የቦታው ስም ቀራንዮ ነው
የ2018 ዓ.ም. መስቀል በዓል ልዩ እትም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በሊቃውንት ጉባኤ ታይቶና ተመርምሮ፤ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተዘጋጀ
የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
ሀገረ ስብከት በወቅታዊ የቤተክርስቲይን ወቅታው ጉዳይ የተሰጠ መግለጫ
ሰበር ዜና
ከቀኖናና ከህግ ውጪ በተደረገው ሲመት ከተሾሙት መካከል መጋቤ ብሉይ ወሐዲስ ቆሞስ አባ ጸጋዘአብ አዱኛ በዚህ ሰዓት ቤተክርስቲያንን ይቅርታ ለመጠየቅ ቅደለስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት ተገኝተው ለብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዶ/ር የይቅርታ ደብዳቤ አስገብተዋል።
አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ መልዕክት
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒዩወርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመላው ዓለም ለሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳሳት ባስተላሐፉት መልዕክት እንደገለጹት በየትኛውም የዓለማችን ክፍል የሚገኙ አበው ሊቃነ ጳጳሳት በቤተክርስቲያናችን ላይ በተፈጸመው የቀኖና ጥሰትና ህገ ወጥ ድርጊት ዙሪያ ለመወያየት በየትኛውም የዓለማችን ክፍል የሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ወደ አገራቸው እንዲገቡ ጥሪ መተላለፉን አስታውሰው በአየር ትራንስፖርቱ ዘርፍ በጉዞአቸው ላይ ችግር እንዳይገጥማቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቅድሚያ እንዲሰጣቸው ከቤቸክርስቲያናችን በቀረቀው ጥሪ መሰረት አየር መንገዱ ፍጹም ፈቃደኛና ተባባሪ መሆኑን አረጋግጧል ብለዋል።
ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የተላለፈ መልእክት
ብፁዕ አቡነ አብርሃም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ይህን የገለጹት በዛሬው ዕለት ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጪ የተፈጸመውን “የጳጳስ ሹመት” አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ ነው።
የጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ጉባኤ ሃይማኖታዊ ክህደት ፣ ቀኖናዊ ጥሰት እናአስተዳደራዊ ግድፈት የታየበትን የወሊሶውን “ሹመት” አወገዘ ቅዱስ ሲኖዶስ ተገቢውን ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ ምዕመናን በጸሎት እንዲቆዩ አሳሰበ
ከዚህ ጋር በተያያዘም ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ምዕመናንና ምዕመናት ከጸሎት በተጨማሪ መዋቅራዊ መመሪያዎችን በትዕግስት እንዲጠብቁ አደራ በማለት የእለቱን ስብሰባ በጸሎት አጠናቋል።
የጥምቀት በዓልን በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተክርስቲያን
የ2015 ዓ/ም የከተራ እና የጥምቀት በዓልን በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ለማክበር ዓርብ ምሽት የተጓዙት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ እና የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ቆይታቸውን በመግታት ወደ አዲስ አበባ ገቡ።
“ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በደረሰባት የውስጥ ፈተና ሀዘኗ ከባድ ነው።” ብፁዕ አቡነ አብርሃም
ብፁዕ አቡነ አብርሃም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ይህን የገለጹት በዛሬው ዕለት ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጪ የተፈጸመውን “የጳጳስ ሹመት” አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ ነው።
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መግለጫ ተሰጠ
መግለጫውን የሠጡት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፖትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት; ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ : በመንበረ ፓትርያርክ የተገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ናቸው።
በበረዶዋማ ፊንላንድ አገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የጥምቀት በዓልን በድምቀት አከበሩ።
የስዊድን፣ ስካንዲናቪያንና የግሪክ ሀገሮች ሀገረ ስብከት በፊንላንድ ሄልሲንኪ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን፣ ዛሬ ጥር 13 ቀን 2015 ዓ.ም የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሰሱ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በርካታ ምእመናን በተገኘበት በድምቀት ተከሯል።
የጋምቤላ የጥምቀት በዓል አከባበር
የጋምቤላ የጥምቀት በዓል አከባበር ዛሬም ቀጥሏል እስከ ሰኞ ጥር 15 ይቀጥላል።