የቦታው ስም ቀራንዮ ነው
የ2018 ዓ.ም. መስቀል በዓል ልዩ እትም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በሊቃውንት ጉባኤ ታይቶና ተመርምሮ፤ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተዘጋጀ
የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
ቅዱስ ሲኖዶስ መጋቢት ፳፩ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ምልአተ ጉባኤ እንዲካሄድ ጥሪ ተላለፈ
በህገ ወጥ መንገድ የተሾሙት ግለሰቦች በአምስት ቀናት ውስጥ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት መገኘት ሪፖርት እንዲያደርጉ ጥሪ አስተላለፈ።
በምሥራቅ አውሮፖ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ተባርኮ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።
በፖላንድ ዋና ከተማ ዋርሶው ከተማ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ የምሥራቅ ጎጃም፣ የጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተባርኮ አገልግሎት ጀምሯል ።
የመምህር የኔታ ሐረገወይን ምሕረቱ የሽኝት መርሐ ግብር
የመምህር የኔታ ሐረገወይን ምሕረቱ የሽኝት መርሐ ግብር ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣የጠቅላይ ቤተክህነት የምምሪያ ኃላፊዎች የመንግስት ባለሥልጣናት፣የባቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባና ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት በዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ተፈጸመ።
ወላዴ አእላፍ መምህር የኔታ ሐረገ ወይን ምሕረቱ የሕይወት ታሪክ
ወላዴ አእላፍ መምህር የኔታ ሐረገ ወይን ምሕረቱ በወሎ ክፍለ ሀገር ሰገራት (ኩታበር ወደ ግሸን መሔጃ) ከወላጅ አባታቸው ከአለቃ ምሕረቱ ካሣ ከእናታቸወ ወ/ሮ አበቡ ወልደ ጻድቅ በየካቲት 16 ቀን 1916 ዓ.ም ተወለዱ። የፊደልና ንባብ ትምህርት የጀመሩት በእናታቸው ሀገር በቦሩ ሥላሴ ነው።
ፍርድ ቤቱ የሕገወጥ ቡድኑን መቃወሚያዎች ሙሉ በሙሉ ውድቅ በማድረግ ቤተ ክርስቲያን ከጠየቀችው ዘጠና ቀናት ውስጥ የ፵፭ ቀናት የእግድ ትዕዛዝ ወሰነ።
የካቲት ፴/፳፻፲፭ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
በቦረና በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ የማሰባሰብ እንቅስቃሴውን የሚያስተባብሩ በብፁዓን አባቶች የሚመራ አምስት አባላት ያሉት ዐቢይ ኮሚቴ ተመደበ፤
. . . በሦስት ብፁዓን አባቶች እና በሁለት የጠቅላይ ቤተክህነት የሥራ ኃላፊዎች የሚመራ ዐቢይ ኮሚቴ እንዲዋቀርና ወደ ሥራ እንዲገባ ያስተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ውሳኔውን እንዲያስፈጽም ኃላፊነት ሰጥቷል።
የጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ጉባኤ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/መገናኛ ብዙሃን ሥርጭት ድርጅትና የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በሰው ሃይል እንዲጠናከሩ ወሰነ።
. . . በቀጣይ ጊዜ በሁለቱ ተቋማት በጥምረትና በተናጠል መሰራት ያለባቸው ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎችን ጉባኤው ያመላከተ ሲሆን በተለይም መረጃዎችን የማሰባሰብ፣ወቅታዊ ምላሽ የመስጠትና በየዕለቱ የዜና ሽፋን የመስጠት ጉዳይ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራ አቅጣጫ አስቀምጧል።
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፬ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፩ኛ ዓመት መታሰቢያ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከናወነ።
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ፬ኛ ዓመታ መታሰቢያ በመንበረ ጸባዖት ቅድስ ስላሴ ካቴድራል ብፁዕአን ሊቃነ ጳጳሳት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የሥራ ኃላፊዎች፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ሊቃውተ ቤተክርስቲያን ወዳጆቻቸው እና የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል።
የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ፲ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ።
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፲ኛ ዓመት በዓሉ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በታላቅ ሥነሥርዓት ተከብሮ ውሏል።በበዓሉ ላይ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ቴጉሃን ታጋይ ታደለ የጠቅላይ ቤተክህነት የመምሪያና የድርጅትኃላፊዎች፣የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ተገኝተዋል።
የቅዱስነታቸውን ፲ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በማስመልከት የተዘጋጀው “ዜና መዋዕል ዘብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክና ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ መጻህፍት በዛሬው ዕለት ተመረቀ።
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖትን ፲ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በማስመልከት በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት በተቋቋመው የሥነ ጽሑፍ ዝግጅት ኮሚቴ ተዘጋጅቶና በሊቃውንት ጉባኤ ተመርምሮ የተዘጋጀውና ለህትመት የበቃው ዜና መዋዕል ዘብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ መጽሐፍና የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ቃለ በረከት መጽሐፍ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ሚኒስትሮች ፣አምባሳደሮች፣የጠቅላይ ቤተክህነት የመምሪያና የድርጅት ኃላፊዎች፣የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ኃላፊዎች፣የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፣የወጣት ማኅበራት ተወካዮችና የክብር እንግዶች በተገኙበት ዛሬ የካቲት ፳፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ተመርቋል።