የቤተክርስቲያናችን የሕግ ባለሙያዎች ኮሚቴ አባል ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ አያሌው ቢታኔ ታሠሩ ።

ታኅሳስ ፱ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
“””””””””””””””””””””””””””
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ

ጠበቃ እና የህግ አማካሪ አያሌው ቢታኔ የዕለት ችሎት ተከራርክሮ ከፍርድ ቤት ወጥቶ ከባለቤቱ እና ከእህቱ ጋር ሜክሲኮ በሚገኘው ነዳጅ ማደያ ለመኪናው ነዳጅ በመቅዳት ላይ ሳለ ሲከታተሉት በነበሩ በመንግስት የጸጥታ አካላት ተወስዶ የታሠረ መሆኑ ታወቀ።

ጠበቃ አያሌው ቢታኔ በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በተቋቋመው የሕግ ባለሙያዎች ኮሚቴን በመምራት ሙያዊ ግዴታቸውን በመወጣት ቤተክርስቲያንን ወክለው የሕግ አገልግሎት ሲያበረክቱ ቆይተዋል። በተለይም በቤተክርስቲያናችን ተከስቶ በነበረው ሕገ ወጥ ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳት ተከትሎ ሃይማኖታዊ ግዴታቸውን በመፈጸማቸው በተለያዩ ምክንያቶች ከሥራቸው ለተፈናቀሉ ምእመናን በነጻ የሕግ ማማከርና ጥብቅና አገልግሎት በመሥጠት ከፍተኛ አገልግሎት አበርክተዋል።

በተጨማሪም በቅዱስ ሲኖዶስ በሚወጡ ሕጎችና መመሪያዎችን በማርቀቅ ሰፊ አገልግሎት አበርክተዋል።
Š EOTC TV

ብፁአን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በመሪ ምሥራቀ ጸሐይ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ተገኝተው የሕንፃ ግንባታው ሒደት ጎበኙ።

ታኅሣሥ 7 ቀን 2016 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ የባሕር ዳርና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ጸሓፊና የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት እና የደቡብ ኦሞ ጅንካ ፣ የአሪ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ብፁዕ አቡነ ሰላማ የምዕራብ ጎንደር ሊቀ ጳጳስ እንዲሁም መልአከ ምሕረት ዘካርያስ ሐዲስ የየካና ለሚ ኩራ ክፍላተ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ በመሪ ምሥራቀ ጸሐይ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ተገኝተው የሕንፃ ግንባታው ሒደት ጎብኝተው መንፈሳዊ አገልግሎት ሰጥተዋል።

ብፁዕ አቡነ አብርሃም በእስራኤል የነበራቸውን ሐዋርያዊ አገልግሎት አጠናቀው ወደ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ተመለሱ።

የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ለሚያስገነባው ባለ ዐስራ ሁለት ወለል ሕንጻ ገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ኅዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም በግራንድ ኤልያና ሆቴል አካሂዷል።

ማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ባከናወነው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ከ7.5 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ለሚያስገነባው ባለ ዐስራ ሁለት ወለል ሕንጻ ገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ኅዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም በግራንድ ኤልያና ሆቴል አካሂዷል።

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከእስራኤል የቱሪዝም ሚንስትር ጋር ተወያዩ፤የእስራኤል ሙዝየምንም ጎበኙ።

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በቅድስት አገር ኢየሩሳሌም የሚያደርጉትን ሐዋርያዊ አገልግሎት ቀጥለዋል።

በወቅታዊ ጉዳዮች ከቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

“ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ፥ ወይስ ጭንቀት፥ ወይስ ስደት፥ ወይስ ራብ፥ ወይስ ራቁትነት፥ ወይስ ፍርሃት፥ ወይስ ሰይፍ ነውን? ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን፥ እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን” ሮሜ 8፡35-36

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የሐዋርያዊ አገልግሎት መዳረሻቸው እስራኤል ገብተዋል።

ብፁዕ  አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፥ የባህር ዳርና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ዻዻስ በእስራኤል ቴልአቪቭ ቤንጎርዮን ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ ብፁዕ  አቡነ ዕንባቆም በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት ሊቀ ጳጳስና የገዳማቱ  አበው መነኮሳት ደማቅ አቀባባል አድርገውላቸዋል።

በሲነርጂ ሀበሻ ፊልምና ኮሚኒኬሽን በመዘጋጀት ላይ የሚገኘው የሰማዕቱ ሊቀ ጳጳስ የብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ፊልም ጽሑፍ በሊቃውንት ጉባኤ እንዲመረመር ታዘዘ።

ኅዳር 28 ቀን 2016 ዓ.ም
“””””””””””””””””””””””””
አዲስ አበባ -ኢትዮጵያ
==============

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ሲነርጂ ፊልምና ኮሚኒኬሽን በኢትዮጵያዊው ሰማዕት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሊቀ ጳጳስ የስማዕትነት ተጋድሎ ዙሪያ የሚያጠነጥን ፊልም ለመስራት የሚያደርገው እንቅስቃሴታሪክን የሚያጎድፍ ሆኖ ስለተገኘ ሊቆም እንደሚገባ በመግለጽ ኅዳር 25 ቀን 2016ዓ.ም በቁጥር 1673/2789/2016 በተጻፈ ደብዳቤ መግለጹ ይታወሳል።

ይህንን ተከትሎ የፊልሙ ጸሐፊ እና ዳይሬክተር ሞገስ ታፈሰ ዶ/ር እየተዘጋጀ የሚገኘውን ፊልም ቤተክርስቲያናችን በሊቃውንቶቿ አማካኝነት መርምራ፣ የሚታረም ካለ አርማና የሚቃናውን አቅንታ በምትሰጠን አስተያየትና ማስተካከያ መሠረት ፊልሙን የምንሠራ መሆኑ ታውቆ አስፈላጊው ትብብር ሁሉ ይደረግልን። በማለት በጽሑፍና በአካል ጠቅላይ ቤተ ክህነት በመገኘት በፊልሙ ዝግጅት ዙሪያ ማብራሪያ በመስጠት ለተፈጠረው የመረጃ ክፍተት ይቅርታ ጠይቀዋል።

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም ዶ/ርሞገስ ታፈሰ ያቀረቡትን ይቅርታ በመቀበል በአካልና በጽሑፍ በፊልሙ ጽሑፍ ዝግጅት ዙሪያ መረጃ ከመስጠት ባለፈ በቤተ ክርስቲያናችን በኩል የፊልሙ ጽሑፍ እንዲመረመርላቸውና እርማት በሚያስፈልገው ጉዳይ ዙሪያ እርማት እንዲደረግበት መጠየቃቸው የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህን ተከትሎም የፊልም ጽሑፉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ጉባኤ በሚገባ ተመርምሮና መታረም ያለበት ሁሉ ታርሞ እንዲቀርብ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ መመሪያ የተሰጠ ሲሆን የፊልም ጽሑፉም በሊቃውንት ጉባኤ እየተመረመረ መሆኑ ታውቋል። ሊቃውንት ጉባኤ የፊልሙን ጽሑፍ መመርመሮ ሲያጠናቅቅም ውጤቱን የምንገልጽ ይሆናል።

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ቤት መፍትሔ ሊሰጥባቸው ይገባል ያላቸውን በ13 ነጥቦች የተዘረዘሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በሀገረ ስብከቱ በኩል መፍትሔ እንዲሰጣቸው ውሳኔ አስተላለፈ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጋር ባደረገው ውይይት በሀገረ ስብከቱ በኩል የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በተመለከተ በተደረገው የጋራ ውይይት በሀገረ ስብከቱ የሚስተዋሉትን ዋናዋና ችግሮች መቅረፍ ይቻል ዘንድ በጠቅላይ ቤተክህነት በኩል ተለይተው የሚታወቁት ዋናዋና ነጥቦች ለሀገረ ስብከቱ እንዲደርሰው ተደርጎ መፍትሔ እንዲሰጥበት የአዲስአበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሔኖክ በጉባኤው ወቅት በሰጡት ማጠቃለያ ሀሳብ ላይ በገለጹት መሰረት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ ኅዳር 24ቀን2016ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ ሀገረ ስብከቱ በኩል በአፋጣኝ ምላሽ ሊያገኙ ይገባቸዋል ያላቸውን 13 ነጥቦችን በመለየት ለሀገረ ስብከቱ እንዲደርሰውና ከበዛ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለተጠቀሱት የመልካም አስተዳደር ችግሮች ምላሽ እንዲሰጥና የውሳኔውን መፈጸም አለመፈጸም በተመለከተም ተከታትለው የሚያስፈጽሙ ሦስት የመምሪያ ኃላፊዎችን መድቧል።

በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የተፈጸመውን ግድያ የጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር ጉባኤ አወገዘ።

ኅዳር ፳፭ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ዓ.ም
“””””””””””””””””””””””””””
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ
******
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር ጉባኤ በዛሬው እለት ባደረገው መደበኛ ስብሰባ በምሥራቅ አርሲ አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ላይ የደረሰውን የሞት አደጋ በተመለከተ ኅዳር 24 ቀን 2016ዓ.ም ከሀገረ ስብከቱ በስልክና በደብዳቤ የደረሰውን መረጃ መነሻ በማድረግ ውይይት ካደረገ በኋላ ውሳኔ አስተላልፏል።

ሀገረ ስብከቱ ለጠቅላይ ቤተክህነት ባደረሰው መረጃ በአርሲ ዞን በሹርካ ወረዳ ሶሌ ሚካኤል፣በዲገሎ ማርያም፣ በሮቤ እንደቶ ደብረ ምጥማቅ ማርያም አብያተክርስቲያናት ላይ በተለያዩ ጊዜያት 36 ኦርቶዶክሳዊያን በደረሰባቸው ጥቃት ሕይወታቸውን ማጣታቸውን በሪፖርቱ አሳውቋል።

በተጨማሪም በሶሌ ዲገሉ እና ጢጆ ለቡ በተባሉ ቀበሌዎች 28 ኦርቶዶክሳዊያን ከየቤታቸው ተለቅመው የተገደሉ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥም 7ቱ ሴቶችና 21ዱ ወንዶች መሆናቸው ነተገለጸ ሲሆን በዚህ ጥቃትም እድሜያቸው ከሰባ ዓመት አዛውንት እስከ ሃያ ስምንት ቀን ጨቅላ ሕጻናት የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸው ተገሌጿል።

ከሁለት ቀናት በፊትም በዲገሉ ማርያም ቤተክርስቲያን 5 ኦርቶዶክሳዊያን ከመገደላቸው በተጨማሪ የሦስት ኦርቶዶክሳውያን ቤት መቃጠሉ ታውቋል።በተያያዘም ከዚህ ቀደም በሮቤ አንዲቶ ደብረ ምጥማቅ ማርያም ቤተክርስቲያን በዓለ ማርያምን አክብረው ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ የነበሩ ሦስት ኦርቶዶክሳዊያን ጨለማን ተገን ባደረጉ ነፍሰ ገዳዮች መገደላቸውንም ሀገረ ስብከቱ በላከው በሪፖርት ገልጿል።በማያያዝም በመንግሥት በኩል አጥፊዎች ላይ እርምጃ መወሰድ የተጀመረ መሆኑንም ሀገረ ስብከቱ ገልጿል።

አስተዳደር ጉባኤው በምሦራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ላይ በደረሰው ጥቃትና ሞት በእጅጉ ማዘኑን ገልጾ በዚህ መልኩ በኦርቶዶክሳዊያን ወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው ጥቃትና ሞት አሳዛኝና ድርጊቱም በጽኑ የሚኮነንና የሚወገዝ ተግባር ነው በማለት አውግዞታል።

ይህን የመሰለ በጭካኔ የተሞላ ድርጊትም መቆም የሚችልበት፣ወገኖቻችን ሕገ መንግስታዊ ከለላን በማግኘት በሰላም መኖር የሚችሉበት መንገድ መፈጠር አለበት ያለው አስተዳደር ጉባኤው በጉዳዩ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ ጉዳዩ ከፍ ባለ ደረጃ መታየት የሚገባው መሆኑን በማመን ለቋሚ ሲኖዶስ ቀርቦ ውሳኔ ማግኘት ይችል ዘንድ ለቋሚ ሲኖዶስ ግብዓት የሚሆን ምክረ ሐሳብን አቅርቧል።

አስተዳደር ጉባኤው በተለያዩ ቦታዎች የሚከሰቱ ችግሮችን ተከትሎ አህጉረ ስብከት ለጠቅላይ ቤተክህነቱ ሪፖርት ባደረጉ ጊዜ ጉዳዩን በማየት ውሳኔ የሚያስተላልፍ መሆኑን ገልጾ ሪፖርት ባልተደረገበትና በሚዲያዎች የተነገሩ መልዕክቶችን ብቻ መነሻ በማድረግ ውሳኔ ማስተላለፍ በተቋም ደረጃ ቤተክርስቲያንን የሚጎዳ ስለሆነ አህጉረ ስብከት ችግሮች በገጠሟቸው ጊዜ ሁሉ በፍጥነት ሪፖርት
መላክ ይገባቸዋል ብሏል።