የቦታው ስም ቀራንዮ ነው
የ2018 ዓ.ም. መስቀል በዓል ልዩ እትም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በሊቃውንት ጉባኤ ታይቶና ተመርምሮ፤ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተዘጋጀ
የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
በሰሜን አሜሪካን የሚገኘው ዳግማዊ ደብረ ሊባኖስ ቅዱስ ያሬድና አቡነ ፊሊጶስ ገዳምና የአብነት ትምህርት ቤት ከስልሳ በላይ ታዳጊ ወጣቶችን በመንፈሳዊ የትምህርት ዘርፍ እያሰለጠነ ነው።
በሰሜን አሜሪካን ቨርጂኒያ ግዛት ኪንግ ጆርጅ ካውንቲ የሚገኘው ዳግማዊ ደብረ ሊባኖስ ቅዱስ ያሬድና አቡነ ፊሊጶስ ገዳም አንድ መቶ ሃያ ተማሪዎችን በሁለት ዙር በመቀበል በልዩልዩ መንፈሳዊ ትምህርት ዘርፎች ማስተማር ጀመረ።
የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ/ም የስብከተ ወንጌል እና የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ የጋራ የአገልግሎት ሥምሪት ሥልጠና ተከናወነ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያና የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ በጋራ የሚያስተባብሩት በስብከተ ወንጌል ማስፋፋትና በሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አደረጃጀት ዙሪያ በ፵፰ አህጉረ ስብከት ሥልጠና ለመሥጠት ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለጸ።
ወቅታዊ መልዕክት
በአንዳንድ ማኅበራዊ ገጾች እየተዘዋወረ የሚገኘው እና በብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ስም ተፈርሞ እንደወጣ በማስመሰል የተለቀቀው ከዚህ በታች የሚታየው ደብዳቤ ፍጹም የሐሰትና ሆን ተብሎ ተቀነባብሮ በፎርጅድ ተሰርቶ የተለጠፈ መሆኑን እንገልጻለን።
በክልል ትግራይ ካሉ ብፁዓን አባቶች ጋር የተፈጠረውን ችግር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመፍታት እየተሠራ እንደሆነ የሰላም ልዑኩ ገለጸ ።
የጠቅላይ ቤተክህነት ልዑካን ቡድን ውይይቱን ውጤታማ ለማድረግ ይቻል ዘንድ እስከ አሁን ያከናወናቸውን ተግባራትና ወደፊት ውይይቱን ስኬታማ በሆነ መንገድ ማካሔድ በሚችልበት ሁኔታ ዙሪያ ሰኞ ሰኔ ፭ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ይፋዊ መግለጫ ይሰጣል።
በትግራይ ክልል ከሚገኙ አባቶች ጋር ውይይት ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተጠናቀቀ።
የጠቅላይ ቤተክህነት ልዑካን ቡድን ውይይቱን ውጤታማ ለማድረግ ይቻል ዘንድ እስከ አሁን ያከናወናቸውን ተግባራትና ወደፊት ውይይቱን ስኬታማ በሆነ መንገድ ማካሔድ በሚችልበት ሁኔታ ዙሪያ ሰኞ ሰኔ ፭ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ይፋዊ መግለጫ ይሰጣል።
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበ በአቡዳቢ ደብረ ሰላም መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያንበዓለ ጰራቅሊጦስ ተከበረ።
በዓለ ጰራቅሊጦስ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በአቡዳቢ ደብረ ሰላም መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ውሏል።
ወቅታዊ መልዕክት ለምዕመናን
የደብረ ኤልያስ ብሔረ ብፁዓን መልክዓ ሥላሴ አንድነት ገዳምን በተመለከተ በበርካታ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችና የመገናኛ አውታሮች ልዩ ልዩ ዘገባዎች እየተላለፉ ይገኛሉ።
ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁን በተመለከተ በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የሚዘዋወረው ዘገባ ከእውነት የራቀ ነው።
ሰሞኑን በአንዳንድ ማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህርዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስን በማስመልከት የሚሰራጩት ዜናዎች ፍጹም ከእውነት የራቁና ሕዝበ ክርስቲያኑን ለማደናገር የሚነዙ ሐሰተኛ ዘገባዎች ናቸው።
በባህርዳር የተገነባው ባለ ፮ ወለል ሁለ ገብ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ተመረቀ።
የባሕር ዳር ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል ገዳም ያስገነባው ባለ ስድስት ወለል ሁለ ገብ ሕንፃ በብፁዕ አቡነ አብርሃም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዛሬ ግግቦት ፳ ቀን ፳ ፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ተመርቋል።
የግንቦት ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የርክበ ካህናት ጉባኤ ባለ ፲ ነጥብ መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ።
ቅዱስ ሲኖዶስ ከግንቦት ፩ ቀን ፳፻ ፲ወ ፭ዓ.ም አስከ ግንቦት ፲፭ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ድርስ በ ፲፰ አጀንዳዎች ዙሪያ የርክበ ካህናት ጉባኤውን ሲያካሒድ ከቆየ በኋላ ዛሬ ግንቦት ፲፮ ቀን ፳፻ ፲ወ ፭ዓ.ም ፲ ነጦቦችን የያዘ መግለጫ በማውጣት ጉባኤውን አጠናቋል።