በኮሪደር ልማት ምክንያት ዚተነሳው ዚቀተ ክርስቲያኗ ህንጻ ዚመልሶ ግንባታ ስራ ተጀመሹ

ዚአዲስ አበባ ኚንቲባ አዳነቜ አቀቀ በኮሪደር ልማት ምክንያት ዚተነሳውን ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን ሕንጻ ዚመልሶ ግንባታ ስራ አስጀምሚዋል፡፡

ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን በአዲስ አበባ ኹተማ ዚሚካሔደውን ዚኮሪደር ልማት ተኚትሎ በርካታ ሥራዎቜን በማኹናወን ላይ ትገኛለቜ።

በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ኚሚካሔደው ዚኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ ንብሚትነታ቞ው ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ዹሆኑ ቀቶቜና ሕንጻዎቜ በአራት ኪሎና በፒያሳ አካባቢ እንዲፈርሱ መደሹጋቾው ይታወቃል።

ቀተ ክርስቲያንም በኹተማ አስተዳደሩ ዚሚካሔደው ዚልማት ሥራ ዹአገር ልማት መሆኑን በመገንዘብ ሁኔታዎቜን በቅርበት ዚሚኚታተል ኮሚ቎ በመሰዹም ብስለትና ትዕግስት በተሞላበት አኳኋን ኚመኚታተል ባለፈ ቋሚ ሲኖዶስ በወሰነው ውሳኔ መሠሚት በብፁዕ አቡነ አብርሃም ዹጠቅላይ ቀተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣
ዚባሕር ዳርና ዹሰሜን ጎጃም አህጉሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ ዚሚመራ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና ዚሚመለኚታ቞ው ዚሥራ ኃላፊዎቜ ዚሚገኙበት ዚቀተ ክርስቲያናቜን ልዑክ ኚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ኚንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነቜ አቀቀና ኚሥራ ባልደሚቊቻ቞ው ጋር ተወያይቷል።

በውይይቱም ቀተ ክርስቲያን በኹተማ አስተዳደሩ ዚሚካሔደው ዚልማት ሥራ ዹአገር ልማት መሆኑን ጠንቅቃ እንደምትገነዘብ፣ ለውጀታማነቱም ዚበኩልዋን አስተዋጜኊ እንደምታበሚክት፣ ኹዚሁ ጎን ለጎንም ዚቀተ ክርስቲያን ይዞታዎቜና መብቶቜ በሚኚበሩበት፣ ቀደም ብለው ለቀተክርስቲያናቜን እንዲመለሱ በተደሹጉ ይዞታዎቜ፣በመኚኑ ካርታዎቜና በሌሎቜም ጉዳዮቜ ጭምር ግልጜና ውጀታማ ውይይቶቜ ተደርገዋል።

ኹኹተማ አስተዳደሩ ኚንቲባና ኚሥራ ኃላፊዎቹ ጋር ዹተደሹገውን ውይይትና ውጀቱን መሠሚት በማድሚግም ዹመንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጜሕፈት ቀት አስተዳደር ጉባኀ ዚቀሚበለትን ሪፖርት መነሻ በማድሚግ ውሳኔና ምክሹ ሀሳብ ለቋሚ ሲኖዶስ አቅርቧል።

ቋሚ ሲኖዶስ በተለይም ጜርሐ ምኒልክ ሕንጻን ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል ዚሚታወቀውን ሕንጻን በተመለኹተ ዹኹተማ አስተዳደሩ ሕንጻው እንዳይፈርስ ለማድሚግ ያደሚገውን ጥሚት ቀተክርስቲያን እያደነቀቜ ሕንጻው መፍሚሱ ግድ በመሆኑ ምክንያት ሕንጻው ኚፈሚሰበት ቊታ ብዙም ሳይርቅ በመንገድ ልማቱ ምክንያት ኹሚወሰደው ይዞታ አጠገብ ባለው ቊታ ላይ ዚሕንጻውን ታሪካዊነትና ጥንታዊነትን መሠሚት ባደሚገ አግባብ ዚአካባቢውን ዚመኪና ማቆሚያ ቜግር ሊፈታ ዚሚቜል ዚመኪና ማቆሚያ አገልግሎት መስጫን ባካተተ መልኩ በራሱ ወጪ በአንድ ዓመት ውስጥ ገንብቶ ለማስሚኚብ ዚገባውን ቃል በመቀበልና በማጜደቅ ለኹተማ አስተዳደሩ በደብዳቀ እንዲገለጜለት አድርጓል።

ዹኹተማ አስተዳደሩም ዚጜርሐ ምኒሊክ ሕንጻ ግንባታ ጉዳይንም ሆነ ሌሎቜ ቀተ ክርስቲያን ያቀሚበቻ቞ውን ዚይዞታ ይገባኛል፣ዚምትክ ቊታና ዚካሳ ክፍያ ሁኔታዎቜን በተመለኹተ ዹሰጠውን ውሳኔ ለጠቅላይ ቀተ ክህነት በደብዳቀ አሹጋግጩ አሳውቋል።

ኹዚህ በተጚማሪ ክብርት ኚንቲባዋ ቀደም ባሉ ጊዜያት ለቀተክርስቲያን ዚተመለሱ፣ ካርታ ወጥቶላ቞ው ዚነበሩና በተለያዩ ምክንያቶቜ ካርታ቞ው እንዲመክኑ ዹተደሹጉ ይዞታዎቜና መሰል ጥያቄዎቜን በአግባቡ በመመርመር ዚማያዳግም ምላሜ እንዲሰጥ ለሚመለኹተው አካል ግልጜ መመሪያ ሰጥተዋል። ቅድስት ቀተክርስቲያናቜንም በኹተማ አስተዳደሩ ዹሚኹናወነውን ዚልማት ሥራ ተኚትሎ ኹኹተማ አስተዳደሩ ጋር በመነጋገር፣ በመመካኚርና በመወያዚት መፍትሔ በሚያስፈልጋ቞ው ጉዳዮቜ ዙሪያ በጋራ መፍትሔ በማስቀመጥ በስምምነት እዚሠራቜ መሆኑን ተኚትሎ ዹኹተማ አስተዳደሩ ቀተ ክርስቲያን ዚምታነሳ቞ውን ጥያቄዎቜና ሃሳቊቜ ሁሉ በቅንነት በመመልኚት እዚሰጠ ላለው ዘላቂ መፍትሔ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን ልባዊ ምስጋናዋን ታቀርባለቜ።

በአጠቃላይ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን በአዲስ አበባ ኹተማ ዚሚካሔደውን ዚኮሪደር ልማትን መሰሚት በማድሚግ ኹዚህ በታቜ ዚተዘሚዘሩትን ዋና ዋና ተግባራት ኹኹተማ አስተዳደሩ ጋር በመወያዚትና በመስማማት አኚናውናለቜ እነርሱምፊ

፩ኛ. በመንገድ ማስፋፋትና በአደባባይ ሥራ ምክንያት በፈሚሱ ዚቀተ ክርስቲያናቜን ቊታዎቜ ምትክ ዹኹተማ አስተዳደሩ በሚሰጠን ካሳና ምትክ ቊታዎቜ ላይ ቀተ ክርስቲያናቜን ዚልማት ሥራዎቜን እንደምታኚናውንፀ

፪ኛ. በመንገድ ኮሪደሩ ዳርቻ አካባቢ ዹሚገኙ ዚቀተክርስቲያናቜን ሕንጻዎቜን በተመለኹተ ሕንጻዎቻቜን ዹኹተማውን ውበት በሚመጥኑና ዹኹተማ አስተዳደሩ ለእድሳት ያወጣውን መስፈርት መሠሚት ባደሚገ አግባብ ባሉበት ሆኔታ እንደሚታደሱ እንደምታደርግና ይኾው ዚእድሳት ሥራ መኹናወን መጀመሩፀ

፫ኛ. ዚቀተ ክርስቲያናቜንን ቀት ተኚራይተው ዚሚኖሩ ወገኖቜ ዚሚኖሩበት ቀትና ሕንጻ በሚፈርስበት ጊዜ እንደ ማንኛውም ዚልማት ተነሺ ሁሉ ኮንዶሚኒዚምና ዹቀበሌ ቀት እንደ ፍላጎታ቞ው እንዲሰጣ቞ው ዹሚደሹግ መሆኑን ኚስምምነት ላይ መደሚሱና ይህንንም ቀተክርስቲያናቜን በደስታ እንደምትቀበለውፀ

፬ኛ. ዚቀተ ክርስቲያናቜንን ዚንግድ ቀት ተኚራይተው ዚንግድ ሥራ቞ውን ያኚናውኑ ዚነበሩና ኚልማቱ ጋር ተያይዞ ንግድ ቀታ቞ው ዚፈሚሰባ቞ው ነጋዎዎቜ ለሌሎቜ ነጋዎዎቜ በተዘጋጀው ቊታ ላይ ምትክ ቊታ እንዲሰጣ቞ው እንዲደሚግ ኹኹተማ አስተዳደሩ ጋር ስምምነት ላይ መደሚሱና ዝርዝር ሥራውም በሒደት ላይ ዹሚገኝ መሆኑፀ

፭ኛ. በፒያሳና በሌሎቜ አካባቢ ዚነበሩ ዚቀተ ክርስቲያናቜን በርካታ ዹጭቃ ቀቶቜ ዚልማቱን ሥራ ተኚትሎ እንዲፈርሱ ዹተደሹጉ መሆኑን ተኚትሎ ኚገቢ አንጻር ለጊዜው ዚተጎዳን ቢመስልም በተለያዩ ቊታዎቜ ተቆራርጠው ዚነበሩ ይዞታዎቜ በዚያው በፈሚሱበት አካባቢ ሰብሰብ ብለው በአንድ ቊታ በርኚት ያሉ ካሬ ሜትር ቊታዎቜ እንዲሰጠን ስለሚደሚግና በሚሰጠን ቊታ ላይ ዘመኑን ዹዋጁ በገቢም ዚቀተ ክርስቲያናቜንን ዚገቢ አቅም ዚሚያሳድጉ ሕንጻዎቜን ዚምንገነባበት ሁኔታ ዹሚፈጠር መሆኑ ዚኚተማቜንን ዚኮሪደር ልማት ተኚትሎ ኹኹተማ አስተዳደሩ ጋር በመሆን ካኚናወና቞ው ዋናዋና ሥራዎቜ መካኚል ጥቂቶቹ ና቞ው።

ኹፍ ሲል ኚተራ ቁጥር ፩ – ፭ ዚተጠቀሱና በቀጣይ ዚልማት ሥራውን ተኚትሎ ዹሚኹናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን ዚሚኚታተሉ፣ ዚቀተክርስቲያናቜንን መብት በአግባቡ ዚሚያስኚብሩና ዚሚያስፈጜሙ ዐቢይና ንዑሳን ኮሚ቎ዎቜ በጠቅላይ ቀተ ክህነት አስተዳደር ጉባኀ ተሰይመው ወደ ሥራ እንዲገቡ መደሹጉን እዚገለጜን መላው ዚመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቜን ዚልማት ሥራውን በተመለኹተ ዹሚኹናወኑ ዝርዝር ተግባራት በዹጊዜው ዚሚገለጹ ስለሆነ አፈጻጞማ቞ውን በተመለኹተ ኚቅድስት ቀተክርስቲያናቜሁ ጎን በጜናት በመቆም መንፈሳዊ ግዎታቜሁን እንድትወጡ መልዕክታቜንን እናስተላልፋለን።

ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን
መንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጜሕፈት ቀት
ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሚያዚያ ፲፱ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም.
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ

“ንጹሕ ምንጭ ኢትዮጵያ ልዩ ታሪካዊ ዐውደ ርእይ” በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም፣ ወእጚጌ ዘመንበሹ ተክለ ሃይማኖት ሐዋርያዊ ጉብኝትና ቡራኬ ተጠናቀቀ።

ሚያዚያ ፲፬ቀን፳፻፲ወ፮ ዓ/ም

በኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን መንበሹ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጜ/ቀት ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አዘጋጅነት ‹‹ኊርቶዶክሳዊ ብዙኃን መገናኛ ለኊርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን›› በሚል መሪ ቃል በተደሹገው ዚሥልጠና፣ ውይይትና ዹምክክር መርሐ-ግብር በተሳተፍን ዚቀተ ክርስቲያን ልጆቜ ዹቀሹበ ዹአቋም መግለጫፀ

ሚያዝያ 7 ቀን 2016 ዓ/ም

ኊርቶዶክሳውያን ብዙኃን መገናኛ ተቋማትና ማኅበራዊ ሚዲያዎቜ ሐሰተኛ ወሬ ባለመቀበል እና ባለማስተላለፍ ኃላፊነታ቞ውን ሊውጡ እንደሚገባ ብፁዕ አቡነ አብርሃም አሳሰቡ።

“ሥርዓተ ቀተክርስቲያንን በጣስ መልኩ ምስጢራተ ቀተክርስቲያን እና ሥርዓተ አምልኮ በዲጂታል ሚዲያ ዚሚያስተላልፉ አገልጋዮቜ እና ሌሎቜ ዚማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎቜ ኚድርጊታ቞ው መቆጠብ ይገባ቞ዋል” ብፁዕ አቡነ አብርሃም

ኊርቶዶክሳውያን ብዙኀን መገናኛ ለኊርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን

ዚኢ.ኩ.ተ.ቀ. ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ “ኊሮቶዶክሳዊያን ብዙኀን መገናኛ ለኊርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቀተክርስቲያን” በሚል ርዕስ በዛሬው ዕለት ዚሥልጠና፣ ዹምክክርና ዚውይይት መድሚክ በጁፒተር ኢንተርናሜናል ሆቮል አካሂዷል።

ብፁዕ አቡነ ሩፋኀል  ዚደምቢ ደሎ ደ/ጾሐይ መድኃኔዓለም ካ቎ድራልን ቅዳሎ ቀት አኚበሩ።

ብፁዕ አቡነ ሩፋኀል  ዹቄለም ወለጋ፣ ዚጋምቀላ ክልልና ደቡብ ሱዳን፣ ዚቀ/ጉሙዝ አሶሳ አህጉሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ፣ ዹሰላምና ዚልማት አምባሳደር  በዛሬው ዕለት በ27/07/2016 በደምቢ ዶሎ ደ/ጾሐይ መድኃኔዓለም ካ቎ድራል በመገኘት ዚታደሰውን ሕንጻ ቀተ ክርስቲያን በመባሚክ፣ ቅዳሎ ቀቱን አክብሚዋል።

ዚብፁዕ አቡነ ሩፋኀል ሐዋርያዊ ጉዞ

ብፁዕ አቡነ ሩፋኀል ዹቄለም ወለጋ፣ ዚጋምቀላ ክልልና ደቡብ ሱዳን፣ ዚቀ/ጉሙዝ አሶሳ አህጉሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ፣ ዹሰላምና ዚልማት አምባሳደር ዚቅዱስ ሲኖዶስ አባል በዛሬው ዕለት (26/07/2016) ሐዋርያዊና መንፈሳዊ ጉዞአቾውን ኚአዲስ አበባ ወደ ቄለም ወለጋ ሀገሹ ስብኚት ደምቢ ዶሎ በማድሚግ ላይ እንዳሉ በዳሌ ሰዲ ወሚዳ ቀተ ክህነት ጫሞ ቅድስት ማርያም ቀተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደርጎላ቞ዋል።

በቁልቢና አካባቢው ልዩልዩ ዚልማት ሥራዎቜ እንዲኚናወኑ ውሳኔ ተለይተው ተላልፏል።

መጋቢት ፳፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም

ዚጜርሐ ጜዮን ዘተዋሕዶ ዚሐዋርያት አንድነት ኑሮ ማኅበር  በማሰልጠኛ ማዕኹሉ ያስተማራ቞ውን ተማሪዎቜ አስመሚቀ ።

ዚጜርሐጜዮን ዘተዋሕዶ ዚሐዋርያት አንድነት ኑሮ ማኅበር ዚሰባክያነ ወንጌልና ዚአብነት ትምህርት ማሠልጠኛ  ለቀተክርስቲያን  ዘቢብ ጧፍ   ጥላ  ሻማ ብቻ ሳይሆን ሰውንም እንስጥ በሚል  መሪ ቃል ዹተቋቋመ ማሰልጠኛ ማዕኹል  እንደመሆኑ መጠን ኚልዩ ልዩ አህጉሹ ስብኚቶቜ ዚተወጣጡ ሰልጣኞቜን  በዹቋንቋቾው አሰልጥኖ አስመርቋል።