የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

በቄለም ወለጋ ሀገረ ስብከት መዋቅራዊ አደረጃጀቱን የጠበቀ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ገለጹ።

August 25, 2023

ነሐሴ ፲፱ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም
“””””””””””””””””””””””

– ለሀገረ ስብከቱ ሠራተኞች፣ ለ13 ወረዳ ሊቃነ ካህናትና ሠራተኞች ከ2.1 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ተደርጎ የስምንት ወር ደመወዝ ተከፍሏቸዋል።

– ለ317 ነዳያን ከ ብር 523,000.00 በላይ ወጪ ተደርጎ ድጋፍ ተደርጓል።

– በሀገረ ስብከቱ መዋቅራዊና ሕጋዊ አግባብን የተከተለ አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል።

– በሀገረ ስብከቱ ፣በካህናት፣ በምዕመናን፣ በወጣቶችና በሕዝበ ክርስቲያኑ መካከል መልካም የሚባል ሕግና ሥርዓትን የጠበቀ ግንኙነት በመጠናከሩ ሠፊ መንፈሳዊ አገልግሎት በመሰጠት ላይ ይገኛል።

የጋምቤላ፣ የአሶሳ፣ የቄለም ወለጋና የደቡብ ሱዳን አህገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል በግንቦት ወር ፳፻፲፭ ዓ/ም በተካሔደው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ የተወሰኑ አህጉረ ስብከት አዳዲስ ጳጳሳት መሾማቸውን ተከትሎ ጳጳሳቱ ወደየተሾሙባቸው አህጉረ ስብከት በመሔድ አገልግሎት እንዲጀምሩ ቅዱስ ሲኖዶስ ያስተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ብፁዕነታቸው አንዱ ሀገረ ስብከታቸው ወደ ሆነው ወደ ቄለም ወለጋ ሀገረ ስብከት መጓዛቸውን በመግለጽ በሀገረ ስብከቱ ባለፉት ጥቂት ጊዜያት የተከናወኑትን ዋና ዋና ሥራዎች በመግለጽ መረጃውን አድርሰውናል።

በዚህም መሠረት በጥር ወር ፳፻፲፭ ዓ/ም የተከናወነውን ሕገ ወጥ ሢመት ተከትሎ በተፈጠረው ችግር ምክንያት ላለፉት ስምንት ወራት ደመወዛቸው ሳይከፈላቸው የቀሩ የሀገረ ስብከቱና የወረዳዎቹ ሊቃነ ካህናትና ሰራተኞች መደበኛ ሥራቸውን እንዲጀምሩ በማድረግ ተቋርጦ የቆየውን ደመወዛቸውን ከሁለት ሚሊየን አንድ መቶ ሺህ ብር በላይ ወጪ በማድረግ እንዲከፈላቸው ተደርጓል ያሉት ብፁዕነታቸው ከሦስት መቶ አሥራ ሰባት በላይ ለሚሆኑ ነዳያንም ከአምስት መቶ ሀያ ሦስት ሺህ ብር በላይ ወጪ በማድረግ ድጋፍ መደረጉን ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት ሀገረ ስብከቱ በተረጋጋ መልኩ መዋቅራዊ አንድነቱን በማጠናከር ሥራውን እየሠራ ነው ያሉት ብፁዕነታቸው ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከምዕመናንና ከወጣቶች ጋር ባደረግናቸው ተደጋጋሚ ውይይቶች መዋቅራችንን በማስከበር ሥራዎቻችንን በሚገባ ማከናወን የምንችልበት ስልት ቀይሰን በመሥራት ላይ እንገኛለን፤ ሀገረ ስብከታችንም ፍጹም ሰላማዊና ሥራዎች በመግባባት የሚከናወኑበት ተቋም በመሆን ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።

በማያያዝም በሀገረ ስብከቱ ሥር በምትገኘው በታሪካዊቷና በንጉሥ ጆቴ ቱሉ ዘመን በተተከለችው በታቦር ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ጾመ ፍልሰታ ለማርያምን ማሳለፋቸውን የገለጹት ብፁዕነታቸው ነሐሴ ፲፮ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም በተከበረው የፍልሰታ ለማርያም በዓል ላይ ቤተክርስቲያኑ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት መልካም ፈቃድ የካቴድራልነት ማዕረግ እንደተሰጠው ገልጸዋል። ከሐምሌ ፳፰ ቀን ፳፱፲፭ ዓ/ም ጀምሮ በሀገረ ስብከቱ ሐዋርያዊ አገልግሎት ላይ የሰነበቱ መሆናተውን የገለጹት ብፁዕነታቸው በሀገር ሽማግሌዎችና በአባ ገዳዎች ደማቅ አቀባበል እንደተደረገላቸው አስታውሰው እስከ ዘመን መለወጫ ድረስ በሀገረ ስብከቱ የሚሰጡትን አገልግሎት አጠናክረው እንደሚቀጥሉና በሀገረ ስብከቱ መንፈሳዊ ትምህርታቸውን ሲከታተሉና በየደረጃቸው ሲያገለግሉ ለቆዩ በርካታ አገልጋዮች ሥልጣነ ክህነትን እንደሚሰጡም ጨምረው ገልጸዋል።

Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ዙሪያ የተላለፈ የሰላም መልዕክት፧ Link to: ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ዙሪያ የተላለፈ የሰላም መልዕክት፧ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ... Link to: በሰሜን አሜሪካ ተተኪ ካህናትን በበቂ ሁኔታ የማፍራት ሂደት ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) ገለጹ። Link to: በሰሜን አሜሪካ ተተኪ ካህናትን በበቂ ሁኔታ የማፍራት ሂደት ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) ገለጹ። በሰሜን አሜሪካ ተተኪ ካህናትን በበቂ ሁኔታ የማፍራት...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top