የቦታው ስም ቀራንዮ ነው
የ2018 ዓ.ም. መስቀል በዓል ልዩ እትም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በሊቃውንት ጉባኤ ታይቶና ተመርምሮ፤ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተዘጋጀ
የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት የ፲ ዓመት ስልታዊ እቅድ ዙሪያ ለሁለት ቀናት የተካሄደው የምክክር ጉባኤ ተጠናቀቀ::
ከሐምሌ ፲፬-፲፭ ቀን ፳፻፲፭ ዓ ም ለሁለት ቀናት በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት የጉባኤ አዳራሽ በሀገረ ስብከትቦቱ የ፲ ዓመት ስልታዊ እቅድ ዙሪያ የተካሄደው የምክክር ጉባኤ መጠናቀቀ።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም ወቅታዊ የቤተክርስቲያንን ሁኔታ አስመልክቶ የሰላም ጥሪ አተስላለፉ።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወቅታዊ የቤተክርስቲያናችንን ሁኔታ አስመልክቶ ዛሬ ሐምሌ ፲፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም ከቀትር በኋላ በጽ/ቤታቸው ልዩ መግለጫ ተሰጥተዋል።
አዲስ ለሚሾሙት ኤጲስ ቆጶሳት የጸሎተ አስኬማ ሥነሥርዓት ተከናወነ።
በዛሬው ዕለት በተፈጸመው ጸሎተ አስኬማ ለሥርዓቱ የተሠራው ጸሎት በቅዱስነታቸው መሪነት ከደረሰ በኋላ ቡራኬ የተሰጠበትን ቅናተ ዮሐንስ ቅዱስነታቸው ለተሿሚ ቆሞሳት አስታጥቀዋል።
የኮሎራዶና አካባቢው ሀገረ ስብከት አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በዛሬው ዕለት መካሔድ ጀመረ።
በሰሜን አሜሪካን የኮሎራዶና አካባቢው ሀገረ ስብከት አምስተኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዛሬ ሐምሌ ፯ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም በኦምሐ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን መካሔድ ጀመረ።
ቅዱስ ሲኖዶስ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲያደርግ የነበረውን አስቸኳይ ጉባኤ በማጠናቀቅ መግለጫ ሰጠ።
በክልል ትግራይ በተካሄደው ጦርነት በቤተ ክርስቲያናችን የበላይ መዋቅርና በክልል ትግራይ አህጉረ ስብከት መካከል የነበረው አስተዳደራዊ መዋቅር ተቋርጦ መቆየቱን ተከትሎ የተፈጠረው አለመግባባት በውይይት ተፈቶ መዋቅራዊ አንድነታችን በድጋሚ ተጠናክሮ እንዲቀጠል ሀገራዊ የሰላም እርቁ ከተፈጸመበት ማግስት ጀምሮ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ፊርማ በተደጋጋሚ በደብዳቤ ሲጠየቅ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልአተ ጉባኤ ተጠራ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ እና በአዲስ አበባ አቅራቢያ ያሉ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ለዛሬ ሐምሌ ፭ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት በቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ ለአስቸኳይ የምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ እንዲገኙ ጥሪውን አስተላልፏል።
ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁን በተመለከተ በትግራይ ተፈናቃዮች የተደረገው መሰረተ ቢስ ውንጀላ ፍፁም ከእውነት የራቀ ነው።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም ወደ አሥመራ ተጉዘው ከፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ጋር የተገናኙት ሁሉም ኢትዮጵያዊ በኤርትራና በኢትዩጵያ ስምምነት በተደሰተበት ማግስት የተፈጠረውን ሰላምና ዕርቅ እውቅና ለመስጠት በተደረገ ሥነሥርዓት ላይ ለመገኘት የአማራ ክልል ልዑክ በመሆን መጓዛቸው በቀጥታም ህነ በተዘዋዋሪ ከትግራይ ጦርነት ጋር ግንኙነት የለውም።
ቅዱስነታቸው በትግራይ የሚገኙ አባቶች ችግሩን በጠረጴዛ ዙሪያ በሚደረግ ውይይት እንዲፈቱ ጥሪ አቀረቡ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በክልል ትግራይ በጦርነቱ ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች ርዳታ ለመስጠትና በትግራይ ከሚገኙ አባቶች ጋር የተፈጠረው ችግር በውይይት ለመፍታት ዛሬ ፣ ሐምሌ ፫ቀን ፳፻ ፲ወ፭ዓ.ም ማለዳ መቐለ ከተማ ገብተዋል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለትግራይ ክልል የ20 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገች
(ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለትግራይ ክልል የ፳ ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገች፡፡በድጋፍ ርክክብ መርሐ ግብሩ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ፣ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት እና ልዑካን ቡድኑ ተገኝተዋል፡፡
በቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራ ልዑካን ቡድን ወደ ክልል ትግራይ ርዕሰ ከተማ መቐለ ተጓዘ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ለክልል ትግራይ የሰብዐዊ ድጋፍ እንዲደረግና ቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በትግራይ ክልል ከሚገኙ አባቶች ጋር ውይይት እንዲደረጉ ውሳኔ አስተላልፏል።