያስገነባው ባለ ስድስት ወለል ሁለ ገብ ሕንፃ በብፁዕ አቡነ አብርሃም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዛሬ ግግቦት ፳ ቀን ፳ ፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ተመርቋል።

የግንቦት ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የርክበ ካህናት ጉባኤ ባለ ፲ ነጥብ መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ።

ቅዱስ ሲኖዶስ ከግንቦት ፩ ቀን ፳፻ ፲ወ ፭ዓ.ም አስከ ግንቦት ፲፭ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ድርስ በ ፲፰ አጀንዳዎች ዙሪያ የርክበ ካህናት ጉባኤውን ሲያካሒድ ከቆየ በኋላ ዛሬ ግንቦት ፲፮ ቀን ፳፻ ፲ወ ፭ዓ.ም ፲ ነጦቦችን የያዘ መግለጫ በማውጣት ጉባኤውን አጠናቋል።

ቅዱስ ሲኖዶስ በ፯ኛ ቀን ውሎው በአራት አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ አሳለፈ።

ቅዱስ ሲኖዶስ ግንቦት ፱ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ባካሄደው ውይይት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ትምህርቷን ለትውልዱ የታስተምርበት ተቋማት አንዱ መንፈሳዊ ኮሌጆች መሆነቸውን አውስቷል፡፡ እነዚህ ኮሌጆች ወጥ የሆነ ሕግ ሳይኖራቸው የቆየ ሲሆን በቅርቡም በሐዋሳ እና በወልቂጤ የተቋቋሙት ኮሌጆች ባቀረቡት መተዳደሪያ ደንብ መሠረት፤ ቅዱስ ሲኖዶስ ውይይት አድርጎ ለሁሉም መንፈሳዊ ኮሌጆች የሚያገለግል ወጥ የሚሆን ሕግ አዘጋጅቶ ማጽደቁን ብፁዕነታቸው ገልጸዋል፡፡

የ2015 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት የሁለተኛው ቀን ውሎን አስመልክቶ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባባቢዋ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ማብራሪያ ሰጡ።

ቅዱስ ሲኖዶስ በ2ኛ ቀን ውሎው የተከፋፈለ ሲኖዶስ እንደሌለ እና ከዚህ ሐሳብ ውጪ የሆነ አካል ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕግና ሥርዓት ውጪ የሆነ መሆኑን በመግለጽ መንግሥትን የሚያነጋግሩ ልዑካን ሰይሟል። በቅዱስ ሲኖዶስ በትግራይ ያሉ አባቶችና አባላቱን በአካል የሚያነጋግሩ ብፁዓን አባቶች ተመርጠው ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል።

የቅዱስ ፓትርያርኩ የግንቦት ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ርክበ ካህናት ጉባኤ መክፈቻ ንግግር ሙሉ ቃል

የሰላም አለቃ፣የምሕረት አባት የሆነው ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅድስት የሆነችውን በዓለ ትንሣኤውን አክብረን ይህንን የረክበ ካህናት ቀኖናዊና ሲኖዶሳዊ ጉባኤ እንድናካሂድ ስለሰበሰበን ክብርና ምስጋና፣ አምልኮና ውዳሴ ለእሱ በማቅረብ፣እንኳን ደኅና መጣችሁ ለማለት እንወዳለን፡፡

በጠቅላይ ቤተክህነት እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ ሁለገብ አዳራሽ የግንባታ ሥራው ፹፯ ፐርሰንት መድረሱ ተገለጸ።

በሥልጠናው መዝጊያ ላይ የተገኙት ብጹዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በህዝብ ግንኘነት አስፈላጊነትና ለቤተክርስቲያን ያለውን ፋይዳ በዝርዝር ገልጸው ቤተክርስቲያን በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን በህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ዘመኑን የዋጀና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ሥራ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

ቅዱስ ፓትርያርኩ የመድኃኔዓለም በዓልን በምስካየ ኀዙናን መድኃኔዓለም ገዳም አከበሩ

በሥልጠናው መዝጊያ ላይ የተገኙት ብጹዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በህዝብ ግንኘነት አስፈላጊነትና ለቤተክርስቲያን ያለውን ፋይዳ በዝርዝር ገልጸው ቤተክርስቲያን በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን በህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ዘመኑን የዋጀና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ሥራ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

ለሁለት ቀናት ሲሰጥ የነበረው የህዝብ ግንኙነት የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተጠናቀቀ።

በሥልጠናው መዝጊያ ላይ የተገኙት ብጹዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በህዝብ ግንኘነት አስፈላጊነትና ለቤተክርስቲያን ያለውን ፋይዳ በዝርዝር ገልጸው ቤተክርስቲያን በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን በህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ዘመኑን የዋጀና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ሥራ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዓለ ንግስ ቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በታላቅ መንፈሳዊ ሥነሥርዓት ተከብሮ  ዋለ።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖትና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዓለ ንግሥ በአዲስ አበባ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ዛሬ ሚያዝያ ፳፫ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ,ም በከፍተኛ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ተከበረ ።

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ “አሜን ኢትዮጵያ” የተሰኘ የበጎ አድራጎት ድርጅት ባተዘጋጀ መርሐ ግብር ላይ ተገኝተው የሰላም መልእክት አስተላለፉ ።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና ከሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ጋር በመሆን በሰበታ ጌተሴማኒ ገዳም በመገኘት የ፳፻ ፲ወ፭ዓ,ም የትንሣኤ በዓልን አከበሩ።

በፌስቡክ ያግኙን

የኅትመትና ሚዲያ ዋና ክፍል

ብፁዕ አቡነ አብርሃም

የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ

በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ

ለውስጥ አገልግሎት

የኢሜይል አገልግሎት

ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን

ርእይ

ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት

ተልእኮ

  • የእግዚአብሔርን ቃል ለሰው ልጆች ሁሉ ማስተማርና ማዳረስ

  • ሰውን በሁለንተናዊ ሰብእናው ማገልገልና ማዳን

  • ሰውን ሁሉ በነገረ መለኮትና በነገረ ጥበብ ትምህርት በማልማት በመንፈሳዊም ሆነ በሥጋዊ ሕይወቱ የተሻለ ኑሮ እንዲኖረው ማድረግ

  • ጥራትና ብቃት፣ ፍትሐዊነትና እኩል ተደራሽነት ያለው መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ለሰው ሁሉ ማበርከት

  • የተለያዩ የልማት መርሀ ግብሮችን በመንደፍ ቤተ ክርስቲያንን በኢኮኖሚ ማበልጸግ

  • በቴክኖሎጂ ስልት የሚመራና አዋጭነቱ አስተማማኝ የሆነ የጠቅላላ ሀብት አስተዳደርና አጠቃቀም እንዲረጋገጥ ማድረግ

  • የሰው ልጆች ሁሉ እኩልነት፣ ሰላምና ፍትሕ፣ ፍቅርና ስምምነት እንዲጠበቅ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ

  • የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አሰራር ግልጽ፣ ለሁሉም ተደራሽና ችግር ፈቺ እንዲሆን ማድረግ

ዕሴቶች

  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅሊናን የሚረታ፣ አእምሮን የሚመሥጥ፣ ከጥንተ ፍጥረት ተነሥቶ በዘመነ አበው በሕገ ልቡና፣ በዘመነ ብሉይ በሕግ ኦሪት፣ ተራምዶ መዳረሻውን ሕገ ወንጌል ያደረገ ጥንታዊ ክርስቶሳዊና ሐዋርያዊ ትምህርተ ሃይማኖት፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን፣ በያሬዳዊ ጣዕመ ዜማ የታጀበ ሥርዐተ አምልኮ፣ በጽሑፍና በትውልድ ቅብብሎሽ የተወረሰ የረጅም ጊዜ ትውፊት ባህልና ታሪክ

  • በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የበለጸገ፣ እግዚአብሔርን የሚወድና የሚፈራ ለእግዚአብሔር የሚታዘዝና ምክረ ካህን የሚቀበል ከስልሳ ሚልዮን በላይ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ

  • ለምጣኔ ሃብት ዕድገት እጅግ የምትጠቅም በውብ ሥነ ተፈጥሮና በሥነ ጽሑፍ፣ በሥነ ጥበብና በኪነ ጥበብ፣ በታሪክና በቅርስ ሃብት የበለጸገች እንዲሁም በሃይማኖት፣ በነጻነትና በአንድነት የደመቀች ሃገር

  • የእግዚአብሔርን ቃል ከሃገር ውስጥ ባሻገር ለመላው ዓለም ማዳረስ የሚችሉ ከግማሽ ሚልዮን ያላነሱ ሊቃውንት፣ ቀሳውስት፣ ዲያቆናት፣ ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ከሁለት ሺሕ ያላነሱ ገዳማት

  • መላውን ዓለም እያዳረሰና እየሰፋ የሚገኝ ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ የተዋቀረ ጠንካራ መዋቅር ያላት መሆኗ

ያግኙን

+251 111 55 0098 P.O.Box 1283 A.A. 5 KILLO, ADDIS ABABA, ETHIOPIA በፌስቡክ ያግኙን የዩትዩብ ቻነል