የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የጽርሐ ጽዮን ዘተዋሕዶ የሐዋርያት አንድነት ኑሮ ማኅበር በማሰልጠኛ ማዕከሉ ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቀ ።

April 1, 2024

መጋቢት 23/2016 ዓ.ም
“””””””””””””””””””””””
አዲስ አበባ- ኢትዮጵያ
******

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የጽርሐጽዮን ዘተዋሕዶ የሐዋርያት አንድነት ኑሮ ማኅበር የሰባክያነ ወንጌልና የአብነት ትምህርት ማሠልጠኛ ማዕከል የ 32ኛ ዙር የበጋ ሠልጣኞች ምረቃና  እና ለቀጣይ ሥልጠና  የሚውል የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡባዊና ደቡባዊ ምሥራቅ ትግራይ አህጉረ ስብከት፣ በኢ/ኦ/ተ/ቤ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የቤተ መጻሕፍት ወመዘክር እና የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ  ዩንቨርሲቲ አዳራሽ አከናውኗል

የጽርሐጽዮን ዘተዋሕዶ የሐዋርያት አንድነት ኑሮ ማኅበር የሰባክያነ ወንጌልና የአብነት ትምህርት ማሠልጠኛ  ለቤተክርስቲያን  ዘቢብ ጧፍ   ጥላ  ሻማ ብቻ ሳይሆን ሰውንም እንስጥ በሚል  መሪ ቃል የተቋቋመ ማሰልጠኛ ማዕከል  እንደመሆኑ መጠን ከልዩ ልዩ አህጉረ ስብከቶች የተወጣጡ ሰልጣኞችን  በየቋንቋቸው አሰልጥኖ አስመርቋል።

በዛሬው ዕለት 59 ተማሪዎች ከ 21 አህጉረ ስብከት የተወጣጡ ሲሆን 20 በሚደርሱ ልዩ ልዩ ቋንቋዎች መሰልጠናቸው በመርሐ ግብሩ  ላይ ተገልጿልተገልጿል።

በምረቃው ላይም በማኅበረ ቅዱሳን አባላት የበገና ዝማሬን ፣ በመጋቤ ሐዲስ ወልደ ትንሣኤ ትምህርተ ወንጌል ተሰጥቷል  እንዲሁም ማኅበሩ  አስተምሮ ለምረቃ ካበቃቸው ተመራቂ ተማሪዎች  መካከል በአማርኛ ፣ ኦሮምኛ ፣ሃድይኛ ፣ ማሊኛ ፣ዴምኛ ፣ ቤንችኛ ቋንቋዎች ጣዕመ ዝማሬ ቀርቧል።

ማኅበሩ ከሀገር ውስጥ ቋንቋዎች በተጨማሪ በውጭ ቋንቋዎች በእንግሊዝኛ ፣ ጀርመንኛና ሱዋህሊኛን ጨምሮ በ77 ቋንቋዎች 2,116 ደቀ መዛሙርትን በማስተማር  ከ1990 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ ነፍሳትን ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መልሷል፡፡

በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስን ጨምሮ በርካታ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ፣ ተመራቂ ተማሪዎች እና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የመልአከ ፀሐይ መኰንን ደስታ ግብአተ መሬት ተፈጸመ። Link to: የመልአከ ፀሐይ መኰንን ደስታ ግብአተ መሬት ተፈጸመ። የመልአከ ፀሐይ መኰንን ደስታ ግብአተ መሬት ተ... Link to: በቁልቢና አካባቢው ልዩልዩ የልማት ሥራዎች እንዲከናወኑ ውሳኔ ተለይተው ተላልፏል። Link to: በቁልቢና አካባቢው ልዩልዩ የልማት ሥራዎች እንዲከናወኑ ውሳኔ ተለይተው ተላልፏል። በቁልቢና አካባቢው ልዩልዩ የልማት ሥራዎች እንዲከናወኑ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top